ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።
@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna
#ኢትዮጵያ
Last updated 2 months, 3 weeks ago
Last updated 2 months, 2 weeks ago
ይህ ስለ Manchester United መረጃዎችን የሚያገኙበት የ Telegram ቻናል ነው 🇪🇹
--------------------------------------------------------------
☞︎| ስለ ማንቸስተር ዩናይትድ ትኩስ መረጃዎች
☞| ቀጥታ ስርጭቶች ከየስታድየሞቹ
☞| የዝውውር ዜናዎች
☞| ስለ ማንችስተር ዩናይትድ ታሪኮች
📩 ለማስታወቂያ ስራ DM :- @Marcoabdu
Last updated 1 month, 1 week ago
13.አርበኛ ሄኖክ አዲሴ ----ምክ/ሰብሳቢና የፖለቲካ ጉዳዮች ጽ/ቤት ኃላፊ
14.አርበኛ ሞገስ አበራው ----የፖለቲካ ጉዳዮች ጽ/ቤት ምክትል ኃላፊ
15.አርበኛ አራጋው ያለው-----የስትራቴጅክ ጉዳዮች መምሪያ
15.1.አርበኛ ፍቅር መንግስቱ----የስትራቴጅክ ጉዳዮች መምሪያ ምክ/ኃላፊ
16.አርበኛ ሽመልስ ትዛዙ -----የውጭ ጉዳይ መምሪያ ኃላፊ
16.1.አርበኛ አብደላ አያሌው -----የውጭ ጉዳይ መምሪያ ምክትል ኃላፊ
17. አርበኛ አበበ ቀዬ -----የአደረጃጀት መምሪያ ኃላፊ
17.1.አርበኛ አሰፋ መሰለ -----የአደረጃጀት መምሪያ ምክትል ኃላፊ
18.አርበኛ አበበ ፈንታው ----የሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ኃላፊ
18.1.አርበኛ ናትናኤል አክሊሉ ---የሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ምክ/ኃላፊ
18.2.አርበኛ ምኒልክ ፈንታሁን --ሚዲያና ኮሚኒኬሸን ኃላፊ
19.አርበኛ ዚነት አደም-----የሴቶችና ማሕበራዊ ጉዳዮች መምሪያ
19.1.አርበኛ አበበች ሲሳይ---የሴቶችና ማሕበራዊ ጉዳዮች መምሪያ ምክ/ኃላፊ
20.አርበኛ ደስታው መለሰ -------የጽ/ቤት ኃላፊ
20.1.አርበኛ አለባቸው ቀስቅሴ --ምክትል የጽ/ቤት ኃላፊ
21.አርበኛ ንጉስ አዳነ ----የፋይናንስና ግዥ አስተዳደር መምሪያ ኃላፊ
21.1.አርበኛ አማረ አያሌው --የፋይናንስና ግዥ አስተዳደር መምሪያ ምክ/ኃላፊ
22.አርበኛ ረዳ ውበቱ ----------የሐብት አፈላላጊ መምሪያ ኃላፊ
23.አርበኛ እስራኤል እሸቴ ---የሕዝብ አስተዳደር መምሪያ ኃላፊ
23.1.አርበኛ ፍቅሩ ፈንታ---የሕዝብ አስተዳደር መምሪያ ምክ/ኃላፊ
24.አርበኛ አክሎግ ሲሳይ-------የእቅድ ዝግጅትና ግምገማ መምሪያ ኃላፊ
25.አርበኛ *-የመረጃና ደህንነት መምሪያ ኃላፊ
25.1.አርበኛ **-ምክ/የመረጃና ደህንነት መምሪያ ኃላፊ መሆናቸውን ለሰራዊታችንና የኅልውና ትግላችንን በስስት ለሚመለከተው በአገር ውስጥና በውጭው ዓለም ለሚኖረው ሕዝባችን መግለጽ እንወዳለን።
ከዚህ ጋር ተያይዞ ለትግሉ ደጋፊዎች በሙሉ፣ ለአማራ ሕዝብ፣ ለኢትዮጵያ ሕዝብና ለሥራዓቱ ደጋፊዎች የሚከተለውን መልዕክት ማስተላለፍ እንወዳለን!
