ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።
@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna
#ኢትዮጵያ
Last updated 2 months, 3 weeks ago
Last updated 2 months, 2 weeks ago
ይህ ስለ Manchester United መረጃዎችን የሚያገኙበት የ Telegram ቻናል ነው 🇪🇹
--------------------------------------------------------------
☞︎| ስለ ማንቸስተር ዩናይትድ ትኩስ መረጃዎች
☞| ቀጥታ ስርጭቶች ከየስታድየሞቹ
☞| የዝውውር ዜናዎች
☞| ስለ ማንችስተር ዩናይትድ ታሪኮች
📩 ለማስታወቂያ ስራ DM :- @Marcoabdu
Last updated 1 month, 1 week ago
የመምህራንና ተማሪዎች ዕገታ
በጎጃም አካባቢዎች በመምህራንና ተማሪዎች ዕገታ ምክንያት ዘንድሮ ማስተማር ጀምረው ያቆሙ ትምህርት ቤቶች መኖራቸውንና በርካታ ተማሪዎች በወላጆች ላይ በሚደርስባቸው ማስፈራሪያ ሳቢያ ትምህርት እያቋረጡ መኾኑን ዋዜማ ተረድታለች።
በርካታ የገጠር ትምህርት ቤቶች መምህራን፣ ርዕሳነ መምህራንና የትምህርት ተቆጣጣሪዎች በየጊዜው በፋኖ ታጣቂዎች እንደሚታገቱ ዋዜማ ተገንዝባለች።
ባንዳንድ አካባቢዎች ዕገታውን በመፍራት ወደ ትምህርት ቤት የማይገቡ መምህራን ደሞ፣ በመንግሥት የጸጥታ ኃይሎች እንደሚታሠሩ ምንጮች ገልጸዋል።
በክልሉ የዚህ ዓመት የትምህርት ዘመን የተማሪዎች ምዝገባ እስከ የካቲት 30 ድረስ መራዘሙን የክልሉ ትምህርት ቢሮ ትናንት አስታውቋል። #Wazema
በሸገር ራዲዮ 102.1 ላይ የሰማሁት አንድ ታሪክ ደስ ስላለኝ ላካፍላችሁ
ገርጂ አካባቢ የሚኖሩ አባትና ልጅ የወደቀ ገንዘብ ያገኛሉ(911 ዶላር እና 11 ብር)።ከገንዘቡ ጋር የፓስፖርት ኮፒም አብሮ ነበር።ለሰውየው ለመመለስ አስበው በፓስፖርቱ ላይ በተጠቀሰው ስም ያፈላልጉት ገቡ።አጡት። ከፎቶው እንደተረዱት ባለገንዘቡ 'ፈረንጅ ' ነው።
ሁለት አመት ሙሉ ነጭ ሲያዩ እያስቆሙ ስሙን እየጠየቁ ከፎቶው እያመሳከሩ አፈላለጉት። የሰፈር ሰው ሁሉ 'ስለምን ትሞኛላችሁ?! ገንዘቡን ተጠቀሙበት!' አላቸው።የሰው ሃቅ አንነካም አሉ።እንደውም በመሃል ልጅየው ታሞ ሆስፒታል ገባ።ኦፕራሲዮን ይደረግ ተባለ። ገንዘብ ከየት ይምጣ?!
'አባዬ በዛ በፈረንጁ ገንዘብ ልታከም?' አላቸው።
አባት 'አላህ በሰው ሃቅ እንድታተከም አይፈቅድም!ፈቃዱ ከሆነ በጥበቡ ያድንሃል! ' አሉት።ያ ችግርም ታለፈ ።
ከሰሞኑ ገንዘቡን የጣለውን ሰው አገኙት። ህንዳዊ ነው።ያችኑ 911 ዶላርና አብራ የነበረችውን 11 ብር ሰጡት።
ምን ሊል እንደሚችል ገምቱ።
ጋዜጠኛው ሰዎቹንም እሱንም አፈላልጎ ኢንተርቪው አደረጋቸው።
ጠዋት ወደ ስራ እየሄድኩ ህንዳዊው ለኢትዮጵያውያን ያለውን አድናቆት ሲገልጽ እየሰማሁት ልቤ ሲሞቅ ይሰማኝ ነበር!!
አንዳንዴ እንደዚህ አይነት ታሪኮችን ስሰማ ያ የድሮው የኢትዮጵያዊ ጨዋነት እንዳልጠፋ አስብና ደስ ይለኛል።
ከዘገባው የገረመኝ 'ታሪኩን የሰሙ በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ለአባትና ለልጅ ገንዘብ አሰባስበው 200 ዶላር ላኩላቸው! ' የሚለው ነው።ሰዎቹ በዚህ ደስ ቢላቸውም እኔ ግን ብዙም ደስ አላለኝም። ማድነቅም በትላልቅ ሚዲያዎች ላይ ማቅረብም ያለብን የእነኚህን አይነቶቹን ሰዎች ነበርኮ!
