ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።
@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna
#ኢትዮጵያ
Last updated 2 months, 3 weeks ago
Last updated 2 months, 2 weeks ago
ይህ ስለ Manchester United መረጃዎችን የሚያገኙበት የ Telegram ቻናል ነው 🇪🇹
--------------------------------------------------------------
☞︎| ስለ ማንቸስተር ዩናይትድ ትኩስ መረጃዎች
☞| ቀጥታ ስርጭቶች ከየስታድየሞቹ
☞| የዝውውር ዜናዎች
☞| ስለ ማንችስተር ዩናይትድ ታሪኮች
📩 ለማስታወቂያ ስራ DM :- @Marcoabdu
Last updated 1 month, 2 weeks ago
በጃል ቆቱ ዳዲ ( የአገዛዙ ) ካርዶች !
የመጀመሪያው የኢትዮጵያ ሕዝብ ብሔራዊ መዝሙር ግጥም ደራሲ የነበሩት ቀኝ ጌታ ዮፍታሔ ንጉሴ ነገሩ ግራ ቢገባቸው
"ማሽላና ስንዴ በአንድ አብረን ስንቆላ፤
እያረረ ሳቀ የባህር ማሽላ፡፡
ከሰል የሚሆኑ ብዙ እንጨቶች ሳሉ፤
ዝግባ ለምን ይሆን ይቆረጥ የሚሉ፡፡"
በማለት ተቃኝተውት ነበር። ዝግባ ካልቆረጥን የሚሉት አውርቶ አደሮች ግን አቅማችሁን እወቁ እንጅ ! እንደ ሻምፖኝ እያፈናጠሩ ማውራት እኮ እውቀት አይደለም።
በመጀመሪያ Screenshot ወስዶ ለሚንጨረጨርበት Post መልስ/ማብራሪያ አልሰጠኝም ምክንያቱም ሁሉም fact ስለነበሩ ነው። ደግሞ እውቀት ቢጤም ይጠይቃል። እንደ ጅብ መጮህ እኮ እውቀት አይሆንም፤ ያስገምታል እንጅ !
ለማነኛውም መርዙን አንድ ባንድ አስተፋዋለሁ አላልኋችሁም ነበር፤ ገና ምን አይታችሁ አንድ በአንድ እንዲተፋት እና ባዶ ቀፎው እንዲቀር አደርገዋለሁ።
አጀንዳ እጦት ወደ ሰኔ-15/ 2011 ዓ.ም ወደ ኋላ ያስሮጣል ለካስ። በጣም ወደ ኋላ ከሄድህ ጥሩ አይደለም ጃል ዳዲ ሳታስበው 16ኛው ክ/ዘመን ላይ እንዳትደርስ እና ማዳጋስካራዊነትህ እንዳይቀላቀልብህ።
ወደ አጀንዳው እንምጣ:-
ጃል ቆቱ ዳዲ ከብልፅግና የተወረወረለትን አዲሷን ዕቅድ ተንፍሷል። መቼም በራዕይ ታይቶኝ ነው አይለኝም። እንግዲህ እራሱን መምህር፣ ዲያቆን፣ እክሊለ ገብርኤል፣ የድንግል አሽከር... ብሎ የሚጠራው አጭበርባሪው ጃል ቆቱ ዳዲ እንዲህ አስቀምጦታል። ሀተታው እንዲህም ይላል። "አገውና ዐማራ የሚል እሳት ይለኮሳል፤ጠብቁ አልኳችሁ በቅርቡ ይጀምሩታል። እስከ አሁን ዐማራውን ሲገድሉት ዝም ስላለ አሁን አገው እየተመረጠ ይገደላል።" ቃል በቃል የወሰድሁት ነው።
