ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።
@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna
#ኢትዮጵያ
Last updated 2 months, 3 weeks ago
Last updated 2 months, 2 weeks ago
ይህ ስለ Manchester United መረጃዎችን የሚያገኙበት የ Telegram ቻናል ነው 🇪🇹
--------------------------------------------------------------
☞︎| ስለ ማንቸስተር ዩናይትድ ትኩስ መረጃዎች
☞| ቀጥታ ስርጭቶች ከየስታድየሞቹ
☞| የዝውውር ዜናዎች
☞| ስለ ማንችስተር ዩናይትድ ታሪኮች
📩 ለማስታወቂያ ስራ DM :- @Marcoabdu
Last updated 1 month, 1 week ago
ተቋሙ ባለፉት ስድስት ወራት በስርቆት ከ126 ሚሊዮን ብር በላይ ጉዳት ደርሶበታል
.........///…......
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በ2017 በጀት ዓመት የመጀመሪያዎቹ ስድስት ወራት በኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ ምሰሶ ብረቶችና ሽቦዎች ስርቆት ምክንያት ከ126 ሚሊዮን ብር በላይ ጉዳት እንደደረሰበት በተቋሙ የኃይል መሰረተ ልማት ደህንነት፣ ክትትልና ቁጥጥር ቢሮ ገለጸ።
የቢሮው ሥራ አስኪያጅ አቶ ዋለ ታምሬ እንደገለጹት በኃይል ማስተላለፊያ መሠረተ ልማቶች ላይ የሚፈፀሙ የስርቆት ወንጀሎች የተቋሙ ብቻ ሳይሆን የብሔራዊ ደህንነት ስጋት ሆነዋል።
ባለፉት ስድስት ወራት በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች 16 የከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ ተሸካሚ ምሰሶዎች በስርቆት ምክንያት መውደቃቸውን እና በስርቆቱ ከ92 ነጥብ 32 ሚሊዮን ብር በላይ ግምት ያላቸው 43 ሺ 671 ብረቶች መሰረቃቸውንም ተናግረዋል።
የወደቁ የኃይል ማስተላለፊያ ተሸካሚ ምሰሶዎችንና የተሰረቁ የኮንደክተር ሽቦዎችን መልሶ ለመተካት ከ34 ነጥብ 35 ሚሊዮን ብር በላይ ወጭ መደረጉን የጠቆሙት አቶ ዋለ ባለፉት በስድስት ወራት ብቻ በስርቆቱ ምክንያት ሳይሸጥ የባከነውን ኃይል ሳይጨምር ተቋሙ በአጠቃላይ ከ126 ነጥብ 81 ሚሊዮን ብር በላይ ጉዳት እንደደረሰበት ተናግረዋል።
እንደ አቶ ዋለ ገለፃ በበጀት ዓመቱ ከባለድርሻ አካላት ጋር በትብብር ሠፊ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራዎች በመከናወናቸው ምክንያት በኃይል ማስተላለፊያ ተሸካሚ የብረት ምሰሶዎች ላይ ይፈፀሙ የነበሩ የስርቆት ወንጀሎች ካለፉት ዓመታት ተመሳሳይ ወቅቶች ጋር ሲነጻጸር መቀነስ አሳይቷል፡፡
የችግሩን አሳሳቢነት በመረዳት ይበልጥ ተደራሽ ለመሆን ተቋሙ በ2017 በጀት ዓመት የኃይል መሰረተ ልማት ደህንነት፣ ክትትልና ቁጥጥር የሥራ ክፍልን አቋቁሞ ወደ ሥራ መግባቱንም ሥራ አስኪያጁ አስታውሰዋል።
የሥራ ክፍሉን በቁሳቁስና በሰው ኃይል ለማደራጀት እየተሰራ እንደሆነና በክልል ከተሞች ጭምር መዋቅሩን ለመዘርጋት በቅጥር ሂደት ላይ እንደሚገኝም ነው የተናገሩት፡፡
የክፍሉ መደራጀት በሁሉም የሀገሪቱ ክፍሎች የሚገኙ የማህበረሰብ ክፍሎች የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ ምሰሶዎችን በባለቤትነት ስሜት እንዲጠብቁ የሚያስችል ሠፊ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራዎችን ለመስራት እንደሚያግዝ ገልጸዋል።
በአሁኑ ወቅት በግንባታ ላይ የሚገኙ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ፕሮጀክቶችን ሳይጨምር በተቋሙ 41 ሺ 747 የኃይል ማስተላለፊያ ተሸካሚ ምሰሶዎች በኦፕሬሽን ላይ ይገኛሉ፡፡
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia
ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ጥር 19 ቀን 2017 ዓ.ም
ምርታማነትን ለማሳደግ ምቹ የሥራ ከባቢ መፍጠር ያስፈልጋል
....//....