ብዙ ሰዎች የወደቀ ገንዘብ አግኝተው መልሰዋል። የነኚህ ግን ይለያል።ሁለት አመት ሙሉ ያውም ድህነትና ችግር እየፈተነህ?!ሃቁን ለባለሃቁ መመለስ!!
አቅራቢው ጋዜጠኛ ወንድሙ ሃይሉ ነው።
Andualem Buketo
ሁሉም መስፈርቱን አላሟሉም
የትምህርትና ሥልጠና ባለሥልጣን፣ በአዲሱ የመመዘኛ መስፈርት በድጋሚ ከተመዘገቡ 273 የግል ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት መካከል አንድም የትምህርት ተቋም መስፈርቱን ሳይሟላ እንደቀሩ መናገሩን ጠቅሶ ዘግቧል።
ኾኖም የትምህርት ተቋማቱ መስፈርቶቹን እንዲያሟሉ የ45 ቀናት የጊዜ ገደብ እንደተሠጣቸው ባለሥልጣኑ ገልጧል ተብሏል።
ባለሥልጣኑ አዲስ ባወጣው የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት መመዘኛ መሠረት 84 ተቋማት ባለመመዝገባቸው እንደተሠረዙ የባለሥልጣኑ ሃላፊዎች መናገራቸውን ዘገባው ጠቅሷል።
የግል ከፍተኛ የትምህርት ተቋማቱ ሃላፊዎች፣ የባለሥልጣኑን መመዘኛ መስፈርቶች ለማሟላት አስቸጋሪ እንደኾነባቸው ገልጸዋል ተብሏል።
ትራምፕ በኢትዮጵያ
"ትራምፕ" የሚባል ምግብ በአዲስ አበባ መኖሩ ተነገረ ።
ይህ ትራምፕ የሚባለው ምግብ ለ3 ሰዎች እንደሚበቃ እና ከተለያዩ ዓይነቶች እንደሚሠራ ተገልጿል።
ዋጋው 250 ብርነው ተብሏል።
የደመወዝ ማስተካከያው አልቀረም - ዶ/ር መኩሪያ ኃይሌ የሲቪል ሰርቪስ ኮምሽን ኮሚሽነር
የተፈቀደው የመንግስት ሠራተኞች የደመወዝ ማስተካከያ ክፍያ ዘግይቷል፥ ቀርቷል የሚሉ ሃሳቦች እየተራመዱ ነው። በሲቪል ሰርቪስ በኩል የሚለቀቁ መረጃዎች ኦፊሴላዊና የሚተገበሩ መሆኑን መተማመን ጥሩ ነው።
የገንዘብ ሚኒስቴር የተጨማሪ ክፍያ በጀቱን ለሚመለከታቸው ተቋማት ፈቅዷል። በእኛ መስሪያ ቤትም በኩል የተስተካከለውን የጥቅምት ወር ደመወዝ ተከፍሏል። ሌሎችም እንደዚሁ የከፈሉ አሉ። የቀሩት ደግሞ የማጥራት ሥራ እየሰሩ ሊሆን ይችላል። እነዚያም ዝግጅታቸውን ሲያጠናቅቁ የተስተካከለው የጥቅምት ወር ክፍያ ታሳቢ በማድረግ የሚከፍሉ ይሆናል"ብለዋል።
ማስታወቂያ
50,000 እና በላይ የቴሌግራም ተከታይ ያለው ቻናል ካላችሁ በኢትዮጵያዊ ድርጅት ሞኒታይዝ ማስደረግ ስለምትችሉ በውስጥ መስመር አነጋግሩን:: ድርጅቱ በቅርቡ በቲክቶክ እና ዩቱብ እመጣለሁ እያለ ነው:: contact: @ethiodlbot
BREAKING: Bitcoin reaches new all-time high of $75,000 following Donald Trump's winning.