እስካሁን በተከፈለው ልክ ምስራቅ/ምዕራብ ጎጃም ፣ ሚስት አገቡ፣ ሴት ጋር ተኙ፣ አረቄ ጠጡ፣ ሰዓት ለበሱ፣ ሸለሉ፣ ፎቶ ተነሱ፣ መግለጫ ሰጡ፣ 3 backpack ያዙ፣ ሰሜን ጎጃም፣ ስጋ በሉ፣ ፆም አልፆሙም... በማለት የአማራ ፋኖ በጎጃምን ያዳክመዋል ብሎ ያሰበውን ሁሉ ሞክሯል፤ ዳክሯል ሁሉም ካርዶች ግን ፉርሽ ሆኑበት። ክብርና ምስጋና እጅግ በጣም ለሚንቁትና ለሚፀየፉት ንቁ አማራዎች።
አሁን ህወሃት 30 ዓመት ሞክራ ሳታሳከው የተፈነገለችበትን፣ የዘመዶቹ ገዳይ ስብስብ ኦነግ 200 ሚሊዮን ብር መድቦ ቁማር የተበላበትን እና ሰማ ጥሩነህ ደጋግሞ ሞክሮ የከሸፈበትን አጀንዳ አገው/አማራ በማለት ጀምሮታል። ሲመስለኝ አገዛዙ ከጃል ዳዲ ጋር በመተባበር ነፍሰ-ገዳይ ቀጥሮም ቢሆን አንድ እንቁ የፋኖ ታጋይ ማስገደል የሚሞክር ይመስለኛል። ምክንያቱም መስቀል ከሱፉ በላይ አድርጎ የድንግል አሽከር ሲላቸው አምነውት በስልክ የሚያገኙት የተወሰኑ ያልበሰሉ ልጆች ላይጠፉ ይችላሉ። እሱ ራሱ እንደ ገለፀው የድሮውን የኦነግ ምልምልም ሊያገኘው ይችላል። ( በነገራችን ላይ የሰራሁበትን አልከፈልከኝም በሚል ያስገደለው ሚኒስተር እንዳለ ስነግራችሁ በጣም ተገርሜ ነው። ) ዞሮ ዞሮ ፋፃሜው ግን እንደሌሎቹ አጀንዳወች በዝረራ ይሸነፋል። የላሊበላን ልጆች የጃል ዳዲ ዲቢሳ ልጅ ቁማር ሲበላቸው አልታያችሁም🤣* የማይሆነውን !
ጃል ዳዲ ሰርጎ-ገብነትህ አክትሟል ጠቅልለህ ኤርሚያስ ለገሰ ዋቅጅራ ጋር ተባብራችሁ አንድ የቴሌቪዥን ጣቢያ ክፈቱ። ኪራዩን ዳንኤል ክብረት በማህበራዊ ዘርፍ በኩል ይሸፍነዋል። አሁን ጋዜጠኝነት የት/ት ዝግጅት አይጠይቅ፣ ፈተና የለው በቃ መዋኘት ነው እዛው ሽታየ ሽታየ እየተባባላችሁ ትዋኙበታላችሁ።
ጃል ቆቱ ዳዲ ጎጃም ግን እንዴት ይዞሃል? ማርና ቅቤው፣ ማኛ ጤፉ፣ ቅኔ ማህሌቱ ሁሉ ሰላም ነው? እስኪ 3 ጊዜ እግዚአብሔር ይመስገን በል! ደግሞ 7 ጊዜ አታማትብ 3 በቂ ነው ዋ🤣 የገለምሶ ባይገኝም በርጫ እኮ ጎጃም ውስጥም አለ። ጌትነት አልማው ጋር ብትደውል ጥሩ ቦታ ይጠቁምሃል።
ወዳጆቼ ጎጃም ከገባ አይቀር መርዙን አስተፍቸ ፣ ከጮቄ ተራራ አውርጄ፣ ከዲማ ጊዮርጊስ እስከ ጣና ገዳማት አስጎብኝቸ፣ ግሽ አባይ አስጠምቄ፣ አስተምሬ ጥሩ ሰው አድርጌ ነው የማስወጣው። ወንቅሸት ይሁንም ካለ እወስደዋለሁ ምን ገዶኝ። ሙሉ መምህር አድርጌ ነው የማስወጣው ስላችሁ። እሪሪሪ እኔ የበላይ ልጅ !
