አስቂኝ ቀልዶችና ሌሎችም

Description
ያፈቀረን ማሳቅ ለኛ ኖርማል ነው አያሳስብም😉

#Join ያርጉና የትም

ባልተሰሙ ቀልዶቻችን ፈታ እያሉ በውብ የፍቅር ቃላቶች ይደመሙ😍

ዘፈን ግጥም ጠቃሚ ምክሮች...

ከቻልክ❤️ ፍቅርን ተናገር፣ኑር!
ለማንኛውም ሀሳብ አስተያየት እና ፕሮሞሽን

👉 @Get_mu 👉 @just_811

Please😊Don't Leave ችግር ካለ አናግሩን
We recommend to visit

ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ

Last updated 2 months, 3 weeks ago

Last updated 2 months, 2 weeks ago

ይህ ስለ Manchester United መረጃዎችን የሚያገኙበት የ Telegram ቻናል ነው 🇪🇹
--------------------------------------------------------------
☞︎| ስለ ማንቸስተር ዩናይትድ ትኩስ መረጃዎች
☞| ቀጥታ ስርጭቶች ከየስታድየሞቹ
☞| የዝውውር ዜናዎች
☞| ስለ ማንችስተር ዩናይትድ ታሪኮች

📩 ለማስታወቂያ ስራ DM :- @Marcoabdu

Last updated 1 month, 1 week ago

1 month, 1 week ago

••●◉ #ከሻወር_ቡሃላ💦 ◉●••
••●◉●••
#ፈረንጆች... ዋው አምሮብሃል ይሉሃል
••●◉●••
#አረቦች... ጠረንህ ደስ ይላል ይሉሃል
••●◉●••
#ሀበሻ... ምነው ቆላህ የት ልትሔድ ነው🤣

1 month, 1 week ago

ባንክ ቤት ለመቀጠር ሄዶ ጠያቂ... እስኪ የወለድ አይነቶችን ጥቀስ ሲለው.. ልብ-ወለድ አየር-ወለድ ያለው ልጅ በመጀመሪያ ደሞዙ አብወለድ ቢጋብዘኝ ደስ ይለኛል!

1 month, 1 week ago

ንግድ ፍቃድ ሊያወጣ ሄዶ የታደሰ መታወቂያ አለህ ሲባል ምን ቢል ጥሩ ነው
.
.
.
የታደሰ የለኝም ግን የራሴ አለኝ

1 month, 2 weeks ago

የራስህን እንጀራ ለመጋገር የሌላውን ቤት አታቃጥል።

1 month, 2 weeks ago

ታክሲ? ውስጥ ለተፈሳ ፈስ እንኳን አብይ ነው ያስደፈረን የሚሉም አሉ።
#ኧረ_አብይን_ለቀቅ

1 month, 2 weeks ago

ሀበሻ ብቻ ነው "እግዚያብሔር ይስጥልኝ" ስትለው

"ኧረ ችግር የለውም" የሚለው !!!
ከፈጣሪም አይፈልግም?

4 months, 1 week ago

ሰዉየዉ ከባለቤቱ ጋር አንድ የከብቶች ማራቢያ ማእከል በመጎብኘት ላይ ነዉ። #በመጀመሪያ የተመለከቱት ኮርማ አንገት ላይ " ይሄ ኮርማ ባለፈዉ አመት ብቻ 250 ቀናት አጥቅቷል "የሚልፅሁፍ ተንጠልጥሎ ይመለከታሉ የሚቀጥለዉ ላይ " 300 ቀናት አጥቅቷል " ይላል የመጨረሻዉ ኮርማ ላይ "ባለፈዉ አመት ብቻ 365 ቀናት አጥቅቷል" ይላል።#በዚህ_ጊዜ ሚስትየዉ አፏን ከፍታ " ዋ...ዉ! በፍፁም አላምንም በቀን አንዴ እኮ ነው ከዚያ ወደ ባሏ ዞር ብላ" እዉነቴን ነዉ ከዚህ ኮርማ ብዙ መማር ይኖርብሀል " ስትለው#ባልም ... "እስቲ ሂጂና 365 ቱንም ቀናት አንዲት ላም ብቻ ነዉ ወይ ያጠቃዉ ብለሽ ጠይቂያቸዉ" ?

