ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።
@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna
#ኢትዮጵያ
Last updated 2 months, 3 weeks ago
Last updated 2 months, 2 weeks ago
ይህ ስለ Manchester United መረጃዎችን የሚያገኙበት የ Telegram ቻናል ነው 🇪🇹
--------------------------------------------------------------
☞︎| ስለ ማንቸስተር ዩናይትድ ትኩስ መረጃዎች
☞| ቀጥታ ስርጭቶች ከየስታድየሞቹ
☞| የዝውውር ዜናዎች
☞| ስለ ማንችስተር ዩናይትድ ታሪኮች
📩 ለማስታወቂያ ስራ DM :- @Marcoabdu
Last updated 1 month, 1 week ago
የእውነተኛ እውነት ጥንካሬ የሚመዘነው በሌላው ሐሰተኛነት መጠን አይደለም። እውነት የራሷ የወርቅ ሚዛን አላት። ዳውላ የሚያክል ውሸት የእውነት ብናኟን እንኳ አይመዝናትም። ስለዚህ በእጅህ ባለችው እውነት ታመን። ሌላው ዘንድ ባለው የሐሰት ክምር አትደንግጥ አትመጻደቅም። የዚያ የሐሰት ተራራ ማደግ ያንተ እውነት ማስረጃ አይኾንም። እውነት ከውሸት አትለካካም።
እውነትን መውደድ ብቻ ሳይኾን እውነተኛ ኹን። የአንተን እውነት ለኹሉ መንገር ግን አይጠበቅብህም። እውነት ያለ ቦታው ሲነገር ዋጋው ይቀልላል።
ጥቂት ስለ ድርድር
"ማንኛውም ጦርነት የሚጠናቀቀው በድርድር ነው" የሚል የተለመደ አባባል አለ። ተለመደ እንጅ ልክ አይደለም። በተለይ በሀገር ውስጥ ሲኾን። የብዙ ሀገር መሪዎች በኃይል ብልጫ የሥልጣን ርካብ ጨብጠዋል። ሌላው ቢቀር ራሷ አሜሪካ የጦርነት አሸናፊዎች የፈጠሯት ናት። በአሜሪካ በካሔደው የእርስ በእርስ ጦርነት የተባበሩት ኃይሎች (The Union Forces) የኮንፌደሬት ኃይሎችን (Confederate States)ን አሸንፈው ጦርነቱ አበቃ።
አባባሉ ተፋላሚዎች ሉዐላዊ የኾኑ ሀገሮች ከኾኑ በአብዛኛው ልክ ሊኾን ይችላል።
በሀገር ውስጥ ጦርነቶች (Civil war) ፵ በመቶ የመንግሥት ኃይል፣ ፴ በመቶ የአማፂ ኃይል በጦርነት ያሸንፋሉ የሚል ጥናት አለ። የቀረው ፴ በመቶ በድርድር ያልቃል ይባላል። ከዚህም የምንረዳው ፸ በመቶው ወይም አብዛኛው ጦርነት በአንደኛው ወገን የኃይል የበላይነት ወይም አሸናፊነት እንደሚጠናቀቅ ነው።
በተለይም ሥልጣን የሚጠይቅ የትጥቅ ትግል በድርድር ያልቃል የሚለው ሞኝነት ብቻ ሳይኾን ጅልነት ይኾናል። ሥልጣን ለመልቀቅ የሚደራደር "ጻድቅ" አገዛዝ አለ ብሎ ማሰብ ያስበላል። ጠበል የገባ ጋኔን እለቃለሁ ይላል። እርሱም ወድዶ ሳይኾን ተገድዶ ነው። እኔ ፍላጎቴ ከመንበረ ሥልጣን በታች ነው የሚል ግን ቢደራደር አይፈረድበትም። ለሥልጣን ከኾነ ግን ድርድርን ከድል በኋላ ያስከተላል። እርሱም ያገባኛል ከሚሉ ኹሉ ጋር እንጅ ከአንድ አካል ጋር ብቻ አይኾንም።
ስለዚህ ብርቱ ጥንቃቄ ይፈልጋል።
