Dive into the Ultimate Free Library: Your One-Stop Hub for Entertainment!

TIKVAH-ETHIOPIA

Description
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
We recommend to visit

ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ

Last updated 3 days, 15 hours ago

ለማንኛውም አስተያየት እና ጥቆማ 👉 @Esat_tv_comment_bot

🇪🇹ኢሳት የኢትዮጵያ አይን እና ጆሮ🇪🇹

Last updated 6 days, 1 hour ago

Last updated 2 months ago

4 days, 15 hours ago

በአዲስ አበባ ከተማ የ2ኛው ዙር የመሬት ሊዝ ጨረታ

የመሬት ልማትና አስተዳደር ቢሮ በአራዳ ክ/ ከተማ (ፒያሳ) በዓድዋ ድል መታሰቢያ አካባቢ በኮሪደር ልማት ምክንያት የፀዱ ቦታዎችን ጨምሮ ፦
- በንፋስ ስልክ ላፍቶ፣
- በኮልፌ ቀራንዮ፣
- በአራዳ፣
- በአቃቂ ቃሊቲ፣
- በየካ፣
- በቦሌ፣
- በአዲስ ከተማ፣
- በቂርቆስ፣
- በጉለሌ
- በልደታ ክፍለ ከተሞች የሚገኙ ለተለያዩ አገልግሎቶች የተዘጋጁ የልማት ቦታዎችን በጨረታ አወዳድሮ በሊዝ ማስተላለፍ እንደሚፈልግ አሳውቋል።

(ዝርዝር የጨረታው መረጃ በPDF ተያይዟል - ይመልከቱ)

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ይህ የጨረታ መረጃ ባለቤት አዲስ ልሳን መሆኑን ያሳውቃል።

#TikvahFamilyAddisAbaba

@tikvahethiopia

4 days, 17 hours ago
TIKVAH-ETHIOPIA
4 days, 17 hours ago
[#ሊዝ](?q=%23%E1%88%8A%E1%8B%9D) [#አዲስአበባ](?q=%23%E1%8A%A0%E1%8B%B2%E1%88%B5%E1%8A%A0%E1%89%A0%E1%89%A3)

#ሊዝ #አዲስአበባ

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመሬት ልማትና አስተዳደር ቢሮ መሬትን በሊዝ ለማስተላለፍ 2ኛ ዙር ጨረታ አውጥቷል።

መሬትን በሊዝ የማስተላለፍ ተግባር ለአራት ዓመታት ከተቋረጠ በኋላ ግንቦት 5 ቀን 2015 ዓ.ም መጀመሩ ይታወሳል፡፡

2ኛው ዙር የመሬት ሊዝ ጨረታም ረቡዕ ሚያዝያ 9 ቀን 2016 ዓ.ም መውጣቱን ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከቢሮና ከአዲስ ልሳን ጋዜጣ መረጃውን አግኝቷል።

በከተማዋ መሬት ልማትና አስተዳደር ቢሮ መረጃ መሠረት፣ በ2ኛው ዙር ጨረታ 243 መሬት (ቦታ) የተዘጋጀ ሲሆን፣ እነዚህ ቦታዎችም በአስር ክፍለ ከተሞች የሚገኙ ናቸው፡፡

በአራዳ ክ/ከተማ (ፒያሳ) በዓድዋ ድል መታሰቢያ አካባቢ በኮሪደር ልማት ምክንያት የፀዱ ቦታዎችን ጨምሮ ፦
- በንፋስ ስልክ ላፍቶ፣
- በኮልፌ ቀራንዮ፣
- በአራዳ፣
- በአቃቂ ቃሊቲ፣
- በየካ፣
- በቦሌ፣
- በአዲስ ከተማ፣
- በቂርቆስ፣
- በጉለሌ እና በልደታ ክፍለ ከተሞች የሚገኙ ለተለያዩ አገልግሎቶች የተዘጋጁ የልማት ቦታዎች በ2ኛው ዙር ጨረታ በሊዝ ሊተላለፉ እንደቀረቡ ታውቋል።

ከዚህ ቀደም አልሚዎች ተጫርተው አሸናፊ ከሆኑ በኋላ በሚተላለፉ የተለያዩ ቦታዎች ላይ “የይገባኛል” ጥያቄዎች ይነሱባቸው እንደነበር ነበር።