አሁን ትንሽ የመሠረተ-ትምህርት ለጃል ዳዲ
ጃል ቆቱ -" ምስራቅ-ጎጃም-ቅባት" የሚልበትን መሠረተ ትምህርታዊ ይኸው:-
በመጀመሪያ አማራ ምስራቅ፣ ሰሜን ምናምን የሚባል የለውም፤ ኢትዮጵያ በሙሉ በደሙ ያፀናት አገሩ ናት የሚለውን የአርበኛ ዘመነ ካሴ ንግግር ውሰዱልኝ። እንደ ጃል ቆቱው አስተሳሰብ ደግሞ ምስራቅ ጎጃምን አብዝቶ ይጠላ እና ለሚጠላቸው አመራሮች ጠበቃ ሆነዋል ብሎ የሚከሰን ደግሞ እኛን የምዕራብ ጎጃም ልጆችን ነው። ሲምታታብህ እኮ ከባድ ነው። መምታታት ብቻ አይደለም ዳፋ*ቅህን በእጥፍ አበዛዋለሁ ገና።
ለማነኛውም ቅባት እያለ ለሀጩን ለሚተፋበት ምስራቅ ጎጃም የተወሰነ ላስተምረው ስለሆነ ዘና እያላችሁ አንብቡ።
ርእሰ ርኡሳን መርጡለ-ማርያም ገዳም
ይች ታላቅ እና ጥንታዊት ገዳም የተመሰረተችው ከእስራኤሉ ንጉሥ ሰሎሞን እና ከኢትዮጵያዊት ንግሥት ሳባ (ማክዳ) የተወለደው ቀዳማዊ ምኒሊክ ይዟቸው በመጣ የኦሪት ካህናት በ4500 ዓመተ ዓለም ነው። በወቅቱ የጃል ቆቱ ዳዲ ቅድመ-አያቶች ማዳካስካር ነበሩ። ፓጋንም ነበሩ። ሌላውን እንዲያነብ የቤት ስራ ሰጥቸዋለሁ ይውሰድ። ምስራቅ ጎጃምን በደንብ አውቆ መውጣት አለበት አይደል ወገን?
ዲማ ቅዱስ ጊዮርጊስ ገዳም
በአጼ አምደ ጽዮን ዘመነ መንግሥት በ1297 ዓ.ም የተመሰረተ ገዳም ነው። የፍቅር እስከ መቃብር ደራሲ ክቡር ዶክተር ሐዲስ ዓለማየሁ የተማሩበት እና የመጽሐፋቸው መቼት የሆነ ገዳም ነው ።
ሙሉ ታሪኩን እንዲያነብ የቤት ስራ ተሰጥታል ይውሰድ።
ገዳሙ ሲመሰረት የጃል ቆቱ አያቶች ከማዳካስካር ተነስተው ኬንያ ደርሰው ነበር፤ቢሆንም ፓጋን ነበሩ ምንም የሚታይና ለትውልድ የሚተላለፍ ቅርስ አልነበራቸውም። ወደ ዋሸራ ሄጄ ቅኔ ላዘርፈው ነበር ለዛሬው ይበቃዋል። ቆቱው ይሄን ህዝብ ነው እንግዲህ ቅባት የሚለው።
ለማነኛውም ዝም ተብሎ እንደ ዝንጀሮ ጮቄ ተራራ ላይ ከመውጣት ታሪክንና ሃይማኖትን ጠንቅቆ ማወቅ ጥሩ ነው። አክሊለ ገብርኤል ነኝ ማለት እና ነጠላ ለብሶ 7 ጊዜ ማማተብ ምንድን ነው ፋይዳው? ዘመዶቹ በታቦተ ህጉ ሲሳለቁ ለሚከተሉት ነጠላ ለባሾች ሞራል እንኳን ስለእምነቱ ምን አለ ? ምንም !!
በእግረ መንገድ የ2.5 ሚ ክሷንና ዘር ቆጥሮ ለአለሚቱ ገለታ አንድ ጊዜ ብቻ የከፈለበትን ሰነድ እያያችሁ።
የሸበሉ ነኝ የ Amanuel Abinet ወንድም !
ሰርተህ ብላ !
የጃል ቆቱ ( ጃል ዳዲ ) ጡዘት !