የበሰበሰውን የብልጽግና ሥርዓት በመደገፍ ወይም የሥርዓቱ አመራር በመሆን እያገለገላችሁ ያላችሁ አካላት፣ በብልጽግና መንግሥት መከላከያ ሰራዊትና የፖሊስ ተቋማት ያላችሁ መሪዎችና የሰራዊት አዛዦች ብዙ የሥራ ባልደረቦቻችሁ እንዳደረጉት የአማራን ሕዝብ የኅልውና ትግል እንድትቀላቀሉ ድርጅታችን የአማራ ፋኖ በወሎ (ቤተ አማራ) ጥሪ ያቀርብላችኋል፡
ውዱ የአማራ ሕዝብ - የሥርዓቱ ሕይወት የሆነውን መንግሥታዊ መዋቅር በማፈራረስ፣ የሥርዓቱ ጠባቂ የሆነውን የብርሃኑ ጁላን ሰራዊት በማግለል ከትጥቅ ትግልህ ጎን ለጎን በሁሉም ከተሞቻችን በሕዝባዊ ማዕበል ስርዓቱን ለመገርሰስ ዝግጁ እንድትሆን እናሳስብሃለን።
ውድ ኢትዮጵያዊያን - አብይ አህመድ ሁሉም አባገነኖች እንደሚያልፉት በቅርብ ቀን ያልፋል! የማያልፉት ኢትዮጵያዊያንና ኢትዮጵያ ናቸው! የአማራን ሕዝብ የኢትዮጵያ አካል ነው ብሎ የሚያምን ኢትዮጵያዊ ሁሉ ፋሽስቱን አብይ አህመድንና የገማውን ሥርዓቱን እንዲቃወምና ከአማራ ሕዝብ ጎን እንዲሰለፍ በአማራ ሕዝብ ስም የትግል ጥሪ እናቀርባለን።
በውጭው ዓለም የምትኖሩ ወገኖቻችን የሥርዓቱን ሁለንተና ለመገርሰስና ከሕዝባችን ጫንቃ ላይ ለአንዴና መጨረሻ ጊዜ አውርዶ ለመጣል የምናደርገውን ትግል በገንዘብ እንድትደግፉ፣ የዘር ጭፍጨፋውን በዲፕሎማሲና በአደባባይ ሰልፎች ለዓለም መንግሥታት፣ ለዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብት ተቋማትና ለዓለም አቀፉ ማህበርሰብ ደጋግማችሁ እንድታጋልጡ እናሳስባለን።
ኅልውናችን በተባበረ ክንዳችን
አማራ ፋኖ በወሎ (ቤተ አማራ)
ወሎ፣ አማራ፣ ኢትዮጵያ፤
ከአማራ ፋኖ በወሎ (ቤተ አማራ) የተሰጠ መግለጫ
ኢትዮጵያዊው ኤዲ አሚን ዳዳ በአማራ ሕዝብ ላይ የሚፈፅመው ጭፍጨፋ የሕዝባችንን ትግል አይቀለብሰውም!!!
መንግሥት መር ጭፍጨፋው በሕዝባዊ የፋኖ ትግል ይቀለበሳል!!!
