Dive into the Ultimate Free Library: Your One-Stop Hub for Entertainment!

️ ንስር አማራ🦅

Description
የተቀደሰን ነገር በእግሩ ለሚረግጥ ፥ ተመልሶም ያጎረሰውን እጅ ለሚናከስ ርኩስ መጫወቻ የማይሆን የነቃ ማህበረሰብ እስክንፈጥር ድረስ ብዕራችን አይነጥፍም።

አንድ አማራ ለሁሉም አማራ ፥ ሁሉም አማራ ለአንድ አማራ።
💚💛❤️

እኛን በውስጥ ለማናገር @NISIREamhraa_bot 👈 ይችን አድራሻ ይጠቀሙ🦅

ንስር አማራ🦅
#የግፉአን_ድምፅ
t.me/NISIREamhra
Advertising
We recommend to visit

ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ

Last updated 5 days, 4 hours ago

Last updated 3 weeks, 1 day ago

በዚህ ቻናል ወቅታዊ፣ታማኝ እና ፈጣን መረጃ ያገኛሉ❗
መረጃ ለማድረስ እና ማስታወቂያ ለማሰራት ከስር ባለው ሊንክ ይጻፉልን👉http://t.me/ayulaw

Last updated 1 month, 3 weeks ago

1 day, 23 hours ago
2 days ago

🔥#መረጃ_ጎንደር...‼️

በጎንደር #አለፋ ወረዳ ጨፍጫፊው እና ህፃን ደፋሪው የኦነግ ብልፅግና መከላከያ እና የባንዳ ስብስብ ዋጋውን አግኝቷል:: በሳንቃበር እና ሻውራ ጨምሮ በተደረጉ ኦፕሬሽኖች እና እልህ አስጨራሽ ውጊያዎች የብልፅግና አራዊት በአማራ ፋኖ በጎንደር ዓድዋ ክፍለጦር አናብስት ሙትና ቁስለኛ ተደርጏል::

በተመሳሳይ #በአርማጭሆ፣ በመተማ እና በወገራ ኦነግ ብልፅግና ጨፍጫፊ እና ህፃን ደፋሪ ቡድን በጎቤ ክፍለጦር እና የጎንደሬ በጋሻው ክፍለጦር ጨምሮ በአማራ ፋኖ ጎንደር ዕዝ የፋኖ ነበልባሎች ሲለበለብ ቆይቷል::

በጎንደር #ታች_ጋይንት ፋኖ ላይ ከበባ አደርጋለሁ ብሎ የገባው የኦነግ ብልፅግና አራዊት እስከ ባንዳ አድማ ብተና እና ሚሊሻ በገፍ የታጨደ ሲሆን በቀጠለው ውጊያ በአማራ ፋኖ በጎንደር ገብርዬ ክፍለጦር ነበልባሎች ጠላትን ውሀ ውሀ እያሰኙት ይገኛሉ::

በአውደ ውጊያ ማሸነፍ የማይችለው የኦሮሙማው መንጋ በተለያዩ አካባቢዎች ንፁሃን አማራዎች ላይ ድብደባ፣ ግድያ እና ስርቆት ፈፅሟል::