(ከይኸነው የሸበሉ ገጽ)
ደራሲ ከበደ ሚካኤል ተረትና ምሳሌ በሚለው መፅሀፋቸው ላይ ”አውራ ዶሮ ሌሊቱ የሚነጋው የእሱን ድምፅ ሰምቶ እየመሰለው ሲኮፈስ ይኖራል።” የምትል ድንቅ አባባል ፅፈዋል። ይች የአውራ ዶሮ ምሳሌ ጃል ዳዲን በደንብ ትገልፀዋለች።
ወደ ዝርዝር ከመግባቴ በፊት በመስቀልና በነጠላ ተሸፍኖ ለሸቅል ወደ ጎጃም እስከ ፋሲካ ድረስ ገብቻለሁ ያለውን አጭበርባሪ የተደበቀውን መርዙን እንዲተፋ በማድረግ ከፍተኛ ስራ ሰርተናል። ለወደፊትም ጥላው ብቻ እስኪቀረው ድረስ የተደበቀውን ጥላቻውን አደባባይ እንዲያወጣው እናግዘዋለን።
ከሰሞኑ "በአህያ ፈስ አይሳቅም" ብለን ዝም ብንለው ቆቱው ልክ እንደ አውራ ዶሮው እያደረገው ነው አሉኝ። አውራ ዶሮው ያልገባው እሱ ባይጮህም መንጋቱ እንደማይቀር ነው።
ታዲያ ቆቱው ጎጃም ላይ ዝናብ ቢዘንብ፣ ጣና ቢደርቅ፣ አባይ ቢሞላ፣ አውሎ ነፋስ ቢነሳ እራሱ እኔ ነኝ ማለቱ እንደማይቀር ነው የሚከታተሉት ሰወች የነገሩኝ።
የሆነ ፋኖ ደብዳቤ ፃፈ "በእኔ ምክንያት ነው" ፤ ሹመት ሰጠ... ከስልጣን አነሳ... ጥይት ተኮሰ .... ተኛ ...ተራራ ወጣ... ሁሉንም በእኔ ምክንያት ነው ሲል ይውላል አሉኝ። አሄሄ ሚሉሽን " በሰማሽ ገቢያ ባልወጣሽ " ነው ነገሩ።
የሆነው ሆኖ ጃል ዳዲ በስድብ በስድ አፍነት ከብልፅግና ካድሬወች ቢበልጥም በተንኮል እና ምቀኝነት ግን ከእነሱ በምን ተሽሎ ነው የአማራ ፋኖ በጎጃምን እንዲህ በምላሱ ብቻ አፈርሳለሁ ብሎ ቃል የገባው አትሉኝም?
የመጀመሪያዋ በነጠላና መስቀል ስም በማጭበርበር ያከማቻት ተቀባይነት ታግዘኛለች ብሎ አስቦ ነበር። መቸም የዳበረ የፖለቲካ እውቀቴ ፣ ሃርቫርድ ያስተማርሁበት ምናምን አይለን መቼስ። የጃል ዳዲ ድን*ቁርና አሁን ከዳንኤል ክብረት እኩል አክ---እንትፍ እንደተባለ አለመረዳቱ ነው። በእርግጥ አማራን የሚጠሉ አንዳንድ ቆሞ ቀሮች አሁንም ዳንኤል ክብረትን የሚከተሉት እንዳሉ ሁሉ ሌሎች አንዳንድ አማራ ጠሎችና ፌክ ኢትዮጲያኒስቶች ቆቱውን ቢያመልኩበት አይገርመንም፣ አህያ ለአህያ .....ስለሆነ አይደንቅም። ጋን ሙሉ ዝንብ ሞሰብ ስለማይከፍት አያስጨንቅም።
የሰሞኑን የከሸፈውን ድካሙን ጠቅላል አድርጌ ሳየው:-
1ኛ- ምስራቅ/ምዕራብ ጎጃም የሚል የባለስልጣን ቆጠራ ነበር አልተሳካም። አማራ ይሁን እና አቅም ይኑረው እንጅ እንኳን ከምስራቅ ጎጃም ለምን ከምስራቅ ሀረርጌ አይሆንም? የሀረር ኦሮሞ ለምዕራብ ጎጃም አስቦ? ክሽፈትን የተከናነበበት ክሹፍ ሀሳብ።
2ኛ - ሀይማኖት ( ቅባት፣ እስላም፣ ፕሮቴስታንት ...)
