Unlock a World of Free Content: Books, Music, Videos & More Await!

ESAT (ኢሳት🇪🇹)✅®

Description
ለማንኛውም አስተያየት እና ጥቆማ 👉 @Esat_tv_comment_bot

🇪🇹ኢሳት የኢትዮጵያ አይን እና ጆሮ🇪🇹
We recommend to visit

ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ

Last updated 1 month ago

እንኳን ደህና መጡ‼

✔ማስታወቂያ ለማሰራት እና ጥቆማ ለመስጠት በዚህ ይጠቀሙ ☞https://t.me/WasuMohammed

✔ ቻናሉን ለመቀላቀል Join ☞http://t.me/Wasulife

ከልብ አመሰግናለሁ♥🙏

Last updated 1 month, 1 week ago

Last updated 1 month ago

1 month, 1 week ago
"ችግሩ ተስተካክሏል" - የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ***‼️***

"ችግሩ ተስተካክሏል" - የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ‼️

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፤ በባንኩ መረጃ ማስተላለፊያ የፋይበር ኦፕቲክስ ገመድ ላይ ተፈጥሮ የነበረው ችግር መስተካከሉን ገልጿል።

በዚህም ፦በቅርንጫፎች፥ በኢንተርኔት ባንኪንግ፥ በሞባይል ባንኪንግ፥ በሲቢኢ ብር  ላይ ተቋርጦ የነበረው አገልግሎቶች ሙሉ በሙሉ መጀመሩን አመልክቷል። ባንኩ ተፈጥሮ ለነበረው የአገልግሎት መስተጓጎልም ይቅርታ ጠይቋል።

@Esat_tv1
@Esat_tv1

1 month, 1 week ago
የአፍሪካ ኅብረት ጉባኤ በሰላምና በስኬት መጠናቀቁን …

የአፍሪካ ኅብረት ጉባኤ በሰላምና በስኬት መጠናቀቁን የጋራ ግብረ-ኃይል አስታወቀ‼️

37ኛው የአፍሪካ ኅብረት የመሪዎች ጉባዔ እና 44ኛው የስራ አስፈፃሚ ምክር ቤት መደበኛ ጉባኤ በሰላምና በስኬት መጠናቀቁን የፀጥታና ደኅንነት የጋራ ግብረ-ኃይል አስታወቀ፡፡

የአዲስ አበባ ከተማን ሰላምና ደህንነት የበለጠ ለማጠናከር፣ የትራፊክ ፍሰቱን የተሳለጠ ለማድረግ ግብረ-ኃይሉ ከጠቅላይ ሚኒስቴር ጽህፈት ቤት፣ ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር፣ ከኢትዮጵያ አየር መንገድ እና ከአፍሪካ ህብረት ጽ/ቤት ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በትብብር በመስራቱ ለተገኘው ስኬት ትልቅ አስተዋጽኦ አበርክቷል ብሏል መግለጫው።

ለጉባኤው የመጡ እንግዶች በአዲስ አበባ ከተማ በተለያዩ አካባቢዎች ሲንቀሳቀሱ በዘመናዊ ቴክኖሎጂ የታገዘ እጀባና ጥበቃ ማድረጉን የገለፀው የጋራ ግብረ-ኃይሉ መሪዎቹም በሰላም ወደ ሀገራቸው እየተመለሱ መሆናቸውን አስታውቋል፡፡

በግብረ-ኃይሉ የተሠራው ፀጥታ የማስከበር ተግባር አፍሪካን ሊወክል እና ሊያኮራ የሚችል በመሆኑ ሀገራችን የአፍሪካ ኅብረትን ለማጠናከር ያላትን ሚና እንዲሁም ቁርጠኝነት ያሳየ ነበር ብሏል መግለጫው።

መላው የሀገራችን ሕዝብ በተለይም የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪዎች እንግዶችን በክብር ከመቀበል ጀምሮ በየሆቴሎቹ ደረጃውን የጠበቀ መስተንግዶ በማድረግ፣ የሚያልፉባቸው መንገዶች ሲዘጉ በትዕግስት ቅድሚያ ሰጥቶ በማሳለፍ, ከፀጥታ ኃይሉ የሚሰጠውን መመሪያ በቅንነት በመቀበል ትብብራቸውንና አጋርነታቸውን በማሳየታቸው, የፀጥታና ደህንነት አመራሮችና አባላትም በጥብቅ ዲሲፕሊን እየተመሩ የተሰጣቸውን ኃላፊነት በመወጣታቸው ጉባኤው ያለምንም የፀጥታ ችግር በሰላምና በስኬት በመጠናቀቁ የፀጥታና ደህንነት የጋራ ግብረ-ኃይሉ ምስጋና አቅርቧል፡፡