#ድል_ለአማራ_ህዝብ💪
#ድል_ለክንደነበልባሉ_ፋኖ💪

11/09/16 ዓ.ም

@NISIREamhra

2 days, 6 hours ago

🔥#ስማዳ_ጎንደር‼️

ስማዳ ወረዳ የሚንቀሳቀሰው ሀገረቢዘን ብርጌድ በ9/09/2016 ባደረገው አስደማሚ ኦፕሬሽን በጀግናው የአማራ ፋኖ የተመቱት ሆዳሙ ሚኒሻ ህክምና ላይ እንደሆኑ እና ኦክስጅን እንደተተከለላቼው በትናት ዘገባችን መረጃውን ማድረሳችን ይታወቃል። ከታካሚዎች መካከል ትናት አመሻሽ 11:30 አካባቢ መዝገቡ የተባለ ሚኒሻ በባንዳነት ሲያገለግል ኖሮ ሞቷል። ነበልባሉ ፋኖ እና ህዝቡ አማራነቱን ሽጧል እና መቀበር የለበትም በማለት ጂብየ ኪዳነምህረት ቤተክርስቲያን ሻለቃ 01 ሲሳይነው ሻለቃ አስከሬን ለማጀብ የመጣው የብርሀኑን ጁላ ጦር በመመለስ ሌሎች ሻለቃ 02 ( አይበገሬዉ) እና ሻለቃ 03 ( ዦጋ ሻለቃ) በአሁኑ ሰዓት ወገዳ ከተማ ውስጥ በመግባት በተለያዩ ግንባሮች የጨበጣ ዉጊያ እየተካሄደ ይገኛል። መጨረሻላይ የሞተ እና የቆሰለ በዝርዝ እምና ቀርብ መሆኑን እንገልፃለን ሲሉ የአማራ ፋኖ በጎንደር ጉና ክፍለ ጦር ሀገረቢዘን ብርጌድ ቃል አቀባይ ፋኖ ደጉ አውለው ለንስር አማራ ገልፀዎል‼️

#ድል_ለአማራ_ፋኖ💪
#ድል_ለአማራ_ህዝብ💪

11/09/16 ዓ.ም

@NISIREamhra

1 week, 2 days ago

🔥የኦነግ ብልፅግና መሪ ከባህርዳር ፈረጠጠ…‼️

ጠቅላይ ሚኒስትሩ የባሕር ዳሩን ፕሮግራም አቋርጠው ወደ መጡበት መመለሳቸው ተሰምቷል።

የአማራ ክልል መዲና በሆነችው ባሕር ዳር ከተማ ቀበሌ 11 ዙሪያ የተገነባው የዓባይ ድልድይ ምርቃ ሥነ ሥርዓት ላይ ከነባለቤታቸውና ከሌሎች ከፍተኛ አመራሮች ጋር የታደሙት በአማራ ህዝብ ላይ ጦርነት ያወጁት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ፡ ፕሮግራሙ ከሚካሄድበት አከባቢ በቅርብ ርቀት ላይ ፋኖ ተደጋጋሚ የሆነ የቦምብ ጥቃት በመፈፀሙ የምረቃ ሥነ ሥርዓቱን አቋርጠው በመጡበት ሄሊኮፍተር ወደ አዲስ አበባ መመለሳቸውን የአማራ ድምፅ ሚድያ የባሕር ዳር ከተማ ቅርንጫፍ ዘጋቢዎች ለማረጋገጥ ችለዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከሰሞኑ የምስራቅ ወለጋ ዋና መቀመጫ በሆነችው ነቀምቴ ከተማ ሄደው በሰላም መመለሳቸው የሚታወቅ ሲሆን ነገር ግን በዛሬው ዕለት የአማራ ክልል ርዕሰ መዲና ባሕር ዳር እንደ ምስራቅ ወለጋዋ ነቀምቴ ከተማ ሳትሆንላቸው ቀርታለች ነው የተባለው።

የዓባይ ድልድይ ምረቃ ሥነ ሥርዓት በሚካሄድበት ቀበሌ 11 ዙሪያ ፋኖ ተደጋጋሚ የሆነ የቦምብ ጥቃት የፈፀመ ሲሆን በዚህም ጠቅላይ ሚኒስትሩና ባለቤታቸው ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው እንዲሁም ሌሎች የፌደራልና የክልሉ ከፍተኛ ባለስልጣናት ተደናግጠው በሁለት ሄሊኮፍተር ተሳፍረው በአፋጣኝ የሰሜን ምዕራብ ዕዝ መቀመጫ ወደ ሆነው መኮድ ካምፕ የሄዱ ቢሆንም፡ ነገር ግን በካምፑ ዙሪያም ተመሣሣይ የሆነ የቦምብ ጥቃት በመፈፀሙ በድጋሚ ሄሊኮፍተሮቻቸውን አስነስተው ወደ አዲስ አበባ መብረራቸውን ነው የአማራ ድምፅ ሚድያ የባሕር ዳር ከተማ ወኪሎች ያረጋገጡት።