ፋኖን ጂሃዲስት አድርጎ ለማሳየትና ከኦርቶዶክስ ሃይማኖት ተከታይ ውጪ ያሉትን ከትግሉ ለማራቅ ይጠቅመኛል ብሎ ተመኝቶ ነበር አልተሳካም። የቆቱው ቤተሰቦች አብዛኞቹ ሙስሊም ቀሪወቹ ደግሞ የፕሮቴስታንት አማኞች ሆነው ሳለ ለምን በዚህ ልክ የሌላ ሀይማኖት ጠል ሆነ ቢባል? ለመከፋፈል ብቻ መሆኑን ሁሉም የነቃበት ጉዳይ ሁኖ አንገቱን አስደፍቶታል።
በጥምቀት በዓል ወቅት የአጎቱ ልጆችና የጃል ዘመዶች በታቦተ ህጉ ላይ ያን ያህል አስተፀያፊ ነገር ሲፈፀም ሳይሰማ ቀርቶ ነው አይደል? አይ ሌቦ😂 ይሄን እንኳን አንስቶ የሚሞግት ነጠላ ለባሽ አገልዳሚዎቹ የት ገቡ ?
3ኛ - በአመራሮች መከካል ጥርጣሬን መፍጠር ሞክሮ ነበር ይሄም ከሽፏል። ከበታች አመራሮች ጀምሮ እስከ አርበኛ ዘመነ ካሴ ድረስ በደረጃ መርዙን ተፍቶባቸዋል ግን ወፍ የለም። በተለይ የጥምቀት በዓል ዕለት በደብረ ብርሃን ፣ ደብረ ታቦር፣ ወልዲያ ፣ ጎንደር እና ሌሎችም አካባቢወች ወጣቶች "ዘመነ ካሴ" ብለው ጨፈሩ ብሎ "የደብረ ብርሃን ሰው ስለ ዘመነ ምን አገባው" ብሎ ሲንጨረጨር ያዬ ሰው አሁንም እንደ ጤነኛ ቆጥሮት ከሆነ አዝናለሁ። የአማራው መናገሻ የሸዋ ሰው ፣ የደብረ ብርሃን ሰው እንዴት ስለ ዘመነ ምን አገባው ይባላል? የአርበኞች ምድር የእናታለም ጎንደር ሰው እንዴት ለአማራይቱ ልጅ ለዘመነ ካሴ አያገባህም ይባላል?
4ኛ - የአማራ ፋኖ በጎጃምን በገንዘብ አትደግፉ የሚል ቅስቀሳ ማካሄድ። አገዛዙ 24/7 የሚሰራው ስራ ነው። በእርግጥ ድሮም አሁንም ትግሉን በገንዘብ የሚደግፉት የእሱ ዘመዶች አይደሉም። አሁን ፋኖ ስንቁንም ትጥቁንም ከጃል ጫላ ያገኛል፣ የነቁ አማሮችና የትግሉ ደጋፊ ማህበረሰብ ድጋፉን ይቀጥላል። በእኔ ምክንያት ድጋፍ ቆመ ፣ የሚበላው ሲያጣ ፋኖ ይበተናል ተብሎ ግን በደስታ ጮቤ የሚያስረግጥ ጉዳይ የለም፤ አይኖርምም።
5ኛ - የአማራ ፋኖ በጎጃምን ወንጀለኛ ድርጅት አድርጎ በማሳየት በኦሮሞው ማስጠላት።
ቦታው ላይ ያለው የአማራ ህዝብ እንደሆነ እውነቱን ያውቀዋል። በዚህ አጀንዳ ላይ ዋነኛ የውሸት ክስ መረጃ ሰጪወች ደግሞ የእስክንድሩ ጋሻ ሚዲያ እና የብርሌው ቲም መሆኑ ያስቃል። ለምን የክስ ጃርጅ ይዘህ አጎትህ አብይ አህመድ ጋር አትሄድም? በቃ ዘመዶቹ የረሸ*ኗቸውም፣ በጦር ሜዳ የተሰው፣ እርምጃ የተወሰደባቸው የአገዛዙ ደህንነቶች፣ ካድሬወች እና ሰላዮችን ስም ዝርዝር ጭምር ከወንደሰን ተክሉ ተቀብሎ በኪሱ ይዞ መዞር ከጀመረ ቆይቷል አሉኝ። በፎቶ ፍሬም አድርገህ የቤትህ ግድግዳ ላይ ስቀለውና እንዴት ድርሰት እንደምትችል ለራስህ ተደመምበት በሉልኝ።
6ኛ - ስራ ብሎት በአገዛዙ ጨፍ*ጫፊ ሰራዊት በአማራ ላይ የሚፈፀሙ ወንጀሎች በቂ የሚዲያ ሽፋን እንዳይኖራቸው የተለያዩ አጀንዳወችን መፍጠር አሁን ከአገዛዙ ደሞዝ የሚያገኝበት በ55 ዓመቱ የመጀመሪያው ስራው ሆኗል። ይሄም አባይን በጭልፋ እንደማለት ነው። Amnesty international ጭምር እየዘገባቸው ያሉት በአገዛዙ የሚፈፀሙ ወንጀሎች ለጃል ዳዲ normal ናቸው። ዘመዶቹንማ አሳልፎ አይሰጣቸውም። እንዴት ተደርጎ እንዴ !
