ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።
@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna
#ኢትዮጵያ
Last updated 2 months, 3 weeks ago
Last updated 2 months, 2 weeks ago
ይህ ስለ Manchester United መረጃዎችን የሚያገኙበት የ Telegram ቻናል ነው 🇪🇹
--------------------------------------------------------------
☞︎| ስለ ማንቸስተር ዩናይትድ ትኩስ መረጃዎች
☞| ቀጥታ ስርጭቶች ከየስታድየሞቹ
☞| የዝውውር ዜናዎች
☞| ስለ ማንችስተር ዩናይትድ ታሪኮች
📩 ለማስታወቂያ ስራ DM :- @Marcoabdu
Last updated 1 month, 2 weeks ago
«ለዚህች ሌት (የሻዕባን አጋማሽ) ትሩፋት አላት ፣ ልዩ የሆነ ምህረትና ልዩ የሆነ የዱዓ ተቀባይነት ይገኝባታል » ኢብኑ ሀጀር አል ሀይተሚ
«የሻዕባን አጋማሽ ሌት ለርሷ ብልጫ አላት ፣ ከሰለፎች በዚህች ሌት የሚሰግዱ ነበሩ ፣ ሌቷን ህያው ለማድረግ በመስጂድ መሳባሰብ ግን አዲስ መጤ ተግባር ነው » ኢብኑ ተይሚያህ
«በዚህች ሌት አንድ ሙእሚን አላህን ለማውሳት እና (ለወንጀል ማህርታን ፣ ለነውር ሲትርን ፣ ለጭንቀት ፈረጃን) ለማግኘት ለዱዓእ እራሱን ነፃ ማድረጉ ተገቢ ነው ። ይህን ተግባሩም በተውባ ሊያስቀድም ይገባል ፣ በዚህች ሌት አላህ አላህ ወደርሱ ለሚመለሱ ፅፀትን ይቀበላል » ኢብኑ ረጀብ አል ሀንበሊ
የተጨነቁ ነፍሶች የተሰበሩ ልቦች አስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ያሉ የአላህ ባሮች ሁሉ የቀልባቸውን መሻት የሚያገኙትባት ሌት አላህ ያድርግልን 🤲
ያሻውን የሚሰራው ወይም በቁርዐን ገለፃ { فَعَّالࣱ لِّمَا یُرِیدُ } የሆነው አላህ ብቻ ነው ። ይሄ አላህ ብቻ የሚገለፅበት የርሱ ብቻ ስልጣን ነው ። ላ ጀብራኢል ወላ ሚካኢል ወላ ኢስራፊል ይሄ ስልጣን የላቸውም ። የብርቱ ኃይል ባለቤት የሆኑት መላዐክት እንኳን ወደ ምድር ለመውረድ የጌታቸውን ፍቃድ የሚጠብቁ ናቸው ።
አሜሪካ ጋዛን አጠፋለው ወይም እጠቀልላለው አለች ማለት ጋዛን ማጥፋት ወይ መውረስ ትችላለች ማለት አይደለም ። ያሉትን ወይም የፈለጉትን ማድረግ ቢችሉማ መለኮታዊ ስልጣን አላቸው ማለትኮ ነው ። በፍጥረተ ዓለም ውስጥ ያለ ሁሉም ነገር በአላህ ፍቃድና ፍላጎት ስር የሚንቀሳቀስ ነው ። ኢብሊስ እንኳን ያለ አላህ ፍቃድ እና ከውንይ ፍላጎት አንዲት እርምጃ አይራመድም ። የዓለም ህዝብ ተሰብስቦ ልጉዳህ ቢልህ አይጎዳህም እርሱ ካልፈቀደ በቀር ። የሚሆነው ሁሉ ሚሆነው በአላህ እይታና ፍቃድ ስር ነው ። ሰዎች የሆነ ነገር እናረጋለን ስላሉ ብቻ ማድረግ አይችሉም ። የስልጣንና ገንዘብ ጥጉን ይዞ የነበረው ፊርዐውን አንዲት ዘንግ ይዞ የመጣውን ሙሳ በቤተመንግስቱ ሲመላለስ ማጥፋት አልቻለም ፣ የዐድ ህዝቦች ተራራን በሚቦረቡር ኃይላቸው ነብዩላህ ሁድን ማስወገድ አልቻሉም ። ለምን ስንል ቁርዐን «በምድር ላይ ምንም ተንቀሳቃሽ የለችም እርሱ አናትዋን የያዛት ብትሆን እንጂ» ሲል ይመልስልናል። ሁሉም መኽሉቅ በኻሊቁ እጅ ስር ነው ። እርሱ ካልፈቀደና ይሁን ካላለ ማንም ምንም ማድረግ አይችልም ። ተውሒድ ማለት ይሄን በፅኑ ማመን ነው ። ነገሮችን ሁልጊዜ በፖለቲካል perspective ብቻ ማየት የለብንም ።
ኢጥመኢኑ አላህ ብቻ ያለው ነው ሚሆነው ፣ ለከሀዲያን ደግሞ የድል መንገድን አያደርግም ። « ... አላህም ለከሓዲዎች በምእምናን ላይ መንገድን በፍጹም አያደርግም » አን-ኒሳእ
በቀድሞ የእስልምና ታሪክ ሲህር ለተደረገባቸው ወይም ጂኒ ለለከፋቸው 🙄 ወይም በሌሎች አካላዊ በሽታዎች ለተጠቁ ሰዎች በቁርዐን ሩቃ የሚደረግባቸው የህክምና ቦታዎች ኖረው ያውቃሉ ?የድሮ ሙስሊሞች አላህ ባገራላቸው አስባቦች ሰዎችን ከበሽታ ለማዳን ሙስተሽፈያት/hospitals እንደናበራቸው ታሪካችን ይነግረናል ፣ የሩቃ ሀኪም ቤቶች እንደነበሩ ግን በግሌ መረጃው የለኝም ። ሲቀጥል በቁርዐን የታመሙ ሰዎችን ለማከም የህክምና ቦታዎችን መክፈትና በሱም ገንዘብ መሰብሰብ ሸሪዓዊ መሰረት አለው ? ከጂኖች ጋ( ዓለመል غيب ) conversation ማድረግስ ከሰሀቦች አሰር አለ ? ሰሞኑ እየተመላለሰብኝ ያለ ጥያቄ ነው ።
አንዳንድ ሰው ላመነበት የፖለቲካ ርዕዮትም ይሁን አልያም "ህዝቤ" ለሚለውም አመለካከቱ ይሁን ብቻ በአካሄዱ ግን ምንም አይነት የአኼራ ግብ ሳይኖረው ለዱንያዊ ግብ የሚያደርገው መራር ትግልና ፅናት ይገርመኛል። የያኔዎቹ ትውልዶች የሚባሉት የዘመነ ሀይለስላሴና የደርግ ፖለቲካ ሰለባዎች እስከሞት ድረስ ላመኑበት መስመር የሚያደርጉት ትንቅንቅ አስደናቂ ነው። በተቃራኒው በዚህ መነጽር ውስጥ ለትግሉ የአኼራን እውነትነት የሚያምነው ህዝቡ ሙስሊምን ለተመለከተ ሰው ደግሞ ራሱን አብዝቶ እንዲፈትሽ የሚያደርግ ነው። አኼራ ያለብን እኛ ለዑማችን ሁለንተናዊ ለውጥ ስንል ዱንያን በመናቅ በሙሉ አቅማችን መትጋትና መልፋት ፈርድ የሚሆነው በኛ ላይ አልነበረም?
ለማስታወሻ ያህል
ፍጡራንን አስመልክቶ የሚያደርጉት ነገር ኹሉ የተጻፈ ነው። የዝህችን ምድር ብርሀን ከማየታችን አስቀድሞ ስለእኛ በመዝገባችን ላይ ተጽፏል። ስለየትኛውም የሚገጥመን ነገር መጨነቅና መጠበብ ትርፉ ነፍስን መጉዳትና ማስጨነቅ እንጂ ሌላ ምንም የለውም። ረጅሙን መንገድ ቀጥል፣ የሚቻለውን ነገር ኹሉ በመፈጸም ላይ ታገል። ነገሮችህን ኹሉ ለእርሱ ብቻ ስጥ። ባሪያ ምን መብት አለው?! ዝም ብሎ አይደል የሚኖረው?!
