Why Pay for Entertainment? Access Thousands of Free Downloads Now!

Getachew shiferaw

Description
Advertising
We recommend to visit

ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ

Last updated 2 days, 4 hours ago

ለማንኛውም አስተያየት እና ጥቆማ 👉 @Esat_tv_comment_bot

🇪🇹ኢሳት የኢትዮጵያ አይን እና ጆሮ🇪🇹

Last updated 2 weeks, 5 days ago

Last updated 2 weeks, 5 days ago

1 week, 4 days ago

የሱዳን ዋና ዋና ሚዲያዎችኀ ትህነግ/ህወሓት የአልቡርሃን ቆጥረኛ ሆኖ በሱዳን እየተዋጋ መሆኑን ቀዳሚ አጀንዳ አድርገዋል። ይህን ቅጥረኛ ኃይል ነው ያለ ምንም ቅድመ ሁኔታ ተፈናቃይ ብላችሁ መልሱ እየተባለ ያለው።

1 week, 6 days ago

የፕሪቶሪያ ስምምነት መቆመሪያቸው ነው!

ስምምነቱ እነ ጌታቸው ረዳ ከአማራ ለመንጠቅ የሚፈልጓቸውን ግዛቶች "የተወረሩ" አይላቸውም። "አወዛጋቢ" ነው የሚላቸው። በዚሁ ስምምነት መሰረት የጥላቻና የጦርነት ቅስቀሳ የተከለከለ ነው። በትህነግ በኩል ፈራሚው ጌታቸው ረዳ ግን አሁንም "ወራሪ" እያለ እየፃፈ ነው። የሰላም ስምምነት ተብሎም ለእሱ አማራ ወራሪ ነው። ስምምነቱ መቋመሪያ ካርድ እንጅ እንደማያከብሩት ይታወቃል። በጓዳ ግዛቶቹን አሳልፎ ለመስጠት የሚስማማው የአብይ አገዛዝም በስምምነቱ መሰረት ባቋቋመው ኮሚቴ ይህን እንደማይገመግም ይታወቃል።

የአማራ ክልል ጉልት ካድሬ ደግሞ በስምምነቱ መሰረት በስሩ እንዲቆይ የተወሰነውንም አስተዳደር አፍርሶ ትግራይ ውስጥ አንድ ቀበሌ በቅጡ ለማያስተዳድረው፣ ስካይ ላይት መቀመጫውን ላደረገው ጌታቸው ረዳ አሳልፎ ሰጥቷል። በዚህ ከቀጠለ አብይ አጠቃላይ አማራ ክልልን ለጌታቸው ረዳ ጊዜያዊ አስተዳደር ቢሰጠውም ከዝምታ የተሻለ ከአማራ ክልል ካድሬ እንደ አማራጭ የሚቆጠር ስልት ያለ አይመስልም።

በዚህ በዓል መልዕክት ቀርቶ በሌላም ጊዜ በአማራ ላይ አፍ መክፈትን የህዝብ መሰብሰቢያ ካደረጉት የትህነግ አመራሮች ውጭ ጦርነት እየቀሰቀሰ ያለ አይመስልም። ለትንሳኤ በዓል መልዕክት እንኳን አማራን በለመዱት ክፍታፍነታቸው ከመዝረፍና ከመውቀስ የሚመለሱ አይደሉም።

1 week, 6 days ago

የባልደራስን ንቁ አባላት ያሳሰረው ኤርሚያስ ለገሰን ተንኮል ተመልከቱ!

የኤርሚያስ ወዳጅ የነበረው ቴድሮስ ፀጋዬ ሰሞኑን ኤርሚያስ የባልደራስ ንቁ አባላትንና የአዲስ አበባ ወጣቶችን እየጠቆመ እያሳሰረ እንደሚገኝ በቀጥታ ስርጭት ተናግሯል። ይህን የባልደራስ የቅርብ አመራሮችም አረጋግጠውልኛል።

ትናንት የሰራውን ፕሮግራም እንኳን ተመልከቱ። ያሳሰራቸው የባልደራስ ንቁ አባላት መካከል ናቲን ፎቶ የፊት ገፅ ላይ ሆን ብሎ አቀናብሮ ከሚከሳቸው የፋኖ አባላት ጋር አቅርቧል። ኤርሚያስ ለፕሮፖጋንዳ የሚጠቀምበትን እያንዳንዱን ጉዳይ የሚያውቅ ሰው ነው። የፊት ገፅ ሲያሰራ ምን ማስተላለፍ እንደፈለገ ግልፅ ነው። ከሰላማዊ መንገድ ውጭ የትጥቅ ትግሉ ላይ ፈፅሞ የሌሉበትን ወጣቶች ፎቶ ሾፕ እየሰራ ጭምር የሀሰት ጥቆማውን እውነት ለማስመሰል እየሰራ ያለ አደገኛ ሰው ነው።