@Esat_tv1
@Esat_tv1

1 month, 1 week ago

ለሶማሊያ ፕሬዝዳንት ክስ ኢትዮጵያ ምን ምላሽ ሰጠች‼️

የሶማሊያ ፕሬዝዳንት ሀሰን ሼክ መሃመድ በራሳቸው እና በልኡካቸው ላይ ደርሷል ስላሉት መጉላላት ላይ የኢትዮያ መንግስት ምለሽ ሰጠ።

37ኛው የአፍሪካ ህብረት ጉባዔ በዛሬው እለት በአዲስ አበባ የተጀመረ ሲሆን፤ የሶማያሊው ፕሬዝዳንት ሀሰን ሼክ መሃድ ወደ ስብሰባው እንዳይገቡ የመከልከል ሙከራ እንደተደረገባቸው አስተውቀዋል።

ፕሬዝዳንት ሀሰን ሼክ መሃመድ ከስብሰባው መክፈቻ በኋላ በሰጡት መግለጫ፤ በዝግ በሚደረገው ስብሰባ ላይ ለመሳተፍ በሚሞክሩበት ጊዜ የኢትዮያ የጽታ ኃይሎች ካረፉበት ሆቴል እንዳይወጡ መንገድ ዘግተው እንደከለከሏቸው ገልጸዋል።“በሌላ ፕሬዝዳንት መኪና ከሆቴል በመውጣት የስብሰባው ስፍራ ብደርስም፤ የፀጥታ አካት እንዳንገባ ክልከላ አድርገውብን ነበር ብለዋል” ፕሬዝዳቱ በመግለጫቸው።

በኋላ ላይ ግን ፕሬዝዳነቱ ወደ ስብሰባው መግታቸው እና በስብሰባው መክፈቻ እንዲሁም የቤተሰብ ፎቶ ላይም ታይተዋል።የሶማሊያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ዛሬ ከሰዓት ላይ በሰጠው መግለጫውም፤ “የኢትዮጵያ መንግስት የሶማሊያ ፕሬዝዳንት እና ልኡካቸው ወደ 2024 የአፍሪካ መሪዎች ጉባዔ እንዳይገቡ ያደረገውን ሙከራ የሶማሊያ ፌደራላዊ ሪፐብሊክ መንግስ በጽኑ ያወግዛል” ብሏል።የኢትዮጵያ መንግስት ድርጊት የዲፕሎማሲ እና ዓለም አቀፍ ደንብን የሚጥቀስ ነው ያለው የሶማሊያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር፤ የአፍሪካ ኅብረትን የቆየ ባህል የሚቃረን በመሆኑ ህብረቱ ጉዳዩን በገለልተኛ ሆኖ እንደሚረምርም ጠይቋል።

አል ዐይ ኒውስ በጉዳዩ ላይ ከምንግስት ኮሙዩኒኬሽን ባገኘው ምላሽ “የኢትዮጵያ መንግሥት ለአፍሪካ ኅብረት ስብሰባ ለመጡ ሁሉም ሀገራትና መንግስታ መሪዎች ያደረገውን የክብር አቀባበል ለሶማሊያ ፕሬዚዳንት ማድረጉን አስታውቋል።እንደ አስተናጋጅ ሀገር ኢትዮጵያ የሁሉንም ሀገራትና መንግስታት መሪዎችን በቆይታው ደህንነታውን የመጠበቅ ኃላፊነት እንዳለበትም አስታውቋል።ነገር ግን የሶማሊያ ፕሬዝዳት ልኡካን በመንግሥት የተመደቡላቸውን የፀጥታ አካላት አንቀበልም ማለታቸውን ነው አል ዐይን ኒውስ ከመንግስት ኮሙዩኒኬሽን አገልግሎት ያገኘው መግለጫ ያመለክታል።