ለኃይል ምርታማነት ምቹ የስራ ከባቢን መፍጠር ላይ ትኩረት ሰጥቶ እንደሚሰራ የኃይል ማመንጫዎች ኦፕሬሽን ዘርፍ አስታወቀ።
በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማመንጫ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን ዘርፍ የ2017 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ስድስት ወራት ዕቅድ አፈጻጸሙን በአዳማ ከተማ ገምግሟል።
በግምገማው ወቅትም የተሽከርካሪ፣ የመለዋወጫ ዕቃዎችና የሥራ ላይ መሣሪያዎች እጥረት፣ የደመወዝና ጥቅማ ጥቅም፣ የሠራተኞች ደህንነትን ከማረጋገጥ፣ የመኖሪያ ቤት ካለመሟላት እንዲሁም ከትምህርት ቤትና የህፃናት ማቆያ በበቂ ሁኔታ አለመኖር ጋር በተያያዘ የተነሱ ችግሮች እልባት እንዲሰጣቸው በጣቢያዎቹ የሥራ ኃላፊዎችና በሠራተኛ ማህበር የዘርፉ ተወካዮች በኩል ተጠይቋል።
በተጨማሪም በተቋሙ እየተከናወነ ስላለው የመዋቅር ማሻሻያ ሥራ፣ ከደረጃ ዕድገትና ዝውውር፣ ከጣቢያዎች የሠው ኃይል አደረጃጀትና የሠራተኛ እጥረት፣ ከመሬት ይዞታ ማረጋገጫ፣ ከመድኃኒትና ከሠራተኞች የደንብ ልብስ አቅርቦት እንዲሁም ከ"ፒቲ ካሽ" በጀት አመዳደብ ጋር በተያያዘም ጥያቄዎች ተነስተዋል፡፡
ለተነሱ ጥያቄዎች ማብራሪያ የሰጡት የዘርፉ ሥራ አስፈፃሚ አቶ እያየሁ ሁንደሳ ተቋሙ የተጣለበትን ተልዕኮ በአግባቡ እንዲወጣ ለሠራተኞች ምቹ የሥራ ከባቢ መፍጠር ያስፈልጋል ብለዋል።
በዚህም የማመንጫ ጣቢያ ሠራተኞችን ደረጃ ከማሻሻል ጀምሮ የመለዋወጫ ዕቃዎችን፣ የደንብ ልብስ፣ የደመወዝና የጥቅማ ጥቅም ጥያቄዎችን ለመመለሰ እየተሰራ እንደሆነም አስረድተዋል።
በቀጣይ በኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች ለሚስተዋሉ ችግሮች ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመነጋገር መፍትሔ በመስጠት ሠራተኛው ተረጋግቶ ሥራውን የሚያከናውንበትን ምቹ የሥራ ከባቢ ለመፍጠር ትኩረት ተሰጥቶ እንደሚሰራም ነው ሥራ አስፈፃሚው የተናገሩት።
በተቋሙ ተግባራዊ እየተደረገ ያለው የመዋቅር ማሻሻያ ሥራ ተቋማዊ ለውጥ ለማምጣትና ስትራቴጅክ ዕቅዱን ለማሳካት እንደሚያስችል የገለፁት አቶ እያየሁ ሠራተኛው በመዋቅር ማሻሻያው ሳይረበሽ ሥራው ለይ ትኩረት በማድረግ ኃላፊነቱን በአግባቡ መወጣት እንደሚኖርበትም አሳስበዋል።
የአሠራር ሥርዓትን ለማዘመን እየተተገበረ ያለውን ሳፕን ጨምሮ በበጀት አጠቃቀም፣ በዕቅድና ሪፖርት አዘገጃጀት፣ በሠራተኞች አቅም ግንባታ እና እውቀት ሽግግር ላይ በትኩረት እንዲሰራ ሥራ አስፈፃሚው አቅጣጫ አስቀምጠዋል።
በዕለቱ የተቋሙን ዋና ሥራ አስፈፃሚ ወክለው መልዕክት ያስተላለፉት በዋና ስራ አስፈፃሚ ጽ/ቤት የዶክመንቴሽንና አስተዳደራዊ ጉዳዮች ቢሮ ሥራ አስኪያጅ አቶ ዋለ ታምሬ በበኩላቸው ሠራተኛው ዘርፉ ለተቋሙ የጀርባ አጥንት መሆኑን ተገንዝቦ የተሰጠውን ሥራ በአግባቡ ማከናወን እንደሚጠበቅበት አስታውቀዋል።
ከደመወዝ፣ ከተሽከርካሪ እጥረት፣ ከደረጃ እድገትና ዝውውር እንዲሁም ከአደረጃጀት ጋር በተያያዘ የሚነሱ ጥያቄዎች እየተከናወነ ባለው የመዋቅር ማሻሻያ መፍትሔ እንደሚሰጣቸው የጠቆሙት አቶ ዋለ ማሻሻያው በሠራተኛው ኽልውና ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ እንደማያሳድርም አረጋግጠዋል።
በቀጣይ በወጭ ቅነሳ፣ ምቹ የሥራ ከባቢ ፈጠራ፣ ክፍት ቦታዎችን በጓሮ አትክልት ማልማት እንዲሁም ሥራን በአግባቡ ለመፈፀም ራስን ማዘጋጀትና ማብቃት ላይ ትኩረት ሰጥቶ መስራት እንደሚገባ ዋና ሥራ አስፈፃሚው ማሳሰባቸውን አቶ ዋለ ተናግረዋል።
ተቋሙ ባለፉት ስድስት ወራት 13 ሺ 517 ነጥብ 6 ጊጋ ዋት ሠዓት ኃይል በማምረት የዕቅዱን 115 ነጥብ 6 በመቶ አፈፃፀም ማስመዝገቡን በግምገማው ወቅት ተገልጿል።