ጦርነት በሚከተሉት ፭ ኹኔታዎች ይቋጫል ተብሎ ይታመናል።
፩. በተናጠል ራስን በማግለል - Disengagement
ከተፋላሚ ኃይሎች አንደኛው ወገን ከጦርነቱ ራሱን ሲያገልል። ቻይና እና ሕንድ በ፲፱፻፶፭ ዓ.ም. በድንበር ይገባኛል የተቀሰቀሰ ጦርነት ውስጥ ገብተው ነበር። ይኽም የSino- Indian Border ጦርነት በመባል የሚታወቀው ነው። ኾኖም ቻይና በተናጠል ውሣኔ ራሷን በማግለሏ ጦርነቱ ቆሟል።
፪. ድል በማድረግ - Conquest
፹፰ ሀገራት የሉዐላዊነት ዕውቅና ሰጥተዋት የነበረችው ደቡብ ቬትናም በ፲፱፻፮፯ ዓ.ም. በሰሜን ቬትናም በጦርነት ተሸንፋ ጦርነቱ ተጠናቅቋል። አንድ ሀገር ቬትናምም ተመሥርታለች።
፫. De facto surrender (በእጅ አዙር እጅ መስጠት)
እየተሸነፈ ያለው ወገን በድርድር የተወሠነ ፍላጎቱ ተጠብቆለት ጦርነት ለማቆም የሚገደድበት ዓይነት ጦርነት ነው። ነገር ግን እጅ እንደመስጠት አይቆጠርም ስለሚባል በእጅ አዙር እጅ መስጠት ይባላል። አልሸሹም ዘወር አሉ እንዲል ያገር ሰው።
የጀርመን እና የፈረንሳይ ኹኔታ ለአብነት ይጠቀሳል። በ፲፱፻፴፪ ዓ.ም. ጀርመኖች ኹለት ሦስተኛ የሚኾነውን ግዛት ድንገት በኃይል ማጥለቅለቃቸውን ተከትሎ የፈረንሳይ ምክትል ጠቅላይ ሚንስትር ማርሻል ፊልፕ ፔቴይን ከጀርመን ናዚዎች ጋር የተኩስ አቁም ይስማማል። ፓሪስ በጀርመኖች እጅ ወድቃ የተደረገ ስምምነት ነው። ስለዚህ ቪቺ የፈረንሳይ ዋና ከተማ ኾነች። የፈረንሳዩ መሪ በጀርመን ቁጥጥር ሥር ያለ "ነፃ ቀጠና" ይኹን ብሎ የአሻንጉሊት አስተዳደሩን ተቀብሎ የፈረመበት ሥርዓት በእጅ አዙር እጅ መስጠት ሊባል ይችላል።
፬. እጅ በመስጠት - Formal Surrender
ተሸናፊው ወገን የአሸናፊውን አሳብ ሙሉ በሙሉ ለመቀበል ሲስማማ ጦርነት የሚቆምበት መንገድ ነው። በኹለተኛው ዓለም ጦርነት ጃፓን እና ጀርመን ከተባበሩት ኃይሎች ጋር የገቡት ስምምነት ይኽን ይገልጠዋል።
ጀርመን ከኹለት እንድትከፈል ያስገደደ ጃፓን ደግሞ እስከ ፲፱፻፵፬ ዓ.ም. በውጭ ኃይል እንድትመራ ያደረገ ነው።
፭. በድርድር የሰላም ስምምነት - Negotiated Peace Agreement
ተዋጊ ኃይሎች በሰጥቶ መቀበል መርሕ ወይም በማመቻመች የሚስማሙባቸውን ነጥቦች ለይተው ጦርነት ለማቆም ሲወሥኑ።
ሠናይ ሠናዩ ይታየን እንጅ ጎበዝ። ወንድሞች ደኅና ሰብሰብ እያሉም አይደል? ከትናንት በስቲያ ጎንደር፣ ደሞ ትናንት ቤተ ዐምሐራ ወሎ ነገ ደግሞ ባለ ተራ. . .።
ጥንቱንም ክፉ ወሬ ይበዛል። ሊቀ ነቢያት ሙሴ ምድሪቱን ይሰልሉ ዘንድ ፲፪ ሰዎችን አሰማራ። ዐሥሩ ክፉ ወሬ አሸባሪ ምላሽ ይዘው መጡ። ኹለቱ ብቻ እናሸንፋለን እንውጣ ብለው ሠናይ ዜና አመጡ። የኹለቱ ረታ ኋላም ሰመረ።
እንዲያ ነው። ቤት ዘግቶ መምከር ከዚያም ማበር!
በክርስቶስ ስም እንኳ ሳይቀር ሰይጣን ይመጣል። ክርስቶስ እንዲጠላ ብዙ ክፉና መጥፎ ጭካኔ የተሞላበት የነውር ሥራ በዐደባባይ ያደርጋል። በፋኖ ስም ደግሞ ብልጽግና ያርዳል።
That is it!