4 months, 1 week ago

**ረጅም ቅንድብ ሰክታ አይቷት

አንቺ ኳስ ተጨዋች ብትሆኚ ከእግርሽ ቀድሞ ቅንድብሽ ነበር off side ሚገባው ?*?*

4 months, 1 week ago

**ትዕግስት ምን እንደሆነ ማወቅ ከፈለክ...

2G ሚጠቀሙ ሰዎችን ጠይቅ**

4 months, 1 week ago

♥️ ተማሪዋ ♥️ ...
           .
           .
?...ክፍል 24...?

ሄሎ ኤፍዬ ደናነህ? ለቀቀህ?"
"ምኑ ቃልዬ?
" ትራፉኩ ካካካ ፣ ድብርቱ ነዋ"
"ምነው በዚህ ሰአት በሰላም ነው ምን ሆነች ብዬ ደነገጥኩ"
"ሰላም ነኝ ኤፍዬ ምን ሆናለሁ ብለህ ነው፣ ገባህ እንዴ ወደቤት?"
"አዋ እቤት ነኝ ቃልዬ"
"ድብርቱ አለቀቀህም ማለት ነው?"
"ሌላ ግዜ በዚህ ሰአት ስራ ላይ ነህ ብዬ ነዋ"
"አንቺስ እስካሁን እንዴት አልተኛሽም ቃልዬ?"
"እያሰብኩ"
"ስለምንድን ነው የምታስቢው "
"ስላንተ እና ስለኔ"
"ስለኔና ስላንቺ ምን?"
"እስቲ በዛሬዋ ቀን ምን ታስታውሳለህ?"
"በዛሬዋ ቀን ማለት ዛሬ?"
"አይ የዛሬ ስድስት ወር ልክ በዛሬዋ ቀን በሀያ ሰባት"
"ምን ላስታውስ ? ያንቺ ፍቅር ስሜንስ ሳያስረሳኝ ይቃራል ቃልዬ እስቲ አንቺ አስታውሽኝ"
"ልክ የዛሬ ስድስት ወር በዚች ቀን በዚች ሰአት  ምሽት ላይ ነበርኮ እዛ ሆቴል በር ላይ የተገናኘነው"
ስትለኝ ልቤ ተረጋጋ።
ስድስት ወር እንደሞላን በደፈናው ባውቅም ቀኗን ለይቼ አላሰብኳትም ነበር። ትኩስ ትንፋሽ በረጁሙ አስወጣሁና።
"ቅድም አብረን እያለን ለምን አልነገርሽኝም ቃልዬ ነው አንቺም ትዝ ያለሽ አሁን ነው?"
"እኔ ነገ ነው የምንገናኘው ስልህ ዛሬ ካልተገናኘን ሞቼ እገኛለሁ ብለህ ስትለኝ ቀኑን አስበህ ነው ብዬ አንተ እንድትነግረኝ ስጠብቅ ነበር አንተ ግን  ሌላ አለም ውስጥ ነበርክ ኤፍዬ ምን ብዬ ልንገርህ"