ክልሎች የትምርት መሳሪያዎች ላይ መጠነኛ ክፍያ እንዲያስከፍሉ የሚደነግግ አዋጅ ሊጸድቅ ነው
ክልሎች በሚያወጠት ሕግ መሠረት ለሌሎች የትምህርት መሣሪያዎች የሚውል መጠነኛ ክፍያ ከተማሪ ወላጆች የመክፈል አቅም ጋር በተጣጣመ መንገድ ሊያስከፍሉ የሚችሉበት ህግ ለቋ ኮሚቴ ተመርቷል።
ይጸድቃል ተብሎ በሚጠበቀው አዋጅ ይህንን አላሟላህም ተብሎ ተማሪው ከትምህርት ገበታው እንዲለይ ማድረግ እንደማይቻልም ተጠቁሟል።
በአገር አቀፍ፣ በክልል ወይም በአካባቢ ደረጃ ያለው የትምህርት ደረጃና ጥራት ከተጠበቀው በታች መወረዱ ሲረጋገጥ የጸጥታ ችግር በሺህ የሚቆጠሩ ትምርትቤቶችን ከመማር ማስተማር ውጪ እንዳደረጋቸው የሚታወቅ ነው፡፡
የአጠቃላይ ትምህርት ረቂቅ አዋጅ ባለፈው ሳምንት በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ውይይት ተደርጎበት ለሰው ሀብት ልማት የሥራ ሥምሪትና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ለዝርዝር ዕይታ በአብላጫ ድምፅ የተላከ ሲሆን ይጸድቃል ተብሎም ይጠበቃል፡፡
ትራምፕ ካማላን ሃሪስን በማሸነፍ ቀጣዩ 47ኛው የአሜሪካ ፕሬዜዳንት ይሆናሉ ሲል " ፎክስ ኒውስ " ጠቁሟል።
ባንዲራ ይዘው የኢትዮጵያን ብሄራዊ መዝሙር ሲዘምሩ የነበሩ ታዳጊዎች ከትምህርት ቤታቸው ታፍሰው ተወስደው እንደተደበደቡ ታወቀ
ጀሞ 1 የሚገኘው የሳውዝ ዌስት አካዳሚ ተማሪዎች የሰንደቅ አላማ ቀንን ለማክበር እያንዳንዳቸው አረንጓዴ፣ ቢጫ እና ቀይ ለየብቻ፣ ማለትም አንዱ ተማሪ አረንጓዴ ሌላው ቀይ ሌላው ቢጫ ለብሰው እና የጥላሁን ገሰሰን "ኢትዮጵያ" መዝሙር ሲዘምሩ ቆይተው ኋላ ላይ ግን ለምን ይህን ቀለም ያለበት ልብስ ለበሳችሁ ብለው የፀጥታ አካላት የጅምላ እስር እንደፈፀሙባቸው መሠረት ሚድያ ያሰባሰበው መረጃ ያሳያል።
በሶስት መኪናዎች ተጭነው የመጡት የፖሊስ አባላት ባለ ኮከቡን የኢትዮጵያ ባንዲራ ጭምር ይዘው ሲዘምሩ የነበሩ 30 ገደማ ታዳጊ ተማሪዎችን ጭነው በመውሰድ በቁጥጥር ስር ካዋሉ በኋላ ድብደባ እንደፈፀሙባቸው ታውቋል።
ከተደበደቡት ተማሪዎች መሀል ቢያንስ ሁለቱ ከፍተኛ ጉዳት እንደደረሰባቸው ምንጮቻችን ጠቁመዋል።
እነዚህ የ10ኛ ፣የ11ኛ እና የ12 ኛ ክፍል ተማሪዎች እንዲሁም ዳይሬክተሩ ሀሙስ እለት ካሰሩዋቸው በኋለ አርብ የተወሰኑትን ከፈቱዋቸው በኋላ ዳይሬክተሩን እና የተወሰኑ ተማሪዎች አስረው አቆይተዋል ተብሏል።
"የራሱን የመንግስት በአል ማክበር ያሳስራል ወይ? በጣም ነው ያዘንነው" ያሉት አስተያየት ሰጪዎች የኢትዮጵያ ህዝብ ልጆቻችን ላይ የደረሰውን ግፍ እና በደል ይወቅልን ብለዋል።
ባንዲራ ከመልበሳቸው ጀርባ የሆነ አላማ አለ በሚል ጥርጣሬ እስሩ እና ድብደባው እንደተፈፀመ ምንጮቻችን ጠቅሰው የወረዳ አመራሮች የልጆቻቸውን ከእስር መፈታት ሊጠይቁ ሲሄዱ "የፈለገ በክላሽ መግጠም ይችላል፣ ምላሽ እንሰጣለን" የሚል አሳዛኝ ምላሽ እንደተሰጣቸው ተናግረዋል።
ማርያም ሰፈር በሚገኘው ፖሊስ ጣብያ በታዳጊዎቹ ላይ የተፈፀመው ድብደባ ልባቸውን የሰበረው ወላጆች "ፖለቲካ ምንድን ነው ቢባሉ እንኳን ምላሽ የሌላቸውን የ10ኛ ክፍል ተማሪዎች አጉሮ መደብደብ የግፍም ግፍ ነው" ብለው በምሬት ተናግረዋል።
Meseret Media
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።
@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna
#ኢትዮጵያ
Last updated 2 months, 3 weeks ago
Last updated 2 months, 2 weeks ago
ይህ ስለ Manchester United መረጃዎችን የሚያገኙበት የ Telegram ቻናል ነው 🇪🇹
--------------------------------------------------------------
☞︎| ስለ ማንቸስተር ዩናይትድ ትኩስ መረጃዎች
☞| ቀጥታ ስርጭቶች ከየስታድየሞቹ
☞| የዝውውር ዜናዎች
☞| ስለ ማንችስተር ዩናይትድ ታሪኮች
📩 ለማስታወቂያ ስራ DM :- @Marcoabdu
Last updated 1 month, 1 week ago