ከቅርቡ የአዲስ አበባ ክስተት በኋላ አዲስ አበባ ላይ ሽብር የሚፈፅሙት የከተማው ተወላጆች ጭምር አሉ ብሎ የአዲስ አበባን ወጣት በሀሰት ከስሷል። በተለይ በተለይ ባልደራስ ሰልፍና ስብሰባ ሲያደርግ ንቁ እንቅስቃሴ ያደርጉ የነበሩ፣ በሚዲያ ያግዛል ተብሎ መረጃ የሚሰጡትና ለፓርቲው ሰላማዊ እንቅስቃሴ በተለያያዩ የማህበራዊ ሚዲያ ግሩፕ ውስጥ የነበሩትን ለአገዛዙ እየጠቆመ አሳስሯል። የባልደራስ አመራሮችም ያረጋገጡት መረጃ ነው።

2 weeks, 4 days ago
Getachew shiferaw
2 weeks, 4 days ago

የትህነግ ታጣቂ ራያ ላይ እየፈፀመው ያለው ሰቆቃ በገለልተኛ ሚዲያ እይታ!

ከስር ያለው መረጃ ዓል አይን አማርኛ የትህነግ ታጣቂ እየፈፀመው ያለውን ተነግሮ የማያልቅ ሰቆቃ በወረራ ስር ያሉትን ነዋሪዎች አናግሮ ከዘገበው የተወሰደ ነው።

#የትግራይ ታጣቂዎች ከመጡበት ዕለት አንስቶ ንብረታችን እየተነጠቀ ነው፡፡ ለገበያ የደረሰ ሀብ ሀብ አትክልቴን በልተውብኛል ሲጠግቡ ደግሞ በያዙት ጦር መሳሪያ በሰደፉ እና በአፈሙዙ እየመቱብኝ ነው”

#በቀበሌያችን ከገቡበት ከሰኞ ከሰዓት በኋላ ጀምሮ በገበሬው ቤት እየገቡ እየደበደቡን ነው። አርሶ አደር ጦር መሳሪያ አምጡ እያሉ እኛ ገበሬዎች ነን ፖለቲካ አናውቅም ብንልም ሊተውን አልቻሉም"

#ከዚህ በፊት አብረውን ይኖሩ የነበሩ ነገር ግን በስጋት ምክንያት ወደ ትግራይ ተፈናቅለው የነበሩ ሰዎች ካሳለፍነው ሰኔ እና ግንቦት ወር ጀምሮ እየገቡ መኖር ጀምረዋል፣ ሳይገቡ የቀሩት ከዚህ በፊት በነበረው አስተዳድር ጊዜ ህዝብን ሲያንገላቱ እና ሲያማርሩ የነበሩት ብቻ ቀርተው ነበር"

#ታጣቂዎች ሲቪል እየለበሱ ወደ ከተማዋ ነዋሪ መስለው እየገቡ ነው፣ የመንግስት ተቋማትን እየዘረፉ እና ፋይሎችን እያወደሙ የከተማዋ ነዋሪዎችንም ፍርሃት ውስጥ እንዲገባ የተለያዩ ጫናዎችን እያደረጉ ነው። በከተማዋ ያለው የፌደራል የጸጥታ ሀይል ቢኖርም ነዋሪውን ከመሰደድ አልታደገውም"

#የፌደራል መንግስት ለራያ እና አላማጣ ጉዳይ ዘለቄታዊ መፍትሔ ይሰጠዋል ብለን እየጠበቅን ለትግራይ ታጣቂዎች አሳልፎ ሰጥቶናል።

#በሰሌን ውሃ ቀበሌ የሚኖረው ሌላኛው አስተያየት ሰጪ በበኩሉ የትግራይ ታጣቂዎች የራያ እና አላማጣ የገጠር ቀበሌዎችን ሙሉ ለሙሉ በሚባል ደረጃ መቆጣጠራቸውን፣ በየቀኑ አዳዲስ እና ተጨማሪ ታጣቂዎች ወደ አካባቢዎቹ እየገቡ መሆኑን አክሏል፡፡
ታጣቂዎቹ በየሰው ቤት እየገቡ የልጆችን ምግብ ሳይቀር እየበሉ እንደሆነ፣ ለባሏ የምሳ እቃ ለማድረስ ወደ እርሻ ቦታ እየሄደች ያለችን እናት ለአማራ ታጣቂ ልትሰጪ ነው በሚል እያንገላቱ ነው ያሉት እኝህ አስተያየት ሰጪ ታጣቂዎቹ ይህን ሲያደርጉም የፌደራል የጸጥታ ሀይሎች እያዩ የማስቆም ፍላጎት እንደሌላቸውም ነግሮናል፡፡