አሁን ለመተላለፍ የተዘጋጁ ቦታዎች ግን ከሶስተኛ ወገን ጥያቄ ነፃ መሆናቸውን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመሬት ልማትና አስተዳደር ቢሮ ገልጿል።

ተጫራቾች የጨረታ ሰነዳቸውን ሚያዝያ 22 ቀን 2016 ዓ.ም ከቀኑ 11፡30 ሰዓት ድረስ ለም ሆቴል አካባቢ ኤም.ኤ (MA) ህንፃ ላይ በሚገኘው በከተማዋ መሬት ልማትና አስተዳደር ቢሮ ለዚህ በተዘጋጀ የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት እንዳለባቸው ተመላክቷል፡፡

ጨረታው ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ሚያዝያ 24 ቀን 2016 ዓ.ም ከጠዋቱ 3፡ዐዐ ሰዓት ጀምሮ በ9 ተከታታይ የስራ ቀናት በቦሌ ክፍለ ከተማ አስተዳደር አዳራሽ የሚከፈት ሆኖ፣ ዝርዝሩ በውስጥ ማስታወቂያ ይገለፃል ተብሏል፡፡

ተጫራቾች ቦታውን በአካል ቀርበው ለመመልከት ከፈለጉ በ16/8/16 ዓ.ም እና በ18/8/16 ዓ.ም ከጠዋቱ በ3፡00 እና ከሰዓት በ8 ሰዓት ለጨረታ የተዘጋጁ ቦታዎች የሚገኙበት ከፍለ ከተማ የመሬት ልማትና አስተዳደር ጽህፈት ቤት ድረስ በመቅረብ ለዚህ ስራ በሚመደቡ አስጎብኚዎች አማካኝነት መመልከት እንደሚችሉ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከአዲስ አበባ የመሬት ልማትና አስተዳደር ቢሮና / ከአዲስ ልሳን ጋዜጣ ያገኘው መረጃ ያመለክታል።

ዝርዝር የጨረታውን መረጃ ከታች (በቀጣይ ፖስት) እናያይዛለን።

@tikvahethiopia

2 months ago
[#BDU](?q=%23BDU)

#BDU

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ፤ እስካሁን ጥሪ ባልተደረገላቸው የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ጉዳይ ላይ ከተቋሙ ተጨማሪ ምላሽ አግኝቷል።

በዚህም ተቋሙ ፤ " ተማሪዎቹን ለመጥራት አስቻይ ሁኔታዎች እየተጠበቀ ነው። " ብሏል።

" አሁን ያለው ሁኔታ ተማሪዎቹን ለመጥራት እየተገመገመ ነው። ተማሪዎቹ በትዕግስት ይጠብቁ። " ሲል አሳውቋል።

ተጨማሪ ዝርዝር የምናጋራችሉ ይሆናል።

@tikvahuniversity @tikvahethiopia

2 months ago
TIKVAH-ETHIOPIA
2 months ago
" ዩኒቨርሲቲው የሚጠራም ከሆነ የማይጠራም ከሆነ …

" ዩኒቨርሲቲው የሚጠራም ከሆነ የማይጠራም ከሆነ አቋሙን ያሳወቀን " - ተማሪዎች

የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ለ2016 ዓ/ም አዲስ ገቢ ተማሪዎች ጥር 21 ቀን 2016 ዓ/ም ያደረገውን ጥሪ ባላወቁት ምክንያት አራዝሞት እንደነበር፣ ይሁን እንጂ ከዚያ ወዲህም “ ኑም ” ሆነ “ አትምጡ ” ባለማለቱና የትምህርት ጊዜው እያገፋ በመሆኑ ጭንቀት ውስጥ መሆናቸው ውሳኔውን እንዲያሳውቃቸው ተማሪዎቹ ዩኒቨርሲቲው ይጠየቅልን ሲሉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።

አንድ ተማሪ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጠው ቃል፣ “ዩኒቨርሲቲው የሚጠራም ከሆነ የማይጠራ አቋሙን ያሳወቀን” ብሏል።