ብዙ ሰው ፈጣን ድል ይፈልጋል። አንድ ኹኑ እያለ ይቃትታል። ከዚህ መኻል ግን አንዳንዱን የኾነ ጎጥ መሳይ ቡድነኝነት ወይም መጥበብ እግር ተወርች ፈጥርቆ ይዞታል። ያለ ማቋረጥ የራሴ ያለውን ሲክብ "ጠላቴ" ያለውን ሲሰድብ ውሎ ያድራል። ከብልጽግና ተከፋዮች በላይ ይኽኛው ይበልጥ ዕረፍት ማጣት ይታይበታል።
አኹን የዐማራ ፋኖ ትግል ኹለተኛ ረድፍ ጠላት እንደዚህ ያለው መንደሬነት ነው። በቅድሚያ መወገድ አለበት። ይኽ ሰፈርተኛ ክፍለ ሀገር ቢሰጠው አውራጃዬ ይላል። አውራጃ ቢሰጠው ወረዳዬ ይላል። ወረዳ ቢሰጠው ቀበሌዬ ይላል። ቀበሌ ቢሰጠው ጎጤ ይልሃል። ጎጡን ብትሰጠው ደሼ ይልሃል። ደሹን ብትሰጠው ጎጆዬ ይልሃል። ከጎጆው ብትገባ እኔ ብቻ ይልሃል። ከራሱ በቀር ለማንም ደንታ የለውም። ይኽ ልክፍት ወይም መጋኛ ነው።
እባካችሁ እኛም የዚህ ልክፍት ተጠቂ ከኾንን ፈጥነን እንውጣ። በሽተኞች ላይም እንዲድኑ ወይም እንዲገለሉ እንጨክን። አንድነት ኑ ወደ እኔ በማለት አይሰምርም። የአንተን ወደሌላው መሔድ ይፈልጋል። ከጎጥ መውጣት!
አንድነትን አብዝተን እንስበክ!
አደራችሁን!
እኛ የምናውቃት ሙንጣዝ ወይ ባንዳ ናት ወይ ጠውላጋ፣ ዐቅመ ቢስ፣ ለዋሳ ናት።
ጣልያን ወደ ኤርትራ በገባ ጊዜ ከእኛው ሰዎች መካከል ጨው እያላሰ ሙንጣዝ፣ ቡልቅ ባሻ እና ባሻ ብዙቅ እያለ በመሾም ወገንን ከወገኑ አለያይቶ አፋጅቷል። እነዚያ ባንዳዎች ከሚጠሩበት አንዱ ሙንጣዝ የሚል ይገኝበታል።
ምናልባትም ባንዳነትን የሚያነውረው ማኅበረሰባችን ለባንዳዎች የሚታደለውን ሙንጣዝነት ከመጠየፍ ሳይኾን አይቀርም ሰላላ፣ መንማና፣ ጠውላጋ የኾነን ሰው ሙንጣዝ ብሎ ያጠይፋል።
የዛሬዋ ሙንጣዝ ግን ቤተ መንግሥት ስትገባ ሥራዋን ቀየረች። ባንዳነቴን እርሱልኝ ባይኾን የሹም ዶሮ ነኝ እንደማለት አለች። ሙንጣዝ ሸፍታም ጀግናም አታውቅም።
"የኢትዮጵያ ሕዝብ የዐማራ ሕዝብ ዕንባ [እና ደም] በዋንጫ ቢሰጣቸዉ የማይጎፈንናቸዉን የብልጽግና ሥርዓት ቁንጮዎች በቃችሁ ሊላቸዉ ይገባል።"
ዶ/ር ወንድወሠን አሰፋ
ዛሬ በፍርድ ቤት የቀረበበትን የፈጠራ ክስ ሲቃወም የተናገረው።
የቅዱሳንም የሊቃውንትም ነቅዕ ዲማ (ድማኅ ራስ እንዲለው) ከመጠቃቱ ይልቅ ነገረ አድግ የሚያብከነክናቸው የአህያ ሥጋ አለመበላቱ የቆጫቸው ሲርመሰመሱ የተፈጠፈጥንበትን ቁልቁለት ያሳያል።
በነገራችን ላይ እንደዚህ ያለው ነገር ጥቅስ አያስጠቅስም። ካመኑበት ነቀላውን ይዘው መዘንጠል ነው ያለባቸው። ይኽን ካልበላችሁ ብሎ ስብከት የለም።
ይበቃል!!!
የዐማራን ማንነት ታሪክ እና ወግ በሚመጥን ደረጃ ልዩነቶች ካሉንም ለመፍታት እንወሥን። መተቻቸት ቢያስፈልግም በጥዩፍ ቃል መሸነቋቆጡ አይበጅም። ተጋድሎውን ባያቆመው እንኳ ይጎትተዋል።
አኹን አንድ መኾንን እንናፍቅ። ከፊት ያለውን ጎልያድ ረስተን ጠጠሮቻችንን ወደ ጎን በማፈናጠር ጊዜም ጉልበትም ሀብትም አናባክን።
እንደዚህ የሚያደርጉት ኹሉ ቃላችንን ሰምተው ከአኹን ጀምሮ ያቆሙ ዘንድ እንጣራለን።
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።
@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna
#ኢትዮጵያ
Last updated 2 months, 3 weeks ago
Last updated 2 months, 2 weeks ago
ይህ ስለ Manchester United መረጃዎችን የሚያገኙበት የ Telegram ቻናል ነው 🇪🇹
--------------------------------------------------------------
☞︎| ስለ ማንቸስተር ዩናይትድ ትኩስ መረጃዎች
☞| ቀጥታ ስርጭቶች ከየስታድየሞቹ
☞| የዝውውር ዜናዎች
☞| ስለ ማንችስተር ዩናይትድ ታሪኮች
📩 ለማስታወቂያ ስራ DM :- @Marcoabdu
Last updated 1 month, 1 week ago