አማራ ንስር ነው፤ ቁራወች የማይደርሱበት ከፍታ ላይ ተሰቅሏል !
ሰርተህ ብላ !
በራያ ቆቦ ግንባር አስደናቂ ጀብዱ ተፈፅሞ ዋለ::
የ802ኛ ኮር 58ኛ ክፍለጦር ከፍተኛ አመራሮችን ጨምሮ በመቶዎች የሚቆጠሩ ወታደሮች አልቀዋል::
የአማራ ፋኖ በወሎ (ቤተ-አምሓራ) ምስራቅ አማራ ኮር ፩ አሳምነው ክፍለ ጦር እና ሃውጃኖ ክፍለ ጦር በጋራ ራያ ቆቦ ዞብል እና ራማ በብረት ለበስ እና በአራት ዙ23 እንዲሁም በሞርተርና መድፍ በመካናይዝድ ታግዞ የመጣውን የጠላት ሰራዊት በከባድ የፀረ ማጥቃት ዉጊያ አሽመድምደውት የሞተው ሞቶ ቀሪው በአዲስ ቅኝ እና ጎለሻን አድርጎ ገሚሱ ወደ ራያ አላማጣ ዋጃ ከተማ እና ገሚሱ ወደ ራያ ቆቦ ጮቢ በር ፈርጥጧል::
የምስራቅ አማራ ኮር1 አሳምነው ክፍለጦር እና ሃውጃኖ ክፍለጦር በጋራ በሰሩት በዚህ ተጋድሎ የ58ኛ ክፍለጦር ከፍተኛ አመራሮችን ጨምሮ በመቶዎች የሚቆጠሩ ወታደሮች እንደሞቱና እንደቆሰሉ ተረጋግጧል::
የቀድሞው 8ኛ ዕዝ የአሁኑ ሰሜን ምስራቅ ዕዝ 48ኛ 49ኛ እና 58ኛ ክፍለጦሮች እንዲሁም ከምስራቅ ዕዝ 12ኛ ክፍለጦርን ጨምሮ ሙትና ቁስለኛ እንዲሁም ምርኮኛ ሆነው ተበታትነው ያለቁበት ሁኔታ ነው ያለው::
በዚህ እልክ አስጨራሽ የሞት የሽረት ተጋድሎ በጀግኖቹ ተጋድሎ ያለዉን ሁሉ ተጠቅሞ ሽንፈት የገጠመው ጠላት እንደተለመደው ንፁሃንን ኢላማ ያደረገ የከባድ መሳሪያ ድብደባ እየፈፀመ ዉሏል:: ድንጋይ ቀበሌ አዲስ ቅኝ እና ኮባ ቀበሌዎች በከባድ መሳሪያ በሰው ህይወት በእንስሳቶችና በንብረት ላይ ከፍተኛ ጉዳት አድርሷል:: ከዚህ ጋር ተያይዞም ከራያ ቆቦ ሮቢት በምዕራብ በኩል ባሉ የገጠር ቀበሌዎች ንፁሃንን ኢላማ ያደረገው የከባድ መሳሪያ ድብደባ ሲፈፀም ዉሏል ሲል የአማራ ፋኖ በወሎ (ቤተ-አምሓራ) አስታውቋል::
ሰበር | የቀኝ አዝማች ይታገሱ አረጋው ተወርዋሪ ክፍለ ጦር እና የአትሮንስ ብርጌድ ፋኖዎችን ለማፈን የመጣው ጠላት 30 ፕርሰንት ኃይሉን ወዥድ ቀበሌ ውስጥ ተነጥቋል:: ክትክታዎቹ የይታገሱ ልጆች ጠላትን በጎመኔ ጥይት ጠቅ ጠቅ አደረጉት:: ቻው ቼልሲ!! ነገ እድሩ ቢዚ ሆኖ ይውላል!!