ለአላህ የሚደረግ ባርነት (ዑቡዲያ) ደግሞ ትክክለኛውን ነጻነት ያወርሳል። ወዳጅ ከወዳጁ ጋር በሚገናኝበት ውድቅት ላይ ተነስቶ አስረዳኝ ብሎ መማጸን፣ ይህን የተወሳሰበ ዐለም ለመረዳት ያግዛል።
አላህ የልብ ንቃት ይለግሰን ♥
«ነገራቶችን በ‹ኩን ፈየኩን› የሚፈፅም ጌታ እስካለን ድረስ ‘ሁሉም ነገር በጊዜው መልካም’ ይሆናል»
ነጂብ መህፉዝ
ሰባሐል ኸይር
ለሰዎች ቀልብ መሰበር ለሰዎች ሀዘን ውስጥ መግባት ለሰዎች ቁስል ሰበብ አትሁኑ ፣ በንግግራቸው በተግባራቸው አማኞችን የሚያስከፉና የማይሽር ጠባሳን የሚጥሉ ሰዎች آجلا أو عاحلا ዋጋቸውን ያገኛሉ ። በተለይ ያሀ ሰው ከአላህ ጋ ቅርበት ያለው ከሆነ መዘዙ የከፋ ነው የሚሆነው ። አንተ ያጠፋሀውን ጥፋት ከነጭራሹ ረስተሀው ሊሆን ይችላል ለዛሰው ግን በቀላሉ ማይሽር ቁስል ትተህ ነው ምታልፈው ። በዚሁ ስራህ ስትያዝ ራሱ ለምን እንደተያዝክ ሁሉ አታውቀውም ። የአማኞች ቀልብ የአላህ ውድ ንብረት ናትና እንጠንቀቃት ።
ታላቁ ሰሀቢይ ሰይዱና ዑስማን በድር ዘመቻ ላይ አልተሳተፉም ነበር ። ምክንያቱ ደግሞ የረሱለላህ ልጅ የሆነቺው ሩቅያህ በመታመሟና ዑስማንም እሷን የመንከባከብና የማስታመም ኃላፊነት ከረሱል በኩል ተጥሎበት ስለነበር ነው ። መዲና ውስጥ የሩቅያህን የማስታመም ኃላፊነት መውሰድ የሚችሉ ብዙ እንስቶች ነበሩ ። ነገር ግን ለሚስት ከቧላ በላይ ቅርብ ሰው የለምና እሷን ለማስታመም ሰይዱና ዑስማን በድርን ሚያህል ታሪካዊና ታላቅ ዘመቻ እንዲያልፈው ሆነ ። በዚህ ውስጥ ለቤት አባ ወራዎች ትልቅ ትምህርት አለ !
በግንኙነት ዓለም ውስጥ ብዙ አይነት ሰዎች ያጋጥሙሀል ።
አንዳንዱ እንደ ፌክ ሽቶ ነው ለጌዜው ማዕዛው ቢማርክህም ግን ወዲያው ሽታው ብን ብሎ ይጠፋል - የማይዘልቁ ግንኙቶች በዚህ ይመሰላሉ ። እንደ በሽታ የሆነ ግንኙትም አለ ከዛ ሰው መለየትህ Reliefን የሚሰጥህ ፣ ሌላኛው ደግሞ በትውልድ ሀገር ይመሰላል ስትለያቸው ባይተዋርነት የሚሰማህ አይነት ግንኙነት ። ከዚህም የባሰ አለ እንደ ሩህና ጀሰድ አይነት ሆኖ እነሱን መነጠል እንደ ሞት የሆነ አይነት ወዳጅነት ። ሁሉንም ግንኙነቶች ጊዜና መከራ ይገልጣቸዋል።
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።
@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna
#ኢትዮጵያ
Last updated 2 months, 3 weeks ago
Last updated 2 months, 2 weeks ago
ይህ ስለ Manchester United መረጃዎችን የሚያገኙበት የ Telegram ቻናል ነው 🇪🇹
--------------------------------------------------------------
☞︎| ስለ ማንቸስተር ዩናይትድ ትኩስ መረጃዎች
☞| ቀጥታ ስርጭቶች ከየስታድየሞቹ
☞| የዝውውር ዜናዎች
☞| ስለ ማንችስተር ዩናይትድ ታሪኮች
📩 ለማስታወቂያ ስራ DM :- @Marcoabdu
Last updated 1 month, 2 weeks ago