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia
ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ጥር 17 ቀን 2017 ዓ.ም
ክልሉ ለተቋሙ አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግ ገለጸ፤
...//...
የቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ለሚያከናውናቸው የኃይል መሰረተ ልማት ሥራዎች አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግ ገለጸ።
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሥራ ኃላፊዎች ከቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል አመራሮች ጋር የአሶሳ ማከፋፈያ ጣቢያ የመሬት ይዞታ ለውጥን በተመለከተ ውይይት አድርገዋል።
በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን ዘርፍ የሪጅኖች ማስተባበሪያ መምሪያ ዳይሬክተር አቶ ጋሻው እንድሪያስ እና የንብረት አስተዳደር መምሪያ ዳይሬክተር አቶ ከሊል ሽፋ ከማከፋፋያ ጣቢያው የመሬት ይዞታ ለውጥ ጋር ተያይዞ በተቋሙ በኩል የሚነሱ ቅሬታዎችንና የማከፋፈያ ጣቢያው የኃይል አቅርቦት በተመለከተ ገለፃ አድርገዋል።
የሥራ ኃላፊዎቹ በገለጻቸው የመሬት ይዞታ ለውጡ በአሶሳ ማከፋፈያ ጣቢያ ላይ በሚከናወነው የማስፋፊያ ሥራ፣ በጣቢያው ደህንነት እና በኃይል አቅርቦቱ ላይ ችግሮችን የሚያስከትል መሆኑን ጠቁመዋል፡፡
የአሶሳ ከተማ ከንቲባ አቶ አብዱልካሪም አብዱራሂም የመሬት ይዞታው ለውጥ በከተማው እየተካሄደ ካለው የኮሪደር ልማት ጋር ተያይዞ የተከሰተ መሆኑንና ለማከፋፈያ ጣቢያውም ምትክ መሬት እንደሚሰጥ ተናግረዋል፡፡
የርዕሰ መስተዳድሩ የመሠረተ ልማት ዘርፍ አማካሪ አቶ አበራ ባያታ በበኩላቸው ከታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ - አሶሳ ለሚዘረጋው የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ግንባታ እና በነባሩ የአሶሳ ማከፋፈያ ጣቢያ ውስጥ ተቋሙ ለሚያከናውናቸው የማስፋፊያ ሥራዎች የክልሉ መንግስት ተገቢውን ክትትልና ድጋፍ እንደሚያደርጉ አስታውቀዋል።
የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጌታሁን አብዲሳ በውይይቱ ወቅት እንደተናገሩት ከማከፋፈያ ጣቢያው የመሬት ይዞታ ለውጥ ጋር ተያይዞ እየተነሱ ያሉ ቅሬታዎች በግንኙነትና በመረጃ ክፍተት የተፈጠሩ ናቸው፡፡
ለክልሉ ሁሉን አቀፍ እድገት የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማት ወሳኝ መሆኑን የገለጹት አቶ ጌታሁን ከተቋሙ ጋር በትብብርና በቅንጅት ለመስራት ዝግጁ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡
ክልሉ ከተቋሙ ጋር በቅርበት ተባብሮ ለመስራት አሶሳ ከተማ ውስጥ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ቢሮ እንዲያደራጅ ምክትል ፕሬዝዳንቱ ጥሪ አቅርበዋል።
? "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia
ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ጥር 14 ቀን 2017 ዓ.ም
ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባው የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክቱን ጎበኙ
.........///.........