"ይቅርታ ቃልዬ ረበሽኩሽ አይደል?"
"አንተ መረበሽህ ነው የደበረኝ ለማንኛውም ይህን ላስታውስህ ብዬ ነው በቃ ተኛ ኤፍዬ እንደማፈቅርህ እንዳትረሳ እሺ" ቃላቶቿን  በጆሮዬ የሰማኋቸው ሳይሆን በደምስሬ በስሪንጅ የወሰድኩ እስኪመስለኝ ድረስ በሁለመናዩ ሲሰራጩ ተሰማኝ።
" እንዳትረሳ ማለት ምን ማለት ነው ቃልዬ?"
"ሆሆሆ ኪኪኪ ይሄ ደሞ ሌላ  ምን ማለት ይሆናል ? በቃ እሺ አፈቅርሀለሁ "
አለች። አዎ እንደዛ ነው የሚባለው  እንዳትረሳ ስትይ የመጨረሻ  የ መለያያ ንግግር አስመሰልሽዋ ታድያ ምን ላድርግ ቃልዬ ልላት አልኩና ካፌ መለስኩት።
"እኔም አፈቅርሻለሁ የኔ ማር"
"ቻው"
"ቻው ደና እደሪልኝ"
ኡፍፍፍፍፍ አልኩና ስልኩን ትራሴ ስር ወትፌ በጀርባዬ ስንጋለል።
አውርተን እስክንጨርስ አንዴ ፈገግ አንዴ ጭፍግግ እያለ ሲሰማን የነበረው ኪያ እኔን ተከትሎ በረጅሙ ተነፈሰና።
"ቆይ ለምንድን ነው ስልኩን ማንሳት የፈራኸው ኤፊ?"
"እኔ እንጃ!"
"አቦ ተወና ኤፊ ደሞ ሀይ በቃ እሺ ስሜትህን ሳልረዳ የማይሆን ነገር ተናግሬ ከሆነ ይቅርታ"
"ተጨማሪ ወሬ ለመስማት ብሎ ይቅርታ የሚጠይቅ ሰው አንተን አየሁ"
"አቦ እኔ ለወሬው ብዬ ነው እንዴ? ወንድሜ አደለህ እንዴ ያንተ ጉዳይ አያስጨንቀኝም ኤፊ"
"ባክህ አንተ ከራስህ ዉጪ ለማንም ተጨንቀህ አታውቅም"
"እሺ ስልኩን ለማንሳት የሸከከህ ለምን እንደሆነ ብቻ ንገረኝ"
"ኧረ ኪያ ልተኛበት ተወኝ ••• በቃ አንደኛ ቃልዬ ሰላም ያልሆነች መሰለኝ ሁለተኛ ቅድም ምን አውርተን ተጦላልበን እንደተለያየን ነግሬህ የለ ስለዛኪ ሌላ ወሬ ሌላ እውነት የምትነግረኝ መስሎኝ ነበር የፈራሁት እኔ ሌላ እሷ ሌላ አለም ውስጥ እንደነበርን ያውቅኩት ግን የደወለችው ልክ የዛሬ ስድስት ወር በዚህ ቀን መገናኘታችንን ልትነግረኝ መሆኑን ስትነግረኝ ነው" አበቃ ይሄው ነው ብዬው ተጠቅልዬ ተኛሁ።

እንቅልፍ አልወስድ ብሎኝ ከአንድ ሰአት በላይ ስገላበጥ ቆየሁ፣ ኪያ እንቅልፍ የወሰደው መስሎኝ ስለነበር ድንገት
" ኤፊ !" በማለት ሲጣራ  እየቃዠ መስሎኝ ዝም አልኩት።
" አንተ ኤፍሬም!" በማለት በድጋሚ ተጣራ ።
"አቤት  ኪያ  ምንድን ነው አልተኛህም እንዴ?" አልኩት ቀና ብዬ የክፍሉን መብራት እያበራሁ። ተነስቶ ፍራሹ ላይ ቁጭ ብሏል።
"አንተስ መች ተኛህ "
"እኔማ መች ተኝቼ አውቃለሁ ኪያ በግድ እኮ ነው እንቅልፍ የሚወስደኝ"
"ፍቅር ከያዘህ ወዲህ ነዋ በፊትማ ገና ጋደም እንዳልክ አልነበር••••" ሲል ብስጭት ብዬ•••|
" እንቅልፍ እንቢ ሲልህ ነቆራህን ለመቀጠል ነው የተነሳኸው?"
"ኧረ ጋደኛዬ ምን ሆነሀል   የምናገረው ነገር በሙሉ  ያንተን ስተትና ድክመት እያነሳሁ አንተን ለማብሸቅ እየመሰለህ የተቸገርከው አንተ እኮነህ፣ ለማንኛውም ዝም ብዬ ከስንት ወር በኋላ ዛሬ ዘለግ ላለ ግዜ ብናወራ እንዴት መግባባት አቃተን ቆይ ለምንድን ነው ኤፊ የምለው ነገር በሙሉ ያልጣመው ዋናው እኔን ማማከር የፈለገበት ምክንያት ምንድን ነው ብዬ እያሰብኩ ነበርና አሁን መጨረሻ ላይ ስልኩን ለምን ማንሳት እንዳልፈለክ የነገርከኝ ነገር አንድ ነገር አመላከተኝ"
"በህልምህ ነው በውንህ"
"ምኑ ኤፊ"
"ያመላከተህ ወይ የታየህ"
"አንተ ማሸፍ ከጀመርክ አይጣል ነው እስቲ ቁም ነገር እናውራ"
"በቁምነገር የሆዴን የውስጤን እውነት ሳካፍልህ እቃቃ ጫወታ መጫወት ያማረህ እኮ አንተ ነህ ኪያ"