ከዚህ በላይ ግን የሶማሊያ ልዑክ የደህንነት አባላት የጦር መሳሪያ ታጥቀው ወደ አፍሪካ ኅብረት ለመግባት ሲሞክሩ በኅብረቱ የፀጥታ አካላት መከልከላቸውን ገልጿል።በዚህም የኢትዮጵያ መንግሥት የሶማያው ፕሬዝዳንት እና የልኡካቸውን ደህንነት ከመጠበቅ ባሻገር በስብሰባው ላይ እንዳይገኙ እንዳላደናቀፈ እንዲሁም ወደ ኅብረቱ ቅጥር ጊዜ እንዳይገቡ እንዳልከለከለ አሳውቋል።ኢትዮጵያ ከጎረቤቶቿ ጋር መልካም ግንኙነት ለመፍጠር ቁርጠኛ አቋም እንዳላትም ነው የመንስት ኮሙዩኒኬሽን መግለጫ የሚያመላክተው።

ኢትዮጵያ እና ሶማሊላንድ ባለው የፈረንጆቹ ጥር አንድ ቀን በፈረሙት የመግባቢያ ሰነድ ምክንያት ቁጣቸውን ያሰሙት የሶማሊያው ፕሬዝደንት ሀሰን ሸክ መሀመድ ትናንት አዲስ አበባ መግታቸው ይታወሳል።የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ እና የሶማሊላንድ ፕሬዝደንት ሙሴ ቢሄ አብዲ የፈረሙት የመግባቢያ ሰነድ፣ ኢትዮጵያ ለሶማሊላንድ የሀገርነት እውቅና ሰጥታ በምላሹ 20 ኪሎሜትር ርዝመት ያለው የባህር ጠረፍ በ50 አመት የሊዝ ኪራይ እንድታገኝ የሚያስችል መሆኑ በወቅቱ ተገልጾ ነበር።

ሶማሊላንድን የራሷ ሉአላዊ ግዛት አካል አድርጋ የምታያት ሶማሊያ በስምምነቱ ከፍተኛ ቁጣ በማሰማት ከአምባሳደሯን ከኢትዮጵያ መጥራቷም አይታወሳል።ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ በቅርቡ በህዝብ ተወካዮች ምክርቤት በቀረቡበት ወቅት ኢትዮጵያ ከሶማሊያ ጋር ግጭት ውስጥ የመግባት ፍላጎት የላትም ብለዋል።

@Esat_tv1
@Esat_tv1

1 month, 2 weeks ago

የመውጫ ፈተና ከየካቲት 6 እስከ የካቲት 11 ቀን 2016 ድረስ ይሰጣል‼️

የ2016 ዓ/ም የአመቱ አጋማሽ የሀገር አቀፍ የመውጫ ፈተና ከነገ ረቡዕ የካቲት 6 ጀምሮ መሰጠት ይጀምራል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ፤ ዩኒቨርሲቲዎች ከትምህርት ሚኒስቴር ተልኮልናል ብለው ያጋሩትን የተሻሻለ የፈተና መርሃ ግብር የተመለከተ ሲሆን በዚህ መርሀ ግብር ሀገር አቀፉ የመውጫ ፈተና እስካ የካቲት 11 /2016 ዓ/ም ድረስ ይሰጣል።

በፈተናው የመጀመሪያ ቀን በሺዎች የሚቆጠሩ የጤና ተማሪዎች ለፈተና ይቀመጣሉ ተብሎ ይጠበቃል።

ዩኒቨርሲቲዎች ከትምህርት ሚኒስቴር ተላከልን ብለው አጋርተውት በተመለከትነው ዳታ ከ6 ሺህ በላይ የነርሲንግ፣ ከ1 ሺህ 900 በላይ የፋርማሲ፣ ከ1 ሺህ 700 በላይ የዶክተር ኦፍ ሜዲስን ተማሪዎች በመጀመሪያው ቀን ፈተናቸውን ከሚወስዱት ውስጥና ከፍተኛውን ቁጥር ከሚይዙት የጤና ትምህርት ዘርፍ ውስጥ ይገኙበታል።

ከዚህ ባለፈ በዘንድሮው የመውጫ ፈተና ከፍተኛ ተፈታኝ ከሚጠበቅባቸው የትምህርት ክፍሎች መካከል አካውንቲንግ ከ8 ሺህ በላይ፣ ኮምፒዩተር ሳይንስ ከ3 ሺህ በላይ ፣ ማርኬቲንግ ማኔጅመንት ከ2 ሺህ በላይ ተማሪዎች በዋነኝነት ይጠቀሳሉ።