የደሴ ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ እና የደሴ ከተማ የንግዱ ማኅበረሰብ አባላት በከተማዋ የተጀመረውን ባለ 230/33/15 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ጎበኙ፡፡
ፕሮጀክቱ ከማከፋፈያ ጣቢያ ግንባታ በተጨማሪ 5 ነጥብ 6 ኪሎ ሜትር ርዝመት ያለው የማስተላለፊያ መስመር ዝርጋታን ያካትታል፡፡
1 ነጥብ 6 ቢሊየን ብር በጀት የተመደበለትን የማከፋፈያ ጣቢያ ግንባታ እና የማስተላለፊያ መስመር ዝርጋታ በሁለት ዓመት ተኩል ጊዜ ውስጥ ለማጠናቀቅ ዕቅድ ተይዞለታል፡፡
የፕሮጀክቱ ግንባታ በኢትዮጵያ አሌክትሪክ ኃይል የራስ ኃይል ግንባታ መምሪያ የሚከናወን ሲሆን በአሁኑ ወቅት የማከፋፈያ ጣቢያው አጥር እና የትራንስፎርመር ማስቀመጫ መሰረቶች ግንባታ በመከናወን ላይ ይገኛል፡፡
የከተማዋ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባው ሳሙኤል ሞላልኝ ከጉብኝቱ በኋላ እንደተናገሩት የማከፋፈያ ጣቢያው የከተማውን ህዝብ የረጅም ጊዜ ጥያቄ የሚመልስ ነው፡፡
ግንባታው ሲጠናቀቅ የከተማዋን የኃይል መቆራረጥ ከማስቀረት ባለፈ ለከተማዋ አጎራባች ለሆኑ የአማራና የአፋር
ክልሎች ወረዳዎች ተጨማሪ ኃይል ለማቅረብ ያስችላል፡፡
? "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia
ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ጥር 09 ቀን 2017 ዓ.ም
ኢትዮ-ኤሌክትሪክ ፋሲል ከነማን አሸነፈ
........///.......
በ7ኛ ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታ ኢትዮ-ኤሌክትሪክ ፋሲል ከነማን ገጥሞ 3 ለ 2 በሆነ ውጤት በማሸነፍ ሁለተኛ ተከታታይ ድሉን አስመዝግቧል።
ሁለቱ ቡድኖች በድሬዳዋ ስቴዲየም ዛሬ ባከናወኑት ጨዋታ አቤል ሀብታሙ፣ ናትናኤል ገ/ጊዮርጊስ እና ያሬድ የማነ ለኢትዮ-ኤሌክትሪክ ሶስቱን የማሸነፊያ ጎሎች አስቆጥረዋል።
ፋሲል ከነማን ከሽንፈት ያልታደጉትን ሁለት ጎሎች አንጋፋው አጥቂ ጌታነህ ከበደ ከመረብ አሳርፏል።
ብርቱ ፉክክር በታየበት የሁለቱ ቡድኖች ጨዋታ ኢትዮ-ኤሌክትሪክ በመስመር ላይ የተመሰረተ የማጥቃት እንቅስቃሴ ሲከተል ፋሲል ከነማ በአንፃሩ ኳስን በመቆጣጠር የጨዋታ ብልጫ ለመውሰድ ቢሞክርም ሳይሳካለት ቀርቷል።
ውጤቱን ተከትሎ ኢትዮ-ኤሌክትሪክ በ12 ነጥብ በሊጉ አራተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል።
? "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ;
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia
ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com:/@ethiopowermedia
ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ጥቅምት 26 ቀን 2017 ዓ.ም
የሁለቱ ተቋማት አመራሮች የደዴሳ ማከፋፈያ ጣቢያን ጎበኙ
........///..........