ባለስልጣናቱ ተደናግጠው የድልድዩን ምረቃ ሥነ ሥርዓት ሳያጠናቅቁ ወደ መኮድ ካምፕ በሚበሩበት ወቅት፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከነ ባለቤታቸው ተሳፍረውበት የነበረው ሄሊኮፍተር በከፍታ ላይ የበረረ ሲሆን ነገር ግን በቅርቡ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተደርገው የተሾሙት አቶ ተመስገን ጥሩነህን ጨምሮ ሌሎች ባለስልጣናትን የያዘችው ሁለተኛዋ ሄሊኮፍተር ዝቅ ብላ መብረሯን ዘጋቢዎቻችን ለመመልከት ችለዋል።

በከተማዋ ሆምላንድን ጨምሮ ባለስልጣናቱ ተሰባስበው ይገኙባቸዋል በተባሉ በተለያዩ ትላልቅ ሆቴሎች ላይ ከለሊት ጀምሮ  የቦምብ ጥቃት ሲፈፀም ማደሩም ነው የታወቀው።

በዚህም እስካሁን የታወቁ አንድ የባሕር ዳር ከተማ አስተዳደር ከፍተኛ አመራርን ጨምሮ ከሚኒሊክ ክ/ከተማ በቁጥር ሦስት አመራሮች፣ ከፋሲሎ ክ/ከተማ ሁለት፣ ከቴዎድሮስ ክ/ከተማ አንድ አመራር ቆስለው ወደ ፈለገ ህይወት ሆስፒታል መወሰዳቸውንም ነው የአማራ ድምፅ ሚድያ የባሕር ዳር ወኪሎች ያረጋገጡት።

ከዚህ በተጨማሪ፡ የድልድዩ ምረቃ ስነ ስርዓት በተጀመረ በደቂቃዎች ውስጥ በቁጥር ከአምስት በላይ የሚሆኑ ሪፐብሊካን ጋርዶች ከነመሣሪያቸው የተሰወሩ ሲሆን፡ እነሱን ፍለጋ መነሻቸውን ከመኮድ ካምፕ ያደረጉ በርካታ ወታደሮች በከተማዋ መሰማራታቸው ታውቋል።

#ድል_ለአማራ_ፋኖ*💪#ድል_ለአማራ_ህዝብ💪*

04/09/16 ዓ.ም**@NISIREamhra

1 week, 2 days ago

*🔥#ሰከላ‼️*

ነበልባለለ የአማራ ፋኖ በጎጃም ሰከላ ብር አዳማ መሽጎ የሚገኜው የብርሃኑ ጁላ ጦር ከጠዎቱ ጀምሮ እየተለበለበ ሲሆን ነበልባሉ #ምሽጉን በመስበር ብር አዳማን ፋኖ ተቆጣጥሯቷል💪

በተያያዘ መረጃ አበሰከን ላይ ብሬን እና ክላሾች ወደ ፋኖ ገቢ ሆነዎል‼️#ክብር_ለጀግኖቻችን‼️#ድል_ለአማራ_ፋኖ💪#ድል_ለአማራ_ህዝብ💪

04/09/16 ዓ.ም**@NISIREamhra

1 week, 2 days ago

🔥ዘንዶው ከሞርታር አምልጧል…‼️

ወደ ባሕርዳር ከተማ ለዲስኩር የሄደው ዘንዶዉ ከሶስት የሞርታር ጥቃት አምልጧል። ይህንንም ተከትሎ በአዲሱ የአባይ ድልድይ ታስቦ የነበረው ዝግጅት እንዳሰቡት እምብዛም ሳይደሰኩሩ መቋረጡ ታውቋል። ለአገዛዙ ሚዲያዎችም ይህንን ለመሸፋፈን በያዙት የቪዲዮ ማስረጃዎች አማካኝነት እንዲያጫጩሁት መታዘዙ ተሰምቷል።

ዝርዝሩ በአማራ ፋኖ በጎጃም ቃል አቀባይ ፋኖ ማርሸት ፀሀዩ በኩል ይገለፃል!