ተወርዋሪ ክፍለ ጦሩ በአማራ ፋኖ በወሎ ምዕራብ ወሎ ኮር ጠቅላይ አዛዥ አርበኛ አደም አሊ እና በአ/ሳይንት መቅደላ ክፍለ ጦር አስተዳደር + የአትሮንስ ብርጌድ አዛዥ በሆነው ፋኖ ጎሹ ሳይንቴው የበላይ ጠባቂነት ብሎም አማካሪነት የሚንቀሳቀስ የነብር ስብስብ ሲሆን ውጊያ እንጅ ወግ ስለማይችሉ ብቻ ማንም በሚዲያ እየወጣ የሉም እያለ ይቀደዳል::
ክፍለ ጦሩ ከተመሰረተ ሳምንት ሳይሆነው ጥቅምት 24 ቀን ከአትሮንስ ብርጌድ አናብስት ጋር በመቀናጀት በፋኖ ጎሹ ሳይንቴው እና በፋኖ በለጠ አከለ አዋጊነት ቀበሮ ሜዳ ላይ ተመሳሳይ ታሪክ ሰርቶ አስደምሞናል:: ይህ ክፍለ ጦር ተስፋ የጣልንበት ክፍለ ጦር እንጅ ማንም አፉን የሚከፍትበት መሸታ ቤት አይደለም!!
የንፁሁ ወንድማችን የደም አሻራ ነው:: የወንድማችንን አደራ ከጠብመንጃ ጋር ተሸክመው በሚዞሩ ሀቀኛ ጀግኖች የተመሰረተ ክፍለ ጦር ሲሆን ከጃማ እስከ ሳይንት ድረስ የተመረጡ ተዋጊዎችን ያቀፈ ነው:: የጃማን ችስቻሶ በልተው ያደጉት እነ ኮማንዶ ቻይና ሹመት እና ፋኖ አዲስ ሙሀመድን ጨምሮ የመሀል ሳይንቱ ዝነኛ ጀግና ፋኖ በለጠ አከለ የሚመራው የጀግና መንጋን የያዘ ክፍለ ጦርን ልለፋደድበት የሚል ሰው ካለ አንገቱ ላይ እባብ መጠምጠም የፈለገ ነው::
የእስካሁኑ የምላስ ወለምታ ነው ተብሎ ታልፏል:: ወደፊት ግን ደም ነው የሚያስተፉት!!
ይታገሱ አልሞተም!!
በስሙ ታሪክ እየተሰራ ነው::
"ውጣና ታገል...እኛ እየታገልን ነው አግዙን..እምቢ ካላችሁ ግን ለምሳሌ እኔ የምሞተው አንዴ ነው የአማራ ህዝብ ግን ተደጋጋሚ ሞት ይሞታል:: ከተደጋጋሚ ሞት ህዝባችንን ለመታደግ በአንድነት ተነስተን እንታገልና ጠላታችንን አሸንፈን ሰላማችንን በጉልበት አውጀን እፎይ እንበል!!"
(የአማራ ፋኖ በወሎ ዘመቻ መምሪያ ኃላፊ ፋኖ በለጠ ሸጋው በአንድ ወቅት ከተናገረው)
የቡልጋው ከሰም ክፍለ ጦር የምስራች አሰምቶናል::
የዚህ የምስራች ይዘት ምን እንደሆነ በዝርዝር ትሰሙታላችሁ!
የደጀኑ ዛምብራ ብርጌድ አስደማሚ ተጋድሎ መፈፀሙ ተገለጸ:: በደጀን ግምባር ስለተፈጠረው ሁኔታ ከስፍራው ያገኘነውን መረጃ በዝርዝር ዜና መርሀግብራችን ከአፍታ ቆይታ በኋላ እናስደምጣችኋለን
እነማይ እና እናርጅ እናውጋ ውስጥ ብዛት ያለው የመንግስት ጥምር ጦር ክፉኛ መመታቱ ታወቀ!!