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይልና የፌደራል ፖሊስ አመራሮች የደዴሳ ባለ 500 ኪሎ ቮልት የማከፋፈያ ጣቢያን ዛሬ ጎብኝተዋል።
በጉብኝቱ ወቅት የፌዴራል ፖሊስ የምዕራብ ኦሮሚያ አዛዥ ኮማንደር ማሙዬ አባተ እንዳሉት የተቋሙ አመራሮች በግዳጅ ላይ ያሉትን የሠራዊት አባላት መጎብኘታቸው ለሠራዊቱ አባላት የሞራል ጥንካሬ ይሰጣል።
ማከፋፈያ ጣቢያው በረሃማ ቦታ ላይ የሚገኝ በመሆኑ የውሃ አቅርቦት እንዲስተካከል እና የወባ መከላከያ አጎበር እንዲሰጣቸው እንዲሁም የጥበቃ ማማ እንዲገነባላቸው ጠይቀዋል።
በተቋሙ የዋና ሥራ አስፈፃሚ ጽ/ቤት የመሠረተ ልማት ደህንነትና ቁጥጥር ቢሮ ሥራ አስኪያጅ አቶ ዋለ ታምሬ እንደተናገሩት ተቋሙ ከፌደራል ፖሊስና ከህብረተሰቡ ጋር በመሆን የመሠረተ ልማት ስርቆትን ለመከላከል በትኩረት እየሰራ ይገኛል።
በሠራዊቱ አመራሮች ለቀረቡት ጥያቄዎች ተገቢውን ምላሽ ለመስጠት ከሚመለከታቸው የሥራ ክፍሎች ጋር እንደሚነጋገሩም ገልፀዋል።
በተቋሙ የንብረት አስተዳደር መምሪያ ዳይሬክተር አቶ ከሊል ሽፋ በበኩላቸው ለጥበቃ ምቹ ሁኔታ ለመፍጠር የንብረት ማስቀመጫ መጋዘን ለመገንባት መታቀዱንና ያልተሟሉ ፋሲሊቲዎችን ከሚመለከታቸው የሥራ ክፍሎች ጋር በመነጋገር ለመመለስ ጥረት እንደሚደረግ አረጋግጠዋል።
? "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ;
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia
ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com:/@ethiopowermedia
ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ጥቅምት 26 ቀን 2017 ዓ.ም
የተቋሙ አመራሮችና ሠራተኞች ደም ለገሱ
………///………
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አመራሮችና ሠራተኞች በተቋሙ ዋና መሥሪያ ቤት የደም ልገሳ ዛሬ አካሂደዋል፡፡
የደም ልገሳ መርሃግብሩ በተለያዩ ምክንያቶች ደም ለሚያስፈልጋቸው የህብረተሰብ ክፍሎች እንዲውል ታስቦ የተዘጋጀ ነው፡፡
ደም ሲለግሱ ያገኘናቸው የተቋሙ የፋይናንስ ሥራ አስፈጻሚ አቶ ደመረ አሰፋ እንደገለፁት በተቋሙ ዋና መ/ቤት የደም ልገሳ ፕሮግራም መዘጋጀቱ የሠራተኛው የሥራ ሰዓት ከመቆጠቡም በላይ ደም ለመስጠት ፈልገው በተለያዩ ምክንያቶች ወደ ኢትዮጵያ ደም እና ህብረህዋስ አገልግሎት ለመሄድ ያልቻሉትን ሠራተኞች በቅርበት ለማግኘት ምቹ ሁኔታ ይፈጥራል፡፡
በተቋሙ ኮርፖሬት ኮሙዩኒኬሽን መምሪያ የህዝብ ግንኙነት እና ኮሙዩኒኬሽን ሥራ አስኪያጅ አቶ ፍስሐ ጌታቸው በበኩላቸው ሁሉም የተቋሙ ሠራተኞችና አመራሮች ግንዛቤያቸውን በማሳደግ የደም ባንክ አባል ሆኖ ደም በመለገስ ህይወትን የመታደግ በጎ ተግባርን አጠናክሮ ሊቀጥል ይገባዋል ብለዋል፡፡
ደም ለመጀመሪያ ግዜ ሲለግሱ ያገኘናቸው አቶ ካሰሁን ጸሀይ፣አቶ አብደላ ሻንቆ እና አቶ ታምሩ ባቱ ቢያንስ የሶስት ሰው ህይወት ሊታደግ የሚችል ደም ደ መለገስ በመቻላቸው እንደተደሰቱ እና ተቋሙ ይህን በማመቻቸቱ መደሰታቸውን ተናግረዋል፡፡