04/09/16 ዓ.ም@NISIREamhra

2 weeks, 2 days ago
***🔥*****እንኳን ለትንሣኤ በዓል አደረሳችሁ*****‼️*** **“ሕያውን ከሙታን …

🔥እንኳን ለትንሣኤ በዓል አደረሳችሁ‼️ “ሕያውን ከሙታን መካከል ስለ ምን ትፈልጋላችሁ? ተነሥቶአል እንጂ በዚህ የለም።” ሉቃ 24፥5 የሞቀ ቤታችሁን አደብዝዛችሁ፣ ቤተሰባችሁን በትናችሁ፣ ደም እና ላባችሁን በዱር በገደሉ እያፈሰሳችሁ ከፍ ሲልም አጥንታችሁን ከስክሳችሁ ውድ ህይዎታችሁን ሰጥታችሁ የአማራ ህዝብ ብሎም ኢትዬጵያን ከአሸባሪው የብልፅግና አገዛዝ ለማላቀቅ ዱርቤቴ ላላችሁ ወድ የፋኖ አመራር እና አባላቶች ፣ለንስር አማራ ቤተሰቦች እንዲሁም ለመላው የኦርቶዶክስ ዕምነት ተከታዮች በሙሉ  እንኳን ለጌታችንና ለአምላካችን ለመድኃኒታችን እየሱስ ክርስቶስ የትንሣኤው በዓል አደረሳችሁ፣ አደረሰን‼️

የፋኖ አመራር እና አባላቶች በዓሉን ስናከብር ለአሸባሪው የጥቃት ቡድን በማያጋልጥ መልኩ እና በጥንቃቄ እንዲከበር እያሳሰብን ከቤታችን የምናከብር የዕምነቱ ተከታዮች በዓሉን የፋኖ ቤተሰቦችን እና አቅመ ደካሞችን ያለንን በማካፈል በዓሉን በአንድነት፣በፍቅር እንደምናሳልፍ ንስር አማራ መልካም ምኞት እንመኛለን‼️

#መልካም_የትንሣኤ_በዓል‼️

27/08/16 ዓ.ም
@NISIREamhra

2 weeks, 3 days ago

*🔥የፋሲካ ሰሞን የጥንቃቄ መልዕክት ለፋኖዎቻችን‼️*
//////////////////////////////////////////////////////////
የአገዛዙ ሰራዊት መጪውን የትንሳኤ በዓል አስመልክቶ ፋኖዎች ተዘናግተዋል ብሎ በገመተው ሰዓት ድንገተኛ ጥቃት ሊፈጽም እንደሚችል ከውስጥ የተገኙ መረጃዎች ያሳያሉ፡፡

በተለይም የኦርቶዶክስ እምነት ተከታዮች በብዛት በሚገኙባቸው የጎጃም፣ ሸዋ፣ ጎንደር እና ወሎ አካባቢዎች በዓሉን ሰብሰብ ብለው በሚያከብሩ ፋኖዎች ላይ ድንገተኛ የድሮን ጥቃት በመፈጸም ጉዳት ለማድረስ ታስቧል፡፡

ከዚህ በተጨማሪም ፋኖዎች የበዓል ሰሞን ከምሽግ ወጥተው ወደ የቤተሰቦቻቸው የሚሄዱ ስለሚኖሩ በተናጠል ቤታቸውን በመክበብ ማጥቃት አለብን ብለው ማቀዳቸው ታውቋል፡፡

ሌላኛው እቅድ ፋኖዎች በበዓሉ ወቅት እንደማንኛውም ሰው መጠጥ ይጠጣሉ እሱን ማዘናጊያ አድርገው ጥቃት ሊከፉቱ አስበዋል፡፡

መላው ሰውነታቸው በአልኮል የሚዝልበትን ሰዓት በደህንነቶች በማጥናት ራሳቸውን መከላከል የማይችሉበትን ትክክለኛ ሰዓት በማገናዘብ ድንገተኛ ከበባ አድርገን እንጨርሳቸዋልን የሚል እቅድ መኖሩ ተሰምቷል፡፡