ፋሽስቱና ደም የጠማው የጠራራ ጋኒን አብይ አህመድ በሕዝባችን ላይ የከፈተውን መንግሥታዊ ጦርነትና እየፈፀመ ያለውን የዘር ማሳሳት፣ የዘር ማፅዳትና የዘር ፍጅት የሰማይ አምላክ ካልሆነ በስተቀር የሰው ልጅ በተለይ ኢትዮጵያዊያን የተረዱት ጉዳይ ነው ብሎ ማሰብ ያስቸግራል። አምባገነኑ የብልፅግና ቁንጮ፣ የኢትዮጵያዊያን የዘመናችን ታላቁ መርገም አብይ አህመድ ሲፈልግ በምድር ጦር፣ ሲፈልግ በሰማይ ጀትና በሰው አልባ ድሮን ጥምረት በአማራ ሕዝብ ላይ እየፈፀመ ያለውን ሁለንተናዊ ፍጅት ሁሉም ኢትዮጵያዊ ዐይንና ጀሮ ሳይሰጠው እንደቀልድ ሁለት ዓመት እያለፈው ነው።
የአማራ ሕዝብ በታንክና በመድፍ እንዲሁም በጀትና በሰው አልባ ድሮን ጥምረት የሚጨፈጨፍበት መሠረታዊ ምክንያት የሰው ልጅ በዴሞክራሲያዊው ዓለም ሊከበሩለት የሚፈልጋቸውን ልዩና የዴሞክራሲያዊ መብቶች ስለጠየቀ አይደለም! ወይም የመንገድና መብራት፣ ፋብሪካና ዘመናዊ ከተሞች ስለጠየቀ አይደለም! ወይም በምከፍለው ግብር ልክ ልዩ ልዩ የጤናና የትምህርት ተቋማት ይከፈቱልኝ ስላለም አይደለም! የአማራ ሕዝብ የመብትና የኑሮ ማሻሻያ ጥያቄዎችን ይዞ ሳይሆን የወጣው ሰው ተብሎና ሰው ሆኖ መኖር በመከልከሉ የሕጋዊ ሰውነት እውቅናን፣ የሕግዊ ሰውነት ውክልናን እንዲሁም ተፈጥሮ በሰጠው ዘመን ውስጥ በኢትዮጵያ ምድር ላይ በሕይወት መኖር መቻልን ለመጠየቅ የወጣ ህዝብ ነው፤ መንግሥታዊ ጦርነት የተከፈተበትም ተፈጥሮ በሰጠው ዘመን ውስጥ በሕይወት መኖርን ስለጠየቀ ብቻና ብቻ ነው። የአማራ ህዝብ ጥያቄ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ውሎች ሁሉንም ሕዝብ በኢትዮጵያዊነቱና በሰውነቱ ልክ ይወቁት፣ ይዳኙት፤ እኔንም ሕጋዊ የዜግነት እውቅናና ሕጋዊ የሕዝብ ውክልና ይስጡኝ፣ ከሌላው ኢትዮጵያዊ ጋርም እኩል ይዳኙኝ የሚል የመኖር ያለመኖር ጥያቄ ነው። በሕዝባችን ጥያቄ ውስጥ በሀገራችን መንግስት በዘራችን ምክንያት ማንነታችን ሳይከዳ፣ ማንነታችን ሳይሳሳና ሳይጠፋ በሕግ ታውቆ መኖርን፣ እኩልነትን፣ ዲሞክራሲንና ፍትሕን የምናገኝ ሲሆን ይህም የኢትዮጵያና የኢትዮጵያዊነት መሠረት ነው። ኢትዮጵያዊያን ግን ልብ ያሉት አይመስልም።
የሰላም ኖቤል ተሸላሚው ሕዝብ ጨፍጫፊውና ጦረኛው አብይ አህመድ ግን እነዚህን የከበሩ የሕዝብ ጥያቄዎች የአማራን ሕዝብ በማንበርከክ ጥያቄዎቹን ድጋሜ እንዳይነሱ ማድረግ ካልሆነም የአማራን ሕዝብ ማጥፋትን ዓላማዬ ብሎ መያዙ ገሃድ የወጣ ሐቅ ነው። በአንዳንድ ፀሐፍት አምባገነኑ ሦስተኛው የዩጋንዳ ፕሬዝደንት ኤዲ አሚን ዳዳ ዘር መርጦ የሰውን ልጅ ስጋና ደም ላልተገባ ተግባር ያውላል ተብሎ እንደተጻፈው ጭራቁ አብይ አህመድን የአማራን ሕዝብ ለማንበርከክ ብሎ በከፈተው ጦርነት የአማራን ልጅ ስጋና ደም እየተመገበ ያለ ሰው በላ መሆኑን ኢትዮጵያውያንም ሆነ ዓለም አቀፉ ማሕበረሰብ ሊገነዘበው የሚገባ እውነት ነው። የአማራ ሕዝብ በማንኛውም የታሪክ አጋጣሚ በሀገሩ መሪና መንግሥት በዚህ ልክ የዘር ጭፍጨፋ ደርሶበት አያውቅም። ፋሽስቱ የጣልያን ወራሪ ክ1928 -33 ዓ.ም ካደረሰው በደል በማይወዳደር መልኩ በሕዝባችን ላይ በዚህ አምሳ ዓመት የደረሰበት በደል የላቀ ሲሆን የሀገር ልጅ በሆነው አብይ አህመድ የደረሰበት በደል ግን የሁሉ ቁንጮ ሆኖ በገሀድ የምናየው ጉዳይ ነው። የአማራን ሕዝብ ባሪያ አደርገዋለሁ ብሎ ቆርጦ የተነሳው አባገነን የገባበት ቅጀት ውስጥ ለመውጣት የሰላም ነጋሪት ቢጎሰምለትም መንቃት የሚፈልግ አይደለም።
ሰሞኑን የአማራ ፋኖ በወሎ (ቤተ አማራ)ን የጠቅላላ ጉባዔ ዓመታዊ ስብሰባን አደናቅፋለሁ ብሎ በማሰብ አመራሮቹ በሌሉበት በደቡብ ወሎ ዞን በአምባሰል ወረዳ በጀትና በድሮን የፈፀመው የንጹሓን ጭፍጨፋ የዚህ አይነተኛ ማሳያ ነው። አማራ መሆናቸውን የማያውቁ ሕጻናት በአብይ አህመድ የግል ንብረት በሆነው አየር ኃይል አማራ ተብለው ተጨፍጭፈዋል።
በእርግጥ የተሸነፈ ስነ ልቦና ባለቤት የሆነውና የስልጣን ጥሙ ከአካሉ የሚገዝፍበት - ከአዕምሮው የሚሰፋበት ይህ የዘመኑ የአፍሪካ አባገነኖች ቀንዲል ከምድር ጦር በዘለለ ሰው አልባ አውሮፕላንና ጀት የሚጠቀመው የሽንፈት ፅዋውን እየተጎነጨ ስለሆነ ነው። ኢትዮጵያዊው ኤዲ አሚን ዳዳ በሕዝባችን ላይ እየፈጸመ ያለው የዘር ጭፍጨፋ ሕዝባዊ ትግላችንን አይቀለብሰውም፤ የተከፈተብን መንግሥት መር ጦርነትም እንደሕዝብ መደራጀታችንን፣ መታጠቃችንን፣ አምባገነናዊ የብልፅግና ሥርዓትን ማስወገዳችንን አያስቀረውም። ሥርዓቱ በሕዝባችን ላይ የሚፈፅመው በደል ከማንኛውም ጊዜ በበለጠ የሚያበረታን እንጅ ክንዳችንን የሚያዝለው አይሆንም።
ስለሆነም ይህንን የአብይ አህመድን ሰይጣናዊ ተግባር ለመቀልበስ በቤተ አማራ (ወሎ) የምንገኝ ፋኖዎች በቀን 14/05/2017 ዓ.ም ወደ አንድነት መምጣታችን ይታወቃል። በመሆኑም ድርጅታችን የአማራ ፋኖ በወሎ (ቤተ አማራ) የመጀመሪያውን የጠቅላላ ጉባዔ ስብሰባውን በማድረግ በስኬት ያጠናቀቀ ሲሆን የማዕከላዊ ምክር ቤትንና የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴውንም አዋቅሯል፤ በሥራ አስፈጻሚና በልዩ ልዩ መምሪያዎች ደረጃ የተመደቡ አመራሮችና ምደባውም የሚከተለውን ይመስላል።
1.ዋርካው ምሬ ወዳጆ --------ሰብሳቢ
2.አርበኛ ድርሳን ብርሃኔ ------ምክ/ሰብሳቢና ወታደራዊ አዛዥ
3.አርበኛ ሀብታሙ ደምሴ -----ምክ/ወታደራዊ አዛዥ
4.ኮሎኔል አባይ ባየው--------ወታደራዊ እቅድና ስትራቴጅ መምሪያ ኃላፊ
5. አርበኛ በለጠ ሸጋው ------ዘመቻ መምሪያ ኃላፊ
5.1. ኮሎኔል ፈንታው መኩዬ ----ምክትል ዘመቻ መምሪያ ኃላፊ
6.ሺ ዓለቃ ያረጋል አሰፋ-----ወታደራዊ አስተዳደር መምሪያ ኃላፊ
6.1. አምሳ ዓለቃ ሲሳይ ገላነው---ምክትል ኃላፊ - ለሰው ሃብት አስተዳደር መምሪያ
6.2. ዶ/ር አቡበክር ሰይድ---ምክትል ኃላፊ - ለጤና ጉዳይ
7.መቶ አለቃ በሪሁን ደምሌ---ሎጂስቲክስ መምሪያ ኃላፊ
