ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።
@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna
#ኢትዮጵያ
Last updated 2 months, 3 weeks ago
Last updated 2 months, 2 weeks ago
ይህ ስለ Manchester United መረጃዎችን የሚያገኙበት የ Telegram ቻናል ነው 🇪🇹
--------------------------------------------------------------
☞︎| ስለ ማንቸስተር ዩናይትድ ትኩስ መረጃዎች
☞| ቀጥታ ስርጭቶች ከየስታድየሞቹ
☞| የዝውውር ዜናዎች
☞| ስለ ማንችስተር ዩናይትድ ታሪኮች
📩 ለማስታወቂያ ስራ DM :- @Marcoabdu
Last updated 1 month, 1 week ago
ወያኔ የተመሠረተበትን አላማና ድብቅ አጀንዳውን በከፊል ለመረዳት ይሄንን ያዳምጡ።
አሁን የወያኔ ወራሽ ነን የሚሉት እነ ደብረፅዮን ይህ የአቦይ ስብሃት አቋምና እሳቤን የሚያራምዱና የሚያስቀጥሉ ናቸው።
አቦይ ስብሃትና መለስ ዜናዊ " ዛላምበሳና ባድመ ለ20 እና ለ30 ዓመታት ከሻዕቢያ ጋር ቢቆዩ ምን ችግር አለው ታዲያ" እንዲሉ ያስገደዳቸው ሌላ ሳይሆን ደማቸው ውስጥ የተዋሃደው የ"አባይ ትግራይ " እሳቤ ነው።
የማታ ማታ የአባይ ትግራይ ምስረታ እውን መሆኑ አይቀርም የሚል ፅኑ አቋም ነበራቸው።
P.S
መተማን እስከ ቤንሻንጉል ድረስ ባካለለውና ወያኔ ባሰራው የታላቋ ትግራይ ካርታ ላይ የተወሰኑትን የአማራ ክልል መሬቶች ለሱዳን መንግስት በአደራ መልክ እንደሰጡስ ታውቁ ነበር ?
ከኢትዮ-ኤርትራ ጦርነት በኋላ ከህወሓት የተባረሩበትን ሁኔታ ወ/ሮ አረጋሽ አዳነ ሲያስረዱ👇
// መለስ ዜናዊ "እያበላና እያለቀሰ" ነው አባላቱን በማሳመን ድጋፍ ያሰባስብ የነበረው ።ለነገሩ ያኔ እነሱ ቀድመው ባያሰናብቱኝ ኖሮ እኔው እራሴ ህወሓትን ለመልቀቅ ውሳኔ ላይ ደርሼ ነበር //
- ወ/ሮ አረጋሽ አዳነ
በትናንትናው ዕለት የተከናወነው የምዕራብ ጎንደር ሃገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ አቡነ ሰላማ ወደ ወልቃይት ጠገዴ ጉብኝት በርካታ ታሪካዊና ፖለቲካዊ ትርጉሞችን የያዘ ነው።
ይህ ጉብኝት የወልቃይት ጠገዴ ህዝብ ጎንደር ጋር ያለውን ጥልቅ ታሪካዊ፣ ባህላዊና መንፈሳዊ ትስስር የሚያሳይ ሲሆን፣ በተለይም ከቅርብ ዓመታት ወዲህ በተፈጠረው የማንነት ጥያቄና የፖለቲካ ውጥረት አውድ ውስጥ ሲታይ ይበልጥ ጠቀሜታ አለው።
ወልቃይት ጠገዴ ለረዥም ዘመናት የጎንደር አካል እንደነበር ይታወቃል። ነገር ግን ከ1984 ዓም ጀምሮ ያለ ህዝቡ ፈቃድና ይሁንታ በጉልበት በትግራይ ክልል ውስጥ እንዲካተት በመደረጉ ምክንያት ነዋሪው ህዝብ ማንነቱን በተመለከተ ከፍተኛ ግጭት ውስጥ መግባቱም በዓለም የታወቀ ሐቅ ነው ።
ይህ ጉዳይ የወልቃይት ጠገዴን ህዝብ ከጎንደር አማራ ህዝብ ለመለየት የተደረጉ ተደጋጋሚ ሙከራዎችን ተከትሎ የተፈጠረም ነው።
ትናንት በአቡነ ሰላማ ወደ ወልቃይት ጠገዴ የተደረገው ጉብኝት የሚያመለክተው፡-
1ኛ. * ታሪካዊ ትስስር:
ይህ ጉብኝት የወልቃይት ጠገዴ ህዝብ ጎንደር ጋር ያለውን ጥልቅ ታሪካዊና መንፈሳዊ ትስስር የሚያረጋግጥ ነው።
2ኛ. * የማንነትና አንድነት ማሳያ :
አቡነ ሰላማ በአካባቢው መገኘታቸው የወልቃይት ጠገዴ ህዝብ ጎንደር ጋር ያለውን ማንነታዊ ትስስር ማረጋገጫ ነው።
3ኛ. * የቤተክርስቲያን አንድነት:
የወልቃይት ጠገዴ ህዝብ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን አንድነት ላይ ያለውን እምነት ያሳያል።
እንደሚታወቀው በቅርቡ የትግራይ ክልል የራሱን ሲኖዶስ በማቋቋም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን አንድነት ላይ ስጋት ፈጥሯል።