በመሆኑም ማንኛውም የፋኖ መሪ፣ አስተባባሪ እና ታጋይ የሚከተለውን ጥንቃቄ ያድርግ ስንል እንመክራለን፡፡

  በዓሉን ለማክበር ከምሽግ ወጥቶ ወደ የቤተሰቡ ወይም ከገጠር ወደ ከተማ ለመሄድ ያሰበ ፋኖ ካለ ሊታሰብበት ይገባል፣

  የበዓሉ አከባበር በውጊያ ወቅት ሲደረግ እንደነበረው የጥንቃቄ እርምጃ ለድሮን ኢላማ አመቺ ሆኖ አለመገኘት ተጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል፣

  ለበዓሉ እንኳን አደረሰን በሚል በጋራ/በቡድን የሚደረጉ ጭፈራዎች፣ዳንኪራዎች ሊታሰብበት ይገባል፣

  በበዓሉ ወቅት በእንኳን አደረሰን የደስታ ስሜት ተነሳስቶ አላግባብ ጥይት መተኮስ እና ተተኳሽ ማባከን ሊታሰብበት ይገባል፣

  የበዓል ሰሞን ወታደራዊ ልዩ ቃኝ ቡድን ማጠናከር ያስፈልጋል፡፡

አገዛዙ በፋኖዎቻችን ላይ ድንገተኛ ጥቃት ለመክፈት በዚህ ልክ አቅዶ የሚንቀሳቀስ ከሆነ በፋኖዎቻችን በኩል ተመሳሳይ እርምጃ ሊኖር ይገባል፡፡

ከትጥቅ ትግል ጎን ለጎን በሚዲያ ትግላችን ከእናንተ አንለይምና የግንባር መረጃዎችን ከቦታው ለእናንተ እናደርሳችኃለን ተከተሉን‼️

ይፋቴው💪#ድል_ለአማራ_ፋኖ‼️#ድል_ለአማራ_ህዝብ‼️

26/08/16 ዓ.ም**@NISIREamhra

2 weeks, 4 days ago

*🔥#የጥንቃቄ_መልዕክት‼️*

ስድስት ኦራል የአሸባሪው የአብይ አህመድ ሰራዊት ከወልድያ መስመር ወደ መርሳ መስመር አልፏል ጥንቃቄ ይደረግ ሲሉ የንስር አማራ ምንጮች ገልፀዎል‼️

ሼርርርር ይደረግ#ድል_ለአማራ_ፋኖ💪#ድል_ለአማራ_ህዝብ💪

25/08/16 ዓ.ም**@NISIREamhra

3 weeks, 5 days ago

ባህርዳር ዘንዘልማ...

ሰምኑን የአማራ ፋኖ በጎጃም ደጉ በላይ ሻለቃ ባህርዳር ከተማ ድረስ ዘልቆ በመግባት በተከታታይ ጥቃት በማድረስ በአገዛዙ አሽከሮች ላይ በርካታ ጉዳት ማድረሱ ይታወሳል ።

በዛሬው ዕለትም የአማራ ፋኖ በጎጃም ደጉ በላይ ሻለቃ አናብስት በዘንዘልማ ቀጠና አንድ የገቢዎች መኪና እና አንድ ፒካፕ እስከ ክልሉ ገቢዎች ባለሙያዎች ጋር በቦንብ አጋይተውታል።

በዚህ የተበሳጨው አገዛዙ የፋኖ ቤተሰቦችን እያፈነ ወስዷል። በዛሬው እለት ብቻ በርካታ የታጋይ እናቶችን አፍኖ ወስዷል።

#አምስት_ለአንድ...‼️

#ድል_ለአማራ_ህዝብ*💪#ድል_ለአማራ_ፋኖ💪*

16/08/16 ዓ.ም**

We recommend to visit

ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ

Last updated 5 days, 4 hours ago

Last updated 3 weeks, 1 day ago

በዚህ ቻናል ወቅታዊ፣ታማኝ እና ፈጣን መረጃ ያገኛሉ❗
መረጃ ለማድረስ እና ማስታወቂያ ለማሰራት ከስር ባለው ሊንክ ይጻፉልን👉http://t.me/ayulaw

Last updated 1 month, 3 weeks ago