በአመቱ አጋማሽ የሚሰጠውን የመውጫ ፈተና በአጠቃላይ በሺዎች የማቆጠሩ የመጀመሪያ ዙር እንዲሁም ባለፈው ፈተና ውጤት ሳያመጡ የቀሩ የድጋሜ ተፈታኞች የሚወስዱ ይሆናል።

እንደ ትምህርት ሚኒስቴር መረጃ ፤ በአጠቃላይ ፈተናው 47 የመንግስት ተቋማት በ84 የፈተና ማዕከላት የሚሰጥ ሲሆን በመንግስትና ግል ተቋማት ለመጀመሪያ ጊዜ የሚፈተኑትን ጨምሮ 149,145  ተፈታኞች በ204 የፈተና ፕሮግራሞች ይፈተናሉ።

በሌላ ለኩል ከጥቂት ቀናት በፊት ፤ " በኦንላይን ለሚሰጥ የአንድ ቀን ፈተና በመቶዎች ኪሎ ሜትር ተጉዘን እንድንፈተን ተነገረን " በሚል ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ቅሬታቸውን ያሰሙ ተመራቂዎች አሁን ላይ ፈተናውን ባሉበት ከተማ በተቋማቸው እንዲወስዱ ማስተካከያ መደረጉንና ስም ዝርዝራቸውም መውጣቱን ገልጸዋል።

ትምህርት ሚኒስቴር በሀገሪቱ የትምህርት ጥራትን ለማስጠበቅ በሚል ከባለፈው አመት ጀምሮ የተመራቂ ተማሪዎች የመውጫ ፈተና ተግባራዊ እያደረገ ሲሆን ፈተናው በዓመት ሁለት ጊዜ (በአመቱ መጨረሻና አጋማሽ) ላይ ይሰጣል።

(ከላይ ዩኒቨርሲቲዎች ከትምህርት ሚኒስቴር እንደተላከላቸው የገለፁትን የ2016 የአመቱ አጋማሽ ተሻሻለ የፈተና መርሀ ግብርን አይዘናል)

@Esat_tv1
@Esat_tv1

1 month, 2 weeks ago
ESAT (ኢሳት🇪🇹)✅®
1 month, 2 weeks ago
ESAT (ኢሳት🇪🇹)✅®
1 month, 3 weeks ago

በአማራ ክልል ያሉ "ኃይሎች" መሳሪያ የሚያስቀምጡ ከሆነ መንግስት ውይይት ለማድረግ ፈቃደኛ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ተናግረዋል ‼️

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይህን ያሉት በዛሬው እለት በህዝብ ተወካዮች ምክርቤት ቀርበው በሀገሪቱ የሰላም ጸጥታ ጉዳይ ማብራሪ በሰጡት ወቅት ነው።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ መንግስት ለታጣቂ ኃይሎቹ የሰላም ጥሪ ማድረጉን እና በጥሪው መሰረት ከጫካ የተመለሱ መኖራቸውን ገልጸዋል።በክልሉ፣ መንግስት ጽንፈኛ በሚላቸው የፋኖ ታጣቂዎች እና በመንግስት የጸጥታ ኃይሎች መካከል ግጭት የተቀሰቀሰው ባለፈው ሚያዚያ ወር ነበር።

ጠቅላይ ሚኒስተር ዐቢይ ከአማራ ክልሉ ግጭት ጋር በተያያዘ ለተነሳላቸው ጥያቄ መንግስታቸው በክልሉ ህዝብ ለሚነሱ የልማት፣ የይገባኛል ጥያቄዎች እና የህገመንግስት ማሻሻያ ጥያቄዎች መልስ ለመስጠት ጥረት ማድረጉን ተናግረዋል።ደርግ ወደ ስልጣን ሲመጣ የንጉሱን ህገ መንግስት መቅደዱ እና ኢህአዴግ የደርግን ህገ መንግስት መቅደዱ ትክክለኛ አካሄድ አለመሆኑን የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከመንግስት ጋር የማይቀየር ህገመንግስት እንዲኖር እንደሚደረግ እና በዚህም የአማራ ክልል ጥያቄ እንደሚመለስ ተናግረዋል።