ይህ ደግሞ የወልቃይት ጠገዴ ህዝብን ጨምሮ በርካታ ኢትዮጵያዊያን ክርስቲያኖችን አሳዝኗል ።
የአቡነ ሰላማ ጉብኝት የወልቃይት ጠገዴ ህዝብ አንድ ፓትርያርክ አንድ ሲኖዶስ የሚለውን የቤተክርስቲያን መርህ በመደገፍ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን አንድነት ላይ ያለውን እምነት አረጋግጧል።
* መደምደሚያ
በአቡነ ሰላማ የተደረገው ጉብኝት በወልቃይት ጠገዴ ስላለው የማንነት ጥያቄና የፖለቲካ ውጥረት ብቻ ሳይሆን፣ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን አንድነት ላይም ጠቃሚ አስተዋጽኦ ያደርጋል።
ይህ ጉብኝት የወልቃይት ጠገዴ ህዝብ ከጎንደር ጋር ያለውን ጥልቅ ታሪካዊ፣ ባህላዊና መንፈሳዊ ትስስር የሚያረጋግጥ ሲሆን፣ በተመሳሳይም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን አንድነት ላይ ያለውን እምነት ያጠናክራል።
#ወልቃይት_ጠገዴ #ጎንደር #አንድ_ሲኖዶስ #አንድ_ፓትሪያርከ
@hilinaazeze (via FB)
ህዳር 2 / 2013 ዓም ጧት ላይ እድሪስ ውስጥ እጆቻቸውን የፊጥኝ ታስረው በጥይት የተደበደቡ ሰማዕታት
ሰማዕታት ሲዘከሩ
(አቶ አማረ ጥሩነህን እንደማሳያ)
በ2009 ዓ.ም አጋማሽ ላይ አቶ አማረ ጥሩነህ አንዳንድ "የወልቃይት ጠገዴ የአማራ ማንነትና ወሰን አስመላሽ ኮሚቴ አባላት ናችሁ" ተብለው በእስር ሲሰቃዩ የቆዩ ወገኖች እንዲፈቱ በተደረገ ጥረት ታሳሪዎቹ ለተጠየቁት የዋስትና ብር ለሁሉም ብርና የቤታቸውን ካርታ በማስያዝ ወንድሞቻቸውን (ለጊዜውም ቢሆን) ያስፈቱ ሰው ነበሩ።ቀድሞዉኑም በወያኔ ጥርስ ከተነከሰባቸው ዝርዝር ውስጥ የተካተቱት አቶ አማረ ከዚያች ዕለት ጀምሮ ለሞት እንደታጩ መረዳታቸውን ለቀርብ ጓደኞቻቸው ይናገሩ ነበር። በየስብሰባውና በየመድረኩ ስማቸው እየተነሳ ይወነጀላሉ - በግምገማ ስም ለሰዓታት እየቆሙ በስድብና በወቀሳ ሰውነታቸው ደክሞና ዝሎ ወደ ቤታቸው ይመለሳሉ።
ከእነዚህ የግምገማ መድረኮች መካከል በ2010 ዓ.ም የሆነው ተጠቃሽ ነው።በወቅቱ በጎንደርና አካባቢውም ተመሳሳይ የ"አይደገምም" መድረኮች ይደረጉ የነበረበት ጊዜ ነው።እናም ከሌሎች የወልቃይት ጠገዴ ተወላጆች ጋር በመሆን ከህዝብ ፊት የቀረቡት እነ አቶ አማረ ጥሩነህ በአገዛዙ ካድሬዎች አማካኝነት " የአስመላሽ ኮሚቴውን በብር ትደግፋላችሁ .... ለኮሚቴው መረጃ ታቀብላላችሁ ...በየእርሻ ካምፖቻችሁ ወታደራዊ ስልጠና ትሰጣላችሁ " የሚሉ ጠንካራ ውንጀላዎች ቢሰነዘርባቸውም ውንጀላው መሠረት የሌለውና ሀሰት መሆኑን በድፍረት ሞግተዋል።ከጥርጣሬ ውጪ መረጃና ማስረጃ ያልነበራቸው ከሳሾቹ አማራጭ በማጣታቸው ብቻ በከባድ ማስጠንቀቂያ እንዲሸኟቸው ቢገደዱም ሰዎቹን ለማጥፋት አመቺ ጊዜንና ቦታን ከመጠበቅ ግን አልቦዘኑም ነበር።
ከሶስት አመታት በኋላ ወያኔ ሲጠብቅ የነበረውን አመቺ ጊዜ አገኘ ።
ከመንግስት ጋር ጦርነት የገቡት የወያኔ ወታደሮች በመጨረሻዎቹ የሽንፈት ቀናቶች ጥቅምት 30 , 2013 ዓ.ም ማይካድራን በደም አበላ አጥበው ከጨረሱ በኋላ አመሻሹ ላይ ወደ ሁመራ በመምጣት በየቤቱ እየዞሩ በቀጠሮ ያቆዩዋቸውን የወልቃይት ጠገዴ ተወላጅ "ሟቾችን" ለቀሟቸው።
ከእነዚህ መካከል አቶ አማረ ጥሩነህ አንዱ ነበሩ። ከቀኑ 11 ሰዓት ላይ ገና ከሻወር እንደወጡ ነበር ወደ ቤታቸው ቅጥር ጊቢ ከገቡ ገዳዮቻቸው ጋር ፊት ለፊት የተያዩት። "ትፈለጋለህ" ብለውም ወሰዷቸው።
ከሁለት ቀናት በኋላ ህዳር 2/ 2013 ዓ.ም ከሁመራ ከተማ 35 ኪሜ ገደማ በምትርቀው "እድሪስ በተባለች ከተማ ዙሪያ ላይ የአቶ አማረ ጥሩነህን ጨምሮ የሌሎቹ "ሟቾች" "አስከሬኖች ተገኙ።
ነብስ ይማር !!