"በቃ ይቅርታ ኤፊ ጋደኛዬ ታውቃለህ እኔ  ሌላው ነገር ላይ ትኩረት አድርጌ ያላስተዋልኩት ነገር ግን አንተን በጣም የረበሸህ ጉዳይ የዛ ዛኪ የተባለ ልጅ ጉዳይ መሆኑ ቆይቶ ነው የገባኝ። ልክ ነኝ አደል እራስ ምታት የሆነብህ የልጁ ጉዳይ ነው አይደል  ኤፊ?"
"እና እሺ ነው እንበል እና እሺ ምንድን ነው?"
"እንበል እና እሺ ምንድን ነው አይደለም ነው ወይ አይደለም በለኝ ኤፊ ያ ነው አደል ?
ቃልኪደን ዛኪ  ያክስቴ ልጅ ነው ብትልህም አምነህ ለመቀበል ተቸግረሀል አደል ኤፊ?"
"እኔ ነው አደለም እንድልህ ለምን ትጠብቃለህ ኪያ ቆይ እሱ ቢሆንስ ምን ልትለኝ ነው? "
አልኩት ጮክ ብዬ ። እንቅልፍ የወሰደው እስኪመስለኝ ድረስ  ከአንድ ሰአት በላይ ድምፁን አጥፍቶ ከተኛ በኋላ ምን ሊለኝ እንደተነሳ ግራ ገብቶኝ።
" ኤፊ የሱን ልጅ ጉዳይ በኔ ጣለው በቃ!"
"በኔ ጣለው ማለት?"
"አንተ ልጅቷ የድሬ ልጅ ስላልሆነች ከጎረቤትም ከሰፈሯ ልጆችም ስለልጁ እና ስለሷ የእውነት ዘመዷ ይሁን ፋሟ ማጣራት የማይቻል መስሎህ እንደተጨናነክ አሁን በደንብ ገብቶኛል ፣ ቅድምም ፍቅር ያዘኝ ስትለኝ ሌላ ታሪክ ውስጥ ገብቼ ንትርክ ውስጥ ገባን ሙሉውን ታሪክ ስትነግረኝ ደሞ  እስካሁን ምንም አለማድረጋችሁ •••ሌላ ሌላውን ነገር እያሰብኩ ሀሳቤ ተበታተንና እንዲሁ ያለውን ነገር ልትነግረኝ ብቻ እንጂ  የሆነ ያስጨነቀህ ጉዳይ እንዳለ አላስተዋልኩም ነበር አሁን ተኝቼ ሳስበው ያልኩህ ነገር ሁሉ ያልተዋጠልህ ለምን እንደሆነ ገባኝ። በቃ የልጁ ጉዳይ ሰላም እንደነሳህ ገባኝ። የሱን ጉዳይ እኔ በራሴ መንገድ አጣራለሁ እሱን ለኔ ተወው"
"እኮ በምን መንገድ?"
.
.
@askignkeldoch

We recommend to visit

ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ

Last updated 2 months, 3 weeks ago

Last updated 2 months, 2 weeks ago

ይህ ስለ Manchester United መረጃዎችን የሚያገኙበት የ Telegram ቻናል ነው 🇪🇹
--------------------------------------------------------------
☞︎| ስለ ማንቸስተር ዩናይትድ ትኩስ መረጃዎች
☞| ቀጥታ ስርጭቶች ከየስታድየሞቹ
☞| የዝውውር ዜናዎች
☞| ስለ ማንችስተር ዩናይትድ ታሪኮች

📩 ለማስታወቂያ ስራ DM :- @Marcoabdu

Last updated 1 month, 1 week ago