7.1.አርበኛ ሞላ ሰማው ------ምክትል ኃላፊ - ለስንቅና ትጥቅ ስርጭት
7.2. አርበኛ ኢሳይያስ መልኩ----ምክትል ኃላፊ - ለኦርዲናንስ ክፍል
7.3. አርበኛ ኑረዲን አበበ ----ምክትል ኃላፊ - ለትራንስፖርት ስምሪት
8.መቶ ዓለቃ ዮሴፍ አስማረ ---ወታደራዊ ሥልጠና መምሪያ ኃላፊ
8.1. አርበኛ ጌታቸው ሲሳይ ----ምክትል የሥልጠና መምሪያ ኃላፊ
9.አርበኛ ** ---ወታደራዊ መረጃ መምሪያ ኃላፊ
10. አምሳ ዓለቃ አደም አሊ ----ወታደራዊ ኢንዶክትሪኔሽን (ስርጸት) መምሪያ ኃላፊ
10.1.አርበኛ ሙላት አላምረው-----ወታደራዊ ኢንዶክትሪኔሽን መምሪያ ምክ/ኃላፊ
10.2.አርበኛ ተመስገን በቀለ ----የኪነትና መዝናኛ ክፍል ኃላፊ
11.አርበኛ ተሾመ ፈንታዬ -----ልዩ ዘመቻ መምሪያ ኃላፊ
12.ኮሎኔል ሞገስ ዘገዬ -----ወታደራዊ አማካሪ
ከሸዋሮቢት ከተማ ወደ ደብረብርሃን አመራር አጅቦ ሲንቀሳቀስ የነበረ የአድማ ብተናና መከላከያ ሠራዊት ተደመሠሠ!
አማራ ፋኖ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት ዕዝ
የካቲት 2/2017 ዓ.ም
የአማራ ፋኖ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት ዕዝ መሃመድ ቢሆነኝ ኮር አስቻለው ደሴ ክፋለጦር 4ኛ ሻለቃ ከሸዋሮቢት ወደ ደብረብርሃን የብልፅግና ከፍተኛ አመራሮችን አጅቦ ሲንቀሳቀስ በነበረ በጠላት ፓትሮል ላይ የደፈጣ እርምጃ በመውሰድ የጠላት ሀይልን ደምስሶታል። አመራሮቹን በ6 ፓትሮል አጅቦ ዲሽቃና ዙ-23 ያጠመደው የጠላት ሃይል ከሸዋሮቢት ከተማ ሳይርቅ ልዩ ቦታው ፍርፍር በተባለ ቦታ የአርበኛ መከታው ቀኝ እጆች በደፈጣ ጠብቀው አርግፈውታል።
በሌላ ግንባር የአማራ ፋኖ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት ዕዝ የአፄ አምደ ጽዮን ኮር 7ለ70 ክፍለ ጦር የኦሮሞ ብሄረሰብን ምሽግ አድርጎ ከሚነሳው የጠላት ሀይል ጋር ገጥሞ ከፍተኛ ድል ተቀዳጅቷል። የጠላት ቡድን ሀይሉን አሰባስቦ ውጊያ ቢክፍትም የአማራ ፋኖ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት ስር የሚገኘው 7ለ70 ክፍለ ጦር በተለያየ አቅጣጫ የጠላትን ሃይል በመግጠም ከፍተኛ ኪሳራ አድርሶበታል። በዚህ ቀጠና በአውደ ውጊያ የተመታው የብልፅግና ሠራዊት በኦሮሞ ብሄረሰብ ዞን ውስጥ ከተደበቀው ከሸኔ ጋር በጥምረት ውጊያ የከፈተ ቢሆንም በተባበረ ክንድ በአማራ ፋኖ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት ዕዝ አናብስቶችና የጦር ጠበብቶች እየተደቆሰ ይገኛል።
ድል ለአማራ ፋኖ
አማራ ፋኖ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት ዕዝ
ከ ሳምንት በኋላ List የሚደረግ እና ጥሩ ዋጋ ይወጣለታል ተብሎ የሚጠበቅ በኤርድሮፕ ፕሮጀክት ታሪክ ትልቁ የተባለለትን PAWS ኤርድሮፕ ያልጀመራችሁ ከታች ባለው ሊንክ ጀምሩ ።
?