በቀጣይም መሰል የደም ልገሳዎች ላይ ለመሳተፍ ዝግጁ መሆናቸውን አረጋግጠዋል፡፡
አቶ ሙሉቀን ዮሴፍ እና ወ/ሮ ፋናዩ ዘበነ በበኩላቸው ደም ልገሳውን ለመጀመሪያ ግዜ ቢሰጡም የቅርብ ቤተሰቦቻቸው ጉዳት ደርሶባቸው ህይወታቸው ከማያውቁት ሰው በተለገሰ ደም በመትረፉ ደም ለመስጠት መወሰናቸውን ገልፀዋል፡፡
አቶ ያለውአይቀር ማንደፍሮ እና አቶ ኤርሚያስ ጥላሁን እንደተናገሩት ደግሞ በተለያዩ ጊዜያት ደም መለገሳቸውን አውስተው ደም መሥጠት ዘር፣ጎሳ እና ጾታ ሳይለይ ህይወቱን ሊያጣ የነበረን ሰው ህይወቱን መመለስ ከስጦታዎች በላይ ስጦታ እና የበጎ ተግባርም ምሳሌ እንደሆነ መረዳታቸውን ተናግረዋል ፡፡
ከ 1984 ዓ.ም. ጀምሮ ለ 118 ጊዜያት ደም የለገሱት በደምና ህብረ ህዋስ ባንክ አገልግሎት የትምህርት እና የቅስቀሳ ባለሙያ የሆኑት ሲስተር አሰጋሽ ጎሳ እንደተናገሩት ደም መለገስ ምንም አይነት የጎንዮሽ ጉዳት የማያስከትል እና ዘረፈ ብዙ ጠቀሜታ ያለው ነው፡፡
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አመራሮችና ሠራተኞች በደም እጥረት ምክንያት ህይወታቸውን የሚያጡ የበርካታ ወገኖቻቸውን ህይወት መታደግ እንደሚቻል በመረዳት በዚህ በጎ ተግባር ላይ በመሳተፋቸው ሊመሰገኑ ይገባል ብላዋል፡፡
ደም የሚሞት እና የሚያረጅ እንዲሁም ራሱን የሚተካ በመሆኑ ክቡሩን የሰው ህይወት ልናድንበት እንደሚገባ ጥሪ አቅርበዋል፡፡
የተቋሙ ኮርፖሬት ኮሙዩኒኬሼን መምሪያ ይህን ፕሮገራሙ አስተባብሮ ማዘጋጀቱ የሚመሰገን ተግባር እንደሆነ ያወሱት ሲስተር አሰጋሽ በልገሳ መርሃግብሩ 27 ዩኒት ደም መለገሱንና በቀጣይም በተሻለ እንደሚሰበሰብ ያላቸውን እምነት ጠቁመዋል ፡፡
? "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ;
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia
ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com:/@ethiopowermedia
ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ጥቅምት 19 ቀን 2017 ዓ.ም
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።
@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna
#ኢትዮጵያ
Last updated 2 months, 3 weeks ago
Last updated 2 months, 2 weeks ago
ይህ ስለ Manchester United መረጃዎችን የሚያገኙበት የ Telegram ቻናል ነው 🇪🇹
--------------------------------------------------------------
☞︎| ስለ ማንቸስተር ዩናይትድ ትኩስ መረጃዎች
☞| ቀጥታ ስርጭቶች ከየስታድየሞቹ
☞| የዝውውር ዜናዎች
☞| ስለ ማንችስተር ዩናይትድ ታሪኮች
📩 ለማስታወቂያ ስራ DM :- @Marcoabdu
Last updated 1 month, 1 week ago