በክልሉ ስለሚነሱት የይገባኛል ጥያቄዎች በተመለከተ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ህዝበ ውሳኔ ተደርጎ ህዝቡ ወደፈለገበት እንዲተዳደር ይደረጋል ብለዋል።ችግሩን በሰላማዊ መንገድ እና በውይይት ካልተፈታ ለአማራም ሆነ ለትግራይ የማይጠቅም እና ዘላቂ መፍትሄ የማያመጣ ነው ብለዋል። መንግስት ካቀረበው የህዝበ ውሳኔ ውጭ ሌላ መፍትሄ ሁለቱ ወገኖች ተመካክረው የሚያመጡ ከሆነ መንግስት ለመቀበል ዝግጁ መሆኑን ተናግረዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ መንግስት ከሸኔ ጋር ያደረገውን ድርድር ግልጽ አላደረገም በሚል የተነሳባቸውንም ትችት አጣጥለውታል።

ኦነግ ከኤርትራ ወደ ሀገር ሲገባ ምን ቃል ተገብቶለት ነው?፤ ምን ስላልተፈጸመለት ነው ችግር የፈጠረው የሚሉ ጥያቄዎች ይነሳሉ ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ኦነግ እንደማንኛውም አማጺ በይፋ ጥሪ ተደርጎለት ነው የገባው ሲሉ ተናግረዋል። ኦነግን ብቻ የተለየ አድርጎ ማንሳት እና ነገሩን በሴራ ማየት ተገቢ አይደለም፣ ከኦነግ ሽኔ ጋር በታንዛኒያ የተደረገው ድርድር ይህ ነው የሚባል ውጤት ስላላስገኘልን ለህዝብ ይህን አሳካን ማለት አልቻልንም ብለዋል።

ኦነግ ሸኔ "ወደፊት አደብ ገዝቶ ወደ ሰላም ከመጣ ለህዝብ እናሳውቃለን"።ጠቅላይ ዐቢይ እክለውም ኦነግ በአስመራ በተደረገ ስምምነት ቃል የተገባለት ነገር ሳይፈጸምለት ቀርቶ ወይም ለህዝብ ተጨንቆ ከሆነ እታገልለታለሁ የሚለውን የኦሮሞ ህዝብ በመዝረፍ እና በማገት ተግባር አይሰማራም ነበር ብለዋል።ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ የኦነግ ሸኔ ተግባር ለኦሮሞ ህዝብ ስለማይጠቅም ወደ ሰላም እንዲመጣ አሳስበዋል።

በሰሜን ኢትዮጵያ የተቀሰቀሰውን ግጭት የቋጨው የፕሪቶሪያው ስምምነት ከተፈረመ በኋላ የፌደራል መንግስት እና የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር በጋራ በመሆን ድሎች ማስመዝገባቸውን ገልጸዋል።

ባንኮች በ10ቢሊዮን ተንቀሳቃሽ ገንዘብ ስራ መጀመራቸው፣ በክልሉ ያሉ አየር መንገዶች ስራ መጀመራቸው፣ የ4ጂ የቴሌ ኔትወርክ አገልግሎት መጀመሩ፣ የኢንዱስትሪዎች ስራ መጀመር እና ሌሎች ጠቅላይ ሚኒስትሩ በስኬት ያነሷቸው ተግባራት ናቸው።ነገርግን ይህ በቂ አለመሆኑን እና የሚቀሩ ስራዎች መኖራቸውን ጠቅላይ ሚኒስትሩ ተናግረዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ እስር በዛ በሚል ከምክር ቤት አባላት ለተነሳላቸው ጥያቄ እያታየ ካለው አናርኪ ወይም ህገወጥነት አንጻር በዝቷል ማለት እንደማይቻል ተናግረዋል።"መታሰር የሚገባቸው ሰዎች በየቀኑ እየታለፉ ነው" ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ እየታየ እንዳለው ሁኔታ ቢሆን ፖርክ ሳይሆን እስርቤት ነበር የምንገነባው ብለዋል። ከአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ጋር በተያያዘ የታሰሩ በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች መለቀቃቸውን እና አሁን የቀሩት በ100 የሚቆጠሩ ናቸው ብለዋል።  የቀሩትም ቢሆን አስቸኳይ ጊዜ አዋጅ እዙ እየያ እንደሚፈታቸው ተናግረዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ መንግስት እንከን የለሽ እንዳልሆነ እና በመንግስት ውስጥ ያለ ወታደር፣ ፖሊስ ወይም ካድሬ ቁጥሩ ይነስ እንጁ ህዝብ የሚበድል አለ ብለዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ መንግስት ይህን ችግር ለመፍታት የማጥራት ስራ እንደሚሰራ ገልጸዋል።

@Esat_tv1
@Esat_tv1

1 month, 3 weeks ago
ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና …

ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ ወደ ሀገር እንዳይገቡ ተከለከሉ‼️

ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ እና የኒውዮርክና አካባቢው ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በአሜሪካ የነበራቸውን ሐዋርያዊ አገልግሎት ጨርሰው ቦሌ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ ሲደርሱ እንዳይገቡ መከልከላቸው ተሰምቷል።

ብፁዕነታቸው ከሳምንታት በፊት በቋሚ ሲኖዶስ እውቅና ወደ ሀገረ ስብከታቸው በመሄድ የአጋእዝተ ዓለም ሥላሴ ዓመታዊ በዓል፣ የከተራና የጥምቀት በዓላትን ከመንፈስ ልጆቻቸው ጋር ያከበሩ ሲሆን ለአዳጊ ሕጻናትም ማዕረገ ዲቁና መስጠታቸው ይታወቃል።

ብፁዕነታቸው በአሁኑ ሰዓት ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያው ይገኛሉ ሲሉ መረጃ ሰጭዎቻችን አድርሰውናል ሲል ማኅበረ ቅዱሳን ቴቪ አስታውቋል።

@Esat_tv1
@Esat_tv1

1 month, 3 weeks ago
የፌዴራል መንግስት እና የትግራይ ክልል ጊዜያዊ …

የፌዴራል መንግስት እና የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር በትብብር ትላልቅ ድሎችን አስመዝግበዋል‼️

🗣ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

በፕሪቶሪያ ከተደረሰው የሰላም ስምምነት በኋላ፤ የፌዴራል መንግስት እና የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር በትብብር ትላልቅ ድሎችን ማስመዝገብ ችለዋል ሲሉ የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ።

6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 3ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 14ኛ መደበኛ ስብሰባ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ በተገኙበት እየተካሄደ ይገኛል።

በስብሰባው ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከምክር ቤቱ አባላት ለተነሱላቸው ጥያቄዎች እና አስተያየቶች ምላሽ እና ማብራሪያ እየሰጡ ነው።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በሰጡት ምላሽና ማብራሪያ፤ በፕሪቶሪያ ከተደረሰው የሰላም ስምምነት በኋላ የተገኙት ድሎች የፌድራል መንግስቱ ለብቻው ያመጣቸው እንዳልሆኑ ገልጸው፤ ከትግራይ ክልል ጊዜያው አስተዳደር ጋር ተዳምረው የተገኙ አሙርቂ ውጤቶች ስለመሆናቸው ነው የተናገሩት።

የተገኘው ሰላም ካመጣቸው ድሎች ውስጥ የአየር ትራንስፓርት ወደ ትግራይ ክልል መጀመሩ አንዱ መሆኑን ጠቅሰው፤ ለብዙዎች እፎይታ የሰጠ መሆኑንም አንስተዋል።

በክልሉ የስልክ እና የኤሌክትሪክ አገልግሎት መጀመሩን ገልጸው፤ በፌዴራል መንግስት እና በክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር ትብብር የትግራይ ህዝብ አገልግሎቶቹን እንዲያገኝ መደረጉን አብራርተዋል።

@Esat_tv1
@Esat_tv1

1 month, 4 weeks ago
ESAT (ኢሳት🇪🇹)✅®
We recommend to visit

ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ

Last updated 1 month ago

እንኳን ደህና መጡ‼

✔ማስታወቂያ ለማሰራት እና ጥቆማ ለመስጠት በዚህ ይጠቀሙ ☞https://t.me/WasuMohammed

✔ ቻናሉን ለመቀላቀል Join ☞http://t.me/Wasulife

ከልብ አመሰግናለሁ♥🙏

Last updated 1 month, 1 week ago

Last updated 1 month ago