ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።
@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna
#ኢትዮጵያ
Last updated 5 days, 15 hours ago
ለማንኛውም አስተያየት እና ጥቆማ 👉 @Esat_tv_comment_bot
🇪🇹ኢሳት የኢትዮጵያ አይን እና ጆሮ🇪🇹
Last updated 1 week, 1 day ago
Last updated 18 hours ago
አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የትምህርት መስኮች ያሰለጠናቸውን 154 ተማሪዎች አስመርቋል፡፡
ዩኒቨርሲቲው በመጀመሪያ ዲግሪ ፕሮግራም የሰለጠኑ 110 እንዲሁም በሁለተኛ ዲግሪ ፕሮግራም ትምህርታቸውን የተከታተሉ 44 ተማሪዎችን በዛሬው ዕለት አስመርቋል።
በመጀመሪያ ዲግሪ ከተመረቁት መካከል107ቱ በጤና ሳይንስ የትምህርት መስኮች የሰለጠኑ መሆናቸው ተገልጿል፡፡
የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የካንሰር ህክምና ማዕከል የፊታችን ሰኞ የጨረር ህክምና መስጠት ይጀምራል።
ማዕከሉ ለመጀመሪያ ዙር ፈቃደኛ ሆነው በተገኙ 30 ታካሚዎች ነው የጨረር ህክምና አገልግሎት መስጠት የሚጀምረው። #ኢፕድ
ሰላሌ ዩኒቨርሲቲ በተቋሙ ታሪክ የመጀመሪያ የሆነውን ጆርናል ይፋ አድርጓል።
'Salale Journal of Social and Indigenous Studies' (SJSIS) የተሰኘው የምርምር ውጤቱ፤ በዩኒቨርሲቲው የሶሻል ሳይንስ እና ስነ-ሰብ ኮሌጅ ይፋ ሆኗል።
ጆርናሉ በተለያዩ የማኅበራዊ እና አገር-በቀል ጥናቶች ላይ ትኩረት እንደሚያደርግ ከዩኒቨርሲቲው ያገኘነው መረጃ ያሳያል።
ጆርናሉ በጥልቅ የሚዘጋጁ የምርምር ውጤቶችን በኦንላይን እና በህትመት ተደራሽ እንደሚያደርግ ተገልጿል።
ራያ ዩኒቨርሲቲ በ2016 ዓ.ም አጋማሽ ዓመት የመውጫ ፈተና ካስፈተናቸው ተማሪዎች 96.47 በመቶ የሚሆኑት ተማሪዎች ፈተናውን ማለፋቸውን አሳውቋል።
በራያ ዩኒቨርሲቲ የመውጫ ፈተና ለመስጠትን የሚያስችል የተሟላ የአይ.ሲ.ቲ. መሰረተ ልማት ባለመኖሩ ምክንያት ተማሪዎቹ በመቐለ ዩኒቨርሲቲ ፈተናቸውን እንዲወስዱ መደረጉ ተገልጿል፡፡
መንትዮቹ የማዕረግ ተመራቂዎች
ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ጤና ሳይንስ ኮሌጅ በህክምና ዶክትሬት ዲግሪ በከፍተኛ ማዕረግ የተመረቁት መንትዮች፦ ዶ/ር ቸርነት ተስፋሁን እና ዶ/ር ብሩክ ተስፋሁን
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።
@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna
#ኢትዮጵያ
Last updated 5 days, 15 hours ago
ለማንኛውም አስተያየት እና ጥቆማ 👉 @Esat_tv_comment_bot
🇪🇹ኢሳት የኢትዮጵያ አይን እና ጆሮ🇪🇹
Last updated 1 week, 1 day ago
Last updated 18 hours ago