#ከዚህ በፊት ከመኖሪያ ቤታቸው ተፈናቅለው ወደ መቀሌ እና ሽሬ የሄዱ ነዋሪዎች ወደ ቀድሞ ቤታቸው ተመልሰው አብረን በጋራ እያረስን እና እየኖርን ቢሆንም ታጣቂዎቹ በድንገት መጥተው ለእንግልት እንደዳረጓቸውም አክሏል፡፡

#ታጣቂዎቹ በየጊዜው እየሰበሰቡም ከእንግዲህ እምናስተዳድራችሁ እኛ ነን፣ የያዛችሁትም የአማራ ክልል የነዋሪነት መታወቂያ ከእንግዲህ አይጠቅማችሁም፣ ልጆቻችሁን አምጡ እና ለአማራ ታጣቂዎች ድጋፍ እያደረጋችሁ ነው የሚሉ ወከባዎችን እያደረሱባቸው እንደሆነም እኝህ አስተያየት ሰጪ ተናግረዋል፡፡

#ወቅቱ የሚያዚያ ወር አዝመራ የምናዘምርበት ቢሆንም እርሻችንን ትተን በየቀኑ ምን እንሆን ይሆን የሚል ስቃይ ውስጥ ነን"

2 weeks, 5 days ago

ተፈናቃይ ብለው የሚያስገቡት ይህንን ዘራፊ ኃይል ነው!

ትህነግ በወረራው ወቅት አማራና አፋርን መዝረፍን ጀብዱ አድርጎ ለወጣቱ አስተማረው። አትክልትና ፍራፍሬ ጭምር "ከአማራ ክልል የመጣ" እየተባለ በሞንታርቦ እየተጮኸ ሲሸጥ ነበር። የአማራ ክልል ታርጋን አንስተው ታርጋ አልባ መኪና የሚነዱት "አምጥቶ ነው" እየተባሉ በጀብድ ተነገረላቸው። እርጉዝ ሳይቀር ለዘረፋ መጥታ አማራ ወልዳ ተይዛለች። ወጣቱ "እኔም ይህን አምጥቻለሁ" እያለ በጀግንነት እንዲያወራ ተደረገ። ከጦርነቱ በኋላ ግን ዘረፋውን ትግራይ ውስጥ ቀጠሉት። አማራ ላይ ጀግና የተባሉበት ነዋ! የቀራቸው ነገር የለም። ፍርድ ቤት ስላልቻለ እንደ ድሮው በአደባባይ በዚህ መልክ መቅጣት ጀምረዋል።

ታዲያ ወደ ራያ የላኩት ይህን ዘራፊ ኃይል ነው። አዲስ ልብስና ጫማ ሳይቀር እያስወለቀ ሲወስድ የሚታወቅ ዘራፊ ራያን እያራቆተ ነው። በወረራው ወቅት ሲዘርፍ ጀግና ያሉትና ከወረራ በኋላ ትግራይን ያስመረረውን ነው ወደ ራያ የላኩት። ወደ ጠለምትና ወልቃይትም ለማስገባት የወሰኑት ይህ ሰው በላ የሆነን ኃይል ነው።

3 weeks, 5 days ago

የአማራ ንብረት ወደ መቀሌ እየተጫነ ነው!

በትህነግ ከተወረረው ራያ አካባቢዎች የተፈናቀሉ ንፁሃንን አነጋግሮ ሰሜን ወሎ ዞን መረጃ አጋርቷል። ከእነዚህ መካከል፦

1) የትህነግ ታጣቂ በወረራ በያዛቸው የራያ ባላ፣ የራያ አላማጣ፣ የወፍላ ወረዳ እንዲሁም የአላማጣ እና የኮረም ከተማ አስተዳደሮች የሚገኙ የመንግስት እና የሃይማኖት ተቋማቶች ንብረት በመቅደድ፣በማቃጠልና ወደ መሃል ትግራይ ሲጭን ሰንብቷል።

ከሞቀ ቤታቸው ወጥተው በቆቦ ከተማ ተፈናቅለው ለሚገኙት ተፈናቃዮች የምግብ ዱቄት ይዘው የመጡት የአስተዳደሩ ተወካዮች ይህ ድጋፍ ለዚህ ህዝብ የሚመጥንና የሚገባ ሆኖ ሳይሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ስንገናኝ ባዷችንን ከምንመጣ በማሰብ ሲሆን፣ የደሴ እና የኮምቦልቻ ህዝብ አምሳያው የሆነው የራያ እና የወፍላ ሕዝብ ወደ ቀየው እንዲመለስ አስፈላጊውን ሁሉ እንደሚያደርጉ ተናግረዋል፡፡