ተማሪዎቹን ወክሎ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ማብራሪያ የሰጠ ሌለኛው ተማሪ ፤ “ እኛ የ2016 ዓ/ም ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የተመደብን Freshman እና Remedial ተማሪዎች ነን። ነገር ግን አስካሁን ከሌሎች የአማራ ክልል በተለዬ የእኛ ካምፓስ ለተማሪዎቹ ጥሪ አላደረገም ” ሲሉ አማሯል።

ዩኒቨርሲቲው ጥር 21 ቀን 2016 ዓ/ም ጥሪ አድርጎላቸው እንደነበር ያስታወሰው የሁሉንም ተማሪዎች ቅሬታ አቅራቢው፣ “ ባልታወቀ ምክንያት ላልተወሰነ ጊዜ እንደተራዘመ ከተነገረን ወር ሊሞላን ነው ” ብሏል።

በመሆኑም፣ መጥራት የሚችሉ ከሆነ ጥሪ እንዲያደርጉ፣ መጥራት የማይችሉ ከሆነ ደግሞ ተማሪዎቹ በመጠበቅ ጊዜያቸውን እንዳያባክኑ እንዲያሳውቁ፣ እንዲሁም በቅርቡ መቅደላአምባ ዩኒቨርሲቲ እንዳደረገው ከአቅም በላይ የሆነ ችግር ካለ ዩኒቨርሲቲው ወደ ሌሎች ዩኒቨርሲቲዎች እንዲመድባቸው ጠይቋል።

“ ከእነዚህ አማራጮች ውጪ ግን ‘ተማሪዎች ጠብቁ’ የሚል መልስ መስጠት እንደማይቻል ይታወቅልን። ምክንያቱም ከዚህ በላይ ትዕግስት ሊኖረን ስለሚይችል። በዕድሜያችንና በሞራላችን እየተቀለደ ነው ያለው ” ሲልም የተማሪዎቹ ተወካይ አሳስቧል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ያነጋገራቸው አንድ የዩኒቨርሲቲው አካል በሰጡት ቃል፣ “ ዩኒቨርስቲው አሁን አልጠራም ማለትም አይችልም (ምክንያቱም አልጠራም ቢል ከትምህርት ሚኒስቴር ግዳጅ አለበት)። ጠርቶ እንዳያስገባ ደግሞ አካባቢው ላይ እየተንቀሳቀሱ ያሉ ኃይሎች እያደረጉ ያሉትን ነገር በዓይናችን እያዬን ነው ” ሲሉ ተማሪዎቹ ዩኒቨርሲቲው አሁንም ይታገሱ እንዲላቸው ሳይሆን ቁርጡን እንዲያሳውቃቸው ላቀረቡት ጥያቄ ምላሽ ሰጥተዋል።

“ ዩኒቨርሲቲው የማይጠራበትን ምክንያት፣ አሁን አካባቢው ላይ ያለው ነገር ጥሩ ስላልሆነ ነው። በጸጥታ ችግር ከጤና እና ከአግሪካልቸር ግቢዎች ለቀው ወደ ፔዳና ፖሊ ካምፓሶች የተደረቡ ተማሪዎች Still ትምህርት አልጀመሩም። አሁን አዲስ ተማሪዎችን ቢጠራ የት ላይ ነው የሚያደርጋቸው? ” ሲሉም ጠይዋል።

“ ማስተባበሪያ ክላስ ራሱ ጠቦን እየተቸገርን ነው። የዶርም እጥረት አለ። ተማሪዎቹ ወደዬ ግቢያቸው እስካልተመለሱ ድረስ” ያሉት እኚሁ አካል ፣ “አሁንም ፔዳ (Main campus) ያለው ሁኔታ አስጊ ነው። ‘እስከ ነገ ሐሙስ ‘ለቃችሁ ውጡ’ የሚል ወሬ ስለመጣ ዩኒቨርሲቲው አዲስ ተማሪዎችን መጥራት አይችልም። የመጡት እየተሰቃዩ ነው። እነዚህም መጥተው ከሚሰቃዩ ቢረጋጉ ነው የሚሻላቸው ” ሲሉ አሳስበዋል።

ዘገባውን የላከው የአ/አ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል ነው።

@tikvahethiopia

4 months, 2 weeks ago
TIKVAH-ETHIOPIA
4 months, 2 weeks ago
" ማንኛውም ግለሰብ እኔ ከልጆቼና ከቤተሰቦቼ …