(ዛሬ የአቶ አማረ ጥሩነህ አራተኛ አመት የመታሰቢያና የፍትሃት ስነስርዓትን ከፈፀሙ የቤተሰብ አባላት ጋር ከነበረኝ አጭር ቆይታ በኋላ የተፃፈ )
ከድራማ ወደ አክሽን
የደብረፂዮን አንጃ የቀን ተቀን ስራዎቼን ከማደናቀፍ አልፎ አሁን ላይ ግልፅ ወደሆነ የመንግስት ግልበጣ እንቅስቃሴ ውስጥ ገብቷል//
--ከዛሬው የትግራይ ክልል ፕሬዚዳንት ፅ/ቤት መግለጫ ላይ የተወሰደ
እግረ መንገድ ......
እኔ በበኩሌ አጀንዳ እየሰጠሁ አይደለም።የእግረ መንገድ ወሬዬ ነው።
ምናልባት አጀንዳችሁ ሆኖ ከተናጠሳችሁም ያው እንደፍጥርጥራችሁ።?
===============+=========
በአፍሪካ ህብረት አወያይነት የወያኔን ህጋዊ ሰውነት በመመለስና በሌሎች ፖለቲካዊ ጉዳዮች ዙሪያ በመንግስትና በወያኔ መካከል ይደረጋል የተባለው የሁለትዮሽ ውይይት ለህዳር 2017 ዓ.ም ተቀጥሮ ነበር ። ቀኑ የተቆረጠው ግንቦት ወር ላይ በ2016 ዓ.ም ነው።
ለነገሩ አሁን ወያኔ እርስበርሱ እየተናጠሰ ስለሆነ ይህ ውይይት እውን ይሆናል ብዬ አላምንም።
?ለማንኛውም ግን ....
የአሜሪካው ምርጫ ተጠናቆ ትራምፕ በተመረጠ ማግስት ውይይቱ እንዲካሄድ በመፈለግ ይሄንን ቀን የመረጠው አካል በእውነቱ ወያኔን ጠንቅቆ የተረዳ ምጡቅ ፖለቲከኛ መሆን አለበት ‼️
?
Kammala 1
&
Kammala 2
?
ትናንትና ቮድካው ይቺን ገፁ ላይ ለጠፈ።የወያኔ ማቲ ታርቀዋል ብሎ ከበሮ ደለቀ። Ethioforum ከደላቂ ወያኔዎች አንዱ ነው።
መገናኘቱን ተገናኝተዋል ።መሃከል ላይ ያለው ቅቤ ነው ለማስታረቅ የሞከረው። ሳይስማሙ ነው የተለያዩት።
ግንኙነቱን ከጓዶቹ ተደብቆ በምስጢር ያደረገው ደብረፂዮን ስለግንኙነቱ ሲጠየቅ "ውሸት ነው አልተገናኘንም" ብሎ ጓዶቹን ስለካደ ነው ቮድካው ይቺን የለጠፈው - ያው 'ሲያሳጣው' መሆኑ ነው።
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።
@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna
#ኢትዮጵያ
Last updated 2 months, 3 weeks ago
Last updated 2 months, 2 weeks ago
ይህ ስለ Manchester United መረጃዎችን የሚያገኙበት የ Telegram ቻናል ነው 🇪🇹
--------------------------------------------------------------
☞︎| ስለ ማንቸስተር ዩናይትድ ትኩስ መረጃዎች
☞| ቀጥታ ስርጭቶች ከየስታድየሞቹ
☞| የዝውውር ዜናዎች
☞| ስለ ማንችስተር ዩናይትድ ታሪኮች
📩 ለማስታወቂያ ስራ DM :- @Marcoabdu
Last updated 1 month, 1 week ago