2) የአርሶ አደሩን የአትክልትና የፍራፍሬ ውጤቶች የሚጫነው ተጭኖ ያልቻሉትን ማውደማቸውንና ማፈናቀላቸው ታውቋታውቋል።

3) ቤት ለቤት በመፈተሽ ወጣቶችን ባለፈው ጦርነት ተሳትፏል በሚል ግድያ እየፈፀሙ ስለሆነም ተጨማሪ መረጃዎች ወጥተዋል።

ትህነግ/ህወሓት ራያን መሬቱን እንጅ ህዝቡ የትግራይ እንዳልሆነ እንደማይክደው የሰሞኑ ክስተት ማሳያ ነው። ከራያ የህዝብ ንብረትን ዘፈው እያጓጓዙ ያሉት ወደ ራሳቸው ግዛት ወደ ትግራይ ነው። ራያ ግዛታቸው ስላልሆነ የሚዘረፍና የሚጨፈጨፍ ጠላታቸው አድርገው የፈረጁት ነው።

3 weeks, 5 days ago
Getachew shiferaw
3 weeks, 5 days ago
Getachew shiferaw
3 weeks, 5 days ago

ይችን ጉድ ተመልከቷት!

የአብይ አህመድ ብልፅግና ራሱ በመራው ጦርነት "የዘር ፍጅት ተፈፀመብን" ካሉት የትህነግ አካላት ጋር አብሮ እየሰራ መሆኑን "ኮምሽን" አዋቅረው የሚንቀሳቀሱት ተናግረዋል።

ዓለም አቀፍ ገለልተኛ ምርመራ ይደረግ ተብሎ ጥረት ተደርጎ ነበር። ዶክተር ዳንኤል በቀለ የሚመራው አሰመኮና ተመድ በጋራ ይመረምራሉ ከተባለው በሻገር ሌሎችም ሙከራ አድርገው ትህነግ/ህወሓትና አብይ ተስማምተው ምርመራውን አስቁመዋል። ዓለማቀፍ አጣሪዎችን አስቁመው ትህነግ መጀመሪያ ከጥናት በፊት የዘር ፍጅት ተፈፅሟል ብሎ ደምድሞ ያስጀመረውን የትርክት ፕሮጀክቶት ግን አብይ ደግፎ እያሰራው ነው።

ትልቁ ሚስጥር ደግሞ ከአብይ ጋር ብቻ ሳይሆን ከአብይና ከዓለም ባንክ ጋር እንደሚሰሩ የገለፁበት ነው። ዝም ብሎ ትብብር አይደለም። ይህን እውቅና ካልሰጠ ገንዘብ አይሰጥህም ተብሏል። በየጊዜው የብድር ድርድር ሲኖር ትህነግ በማያገባው እግሩን እንዲያስገባ ይፈቀድለታል። የሰሞኑ የራያ ወረራም አብይ ቢሊዮን ዶላሮችን ይሰጡኛል ካላቸው የገንዘብ ተቋማት ጋር ድርድር ሲያደርግ የተፈፀመ ነው። የአማራ ርስቶችን የመበደሪያና የእርዳታ ቀብድ አድርጓቸዋል። አንድ የትህነግ ሰው "ወደራያ የገባነው በአሜሪካ ቀጭን ትዕዛዝና በአብይ ይሁንታ ነው" ብሎ ቃል በቃል ፅፏል።

ስዩም ተሾመ ደግሞ "ህወሓትን መሳሪያ ልናስፈታው ቀርቶ ተጨማሪ መሳሪያ ሰጥተነዋል።" ብሏል። ይህ ሁሉ የጓዳ ውሎቹ መገለጫ ነው። ትህነግ/ህወሓት አላማችን ያስፈፅምልናል ብለው የሚያግዙት በእርዳታና ብድር ስለመጡ ብቻ ሳይሆን አማራና ኤርትራን ካልመታን ተብሎ ብዙ ተሰርቷል። የዘር ፍጅት ተብሎ የተሰራው የትህነግ ትርክት በአብይ አህመድ ድጋፍ ማግኘቱ ሌላ የጓዳ ውል መገለጫ ነው።

We recommend to visit

ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ

Last updated 2 days, 4 hours ago

ለማንኛውም አስተያየት እና ጥቆማ 👉 @Esat_tv_comment_bot

🇪🇹ኢሳት የኢትዮጵያ አይን እና ጆሮ🇪🇹

Last updated 2 weeks, 5 days ago

Last updated 2 weeks, 5 days ago