ከስፍራው የደረሰንን መረጃ በቆይታችን እንዳስሰዋለን
ከደብረማቆስ የተሰማ አዲስ ዜና አለ:: በዚህ ዙሪያ የጎርጎራ ቲቪ ምንጮች የላኩልንን መረጃ እናስደምጣችኋለን::
ምዕራብ ወሎ ውስጥ በመሐል ሳይንት ግምባር አዲስ ነገር ተፈጥሯል ሲሉ የጎርጎራ ምንጮች ገልፀዋል። ይህንንም በተመለከተ ዝርዝሩን እናስደምጣችኋለን
የአማራ ፋኖ በወሎ ዞብል አምባ ክፍለ ጦር ራያ ቆቦ ተኩለሽ ዙሪያ በአይነቱ ልዩ የሆነ ኦፕሬሽን መስራቱ ታወቀ:: ዝርዝሩን ትሰሙታላችሁ::
የኦሮሚያ ተወላጆች የሆኑ ምልምል የመከላከያ ሰራዊት ሰልጣኞች ቤተሰቦች የስልጠና ወጭ እየከፈሉ ልጆቻቸውን መውሰዳቸው ተነገረ
የአማራ ዘር ፍጅት ይቁም በሚል መፈክር በተለያዩ የአለም ሀገራት ከተሞች ውስጥ ሰላማዊ ሰልፍ ተደረገ:: የለንደን ፋኖ ታሪክ ሰርቷል::
በእነዚህና በሌሎች ርእሰ ጉዳዮች ዙሪያ የጎርጎራ ቲቪ የዜና መሰናዶ በፋኖ ብሩክ ታደሰ ግዮናዊ ከደቂቃዎች በኋላ ይቀርባል::
እስከዚያው በዚህ ሊንክ ገብታችሁ ጠብቁ::
https://youtu.be/3nrnHI7Todc
ጎርጎራ ሳተላይት ቴሌቪዥን
ከእውነት ጋር!!
ምስራቅ ጎጃም ተጨማሪ በላይ ዘለቀዎችን እያፈራች ነው::
አርበኛ በላይነህ ዋልተንጉሥ ይባላል፤ የአማራ ፋኖ በጎጃም በላይ ዘለቆ ክፍለ ጦር ራስ (ሰብሳቢ) ነው:: የደጀኑ ዛምበራ ብርጌድ አንበሳ እና የጉበያ በርሀ ዳኛም ነው::
የበላይ ጥሪታችን ብለን እንጠራዋለን። በዚሁ በምስራቅ ጎጃም ግምባር ብዙ አባ ኮስትሮች አሉ።
አርበኛ እና ጠበቃ አስረስ ማረ፣ አርበኛ ጥላሁን አበጀ፣ አርበኛ በላይነህ ዋልተንጉሥ፣ ፋኖ ይበልጣል ጌቴ፣ ፋኖ ባዬ ደስታ፣ ፋኒት ትዕግስት ጫንያለው፣ ፋኖ ጥጋቡ፣ መቶ አለቃ ውዳለው፣ ሀምሳ አለቃ ዮሴፍ፣ አስር አለቃ ግዛቸው፣ ኮማንዶ መንበር፣ ኮማንዶ ግዛቸው፣ ፋኖ ምስጋናው፣ መ/አ አዳነ፣ ፋኖ ደምሰው ታመነ፣ ፋኖ አባይነህ፣ ሻለቃ መንበሩ እና የመሳሰሉት የምስራቅ ክዋክብት ከሞት አይፈሬው ሰራዊታቸው ጋር በሶማ እና ጉበያ፣ በአራጢ ጫካ ብቻ ሳይሆን በመሀል ከተማ ይንጎባለላሉ።
ጀግኖች ወንድሞቻችን፤ ከአባይ በርሀ እስከ አረፋ ዳሞት ድረስ ተምዘግዝገው የአባ ኮስትርን ታሪክ በጥይት እርሳስ ደግመው እየጻፉት ነው።
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።
@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna
#ኢትዮጵያ
Last updated 2 months, 3 weeks ago
Last updated 2 months, 2 weeks ago
ይህ ስለ Manchester United መረጃዎችን የሚያገኙበት የ Telegram ቻናል ነው 🇪🇹
--------------------------------------------------------------
☞︎| ስለ ማንቸስተር ዩናይትድ ትኩስ መረጃዎች
☞| ቀጥታ ስርጭቶች ከየስታድየሞቹ
☞| የዝውውር ዜናዎች
☞| ስለ ማንችስተር ዩናይትድ ታሪኮች
📩 ለማስታወቂያ ስራ DM :- @Marcoabdu
Last updated 1 month, 2 weeks ago