https://t.me/PAWSOG_bot/PAWS?startapp=89zFxsHl
የ አማራ ፋኖ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት ዕዝ የመንዝ ማማ ወረዳን (ሞላሌን) ተቆጣጥሯል። @showapress
የ አማራ ፋኖ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት ዕዝ የመንዝ ማማ ወረዳን (ሞላሌን) ተቆጣጥሯል።
ሕዳር 27 ቀን 2017 ዓ.ም
ከአማራ ፋኖ በጎጃም የተላለፈ መመሪያ
```````````````````````````````````````````
የብልፅግና ወራሪ ሰራዊት በመደበኛ ጦርነት በህዝብ ላይ ከሚያደርሰው እልቂት ባሻገር በርካታ የውንብድና እና የሽብር ተግባራትን እየፈፀመ ይገኛል።
በከተሞች አካባቢ በየዕለቱ ወጣቶችን ይረሽናል፤ በየማጎሪያ ካምፖች ያጠራቅማል፤ ወደ ማሰልጠኛ ካምፖች ያግዛል። ከዚህ ጎንለጎንም የፋኖ ቤተሰቦችን ያስራል፤ ይረሽናል፤ ንብረት ያወድማል።
በማንኛውም ፀያፍ መንገድ የአብይ አህመድን ስልጣን ማስቀጠልን የመረጠው ወራሪ ሰራዊት ባንኮችን፣ ጤና ጣቢያወችን ዘርፏል፤ አውድሟል። በርካታ ትምህርት ቤቶችንም በመድፍ፣ በሮኬት፣ በድሮን እና በጀት አውድሟል። የገበያ ቀናትን እየመረጠ በሚያደርገው የወረራ ዘመቻ የማህበረሰባችንን ደህንነት ከባድ አደጋ ላይ ጥሎት ይገኛል።
ከሰሞኑም በሚተኩሳቸው መሳሪያወች በህዝብ ላይ ከባድ እልቂት እያስከተለ ነው። በመሆኑም እነዚህን እና መሰል ጉዳቶችን ለመከላከል በምናደርገው ተጋድሎ ምክንያት የህዝብን ደህንነት ለመጠበቅ ሲባል ከመጭው ሰኞ ሕዳር 30/ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ ላልተወሰነ ግዜ:-
1) ከአምቡላንሶች በስተቀር መንገዶች ለሁሉም ተሽከርካሪወች ዝግ እንዲደረጉ መመሪያ ተሰጥቷል።
2) ለህዝብ ደህንነት ሲባል ከጤና ተቋማት በስተቀር ባንኮችን እና ትምህርት ቤቶችን ጨምሮ የህዝብ አገልግሎት የሚሰጡ ተቋማት ዝግ እንዲሆኑ ታዟል።
3) በመጨረሻም ሰራዊታችን እና መላው ህዝብ ወራሪውን ሰራዊት ለመመከት ለምናደርጋቸው ተከታታይ ወታደራዊ ጥሪወች በወትሮ ዝግጁነት እንዲጠብቅ እናሳስባለን
አዲስ ትውልድ! አዲስ አስተሳሰብ! አዲስ ትስፋ!
የአማራ ፋኖ በጎጃም!
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።
@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna
#ኢትዮጵያ
Last updated 2 months, 3 weeks ago
Last updated 2 months, 2 weeks ago
ይህ ስለ Manchester United መረጃዎችን የሚያገኙበት የ Telegram ቻናል ነው 🇪🇹
--------------------------------------------------------------
☞︎| ስለ ማንቸስተር ዩናይትድ ትኩስ መረጃዎች
☞| ቀጥታ ስርጭቶች ከየስታድየሞቹ
☞| የዝውውር ዜናዎች