" ማንኛውም ግለሰብ እኔ ከልጆቼና ከቤተሰቦቼ ጋር እራሴ አወርዳለሁ ካለ #አይገደድም " - የአ/አ ሰላምና ፀጥታ አስተዳደር

በአዲስ አበባ የጋራ መኖሪያ ቤቶች፣ የማህበር ቤቶች፣ ሪል ስቴት ያሉባቸው አካባቢዎች ላይ ጫኝ እና አውራጆች በሚጠይቁት ያልተመጣጠነ ክፍያና በሚፈጥሩት ግብግብ በርካቶች እንደሚማረሩ ይታወቃል።

" እቃዬን እኔ እራሴ አወርዳለሁ " ሲባልም አንዳንድ ጫኝ እና አውራጆች ከአፃያፊ ቃላት ውርወራ ጀምሮ ለግብግብ እና ፀብ እስከማጋበዝም ይደርሳሉ።

" መንግስት እስካደራጀን ድረስ ባለቤቱ ፈለገም አልፈለገም እቃውን የምናወርደው እኛ ነን " እስከማለትም ይደርሳሉ።

አንዳንዴም እቃዎች እንዲጎዱ ፣ እነሱ ካላወረዱት እዛ አካባቢ ላይ በነፃነት ለመንቀሳቀስ ስጋት እንስከመሆንም ይደርሳል።

በዚህ ላይ ያለውን ዘርፈ ብዙ ችግር ይቀርፋል፣ ነዋሪዎችንም ከምሬት እና እንግልት ያታደጋል የተባለው መመሪያ ማንኛውም ህገወጥና ነዋሪዎችን የሚያማርሩ ተግባራትን ይከለክላል።

" ግለሰቡ እኔ ከልጆቼ፣ ከቤተሰቤ ጋር ሆኜ አወርዳለሁ ካለ አይገደድም ፤ እራሱ ማውረድ ይችላል። ማህበራቱም እኛ ነን የተደራጀነው ማስወረድ አትችሉም ማለት አይችሉም " ሲሉ አቶ ማስረሻ ሃብቴ የአዲስ አበባ ሰላምና ፀጥታ ቢሮ አማካሪ ተናግረዋል።

የባለቤቱን መብት መጠበቅ የማህበራቱ ግዴታ እንዳሆነ ገልጸዋል።

በስምምነት  እቃው የሚወርድ ከሆነ ደግሞ ጫኝ እና አውራጅ ማህበሩ ሙሉ ኃላፊነት ለእቃው ይወስዳል ብለዋል።

አቅምን ያላገናዘበ ፣ ከእቃው ጋር ያልተመጣጠነ ክፍያም እንዳይኖር የዋጋ ተመን መውጣቱን አቶ ማስረሻ ገልጸዋል።

" ለእያንዳንዱ እቃ ዋጋ ተቀምጦለታል "  ያሉት አቶ ማስረሻ " የራሱ የሆነ ርቀት አለው ለምሳሌ ከተሽከርካሪ ከወረደበት 50 ሜትር የመጀመሪያ ዋጋ አለ ከዛ በኃላ እያጨመረ ይሄዳል። ኮንዶሚየም ላይ የሚወጣ ከሆነ እስከ ብሎክ ስር 50 ሜትር ከሆነ ከታች ወደላይ ዋጋው እያጨመረ ይሄዳል።  " ብለዋል።

ቢሮው ተግባራዊ ስለተደረገው መመሪያ በጫኝ እና አውራጅ ዘርፍ ላይ ለተሰማሩ ወጣቶች እና ማህበራት የ2 ቀን የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና መስጠት መጀመሩን ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከአዲስ ሚዲያ ኔትዎርክ ያገኘው መረጃ ያሳያል።

@tikvahethiopia

4 months, 2 weeks ago
TIKVAH-ETHIOPIA
4 months, 3 weeks ago
TIKVAH-ETHIOPIA
We recommend to visit

ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ

Last updated 3 days, 15 hours ago

ለማንኛውም አስተያየት እና ጥቆማ 👉 @Esat_tv_comment_bot

🇪🇹ኢሳት የኢትዮጵያ አይን እና ጆሮ🇪🇹

Last updated 6 days, 1 hour ago

Last updated 2 months ago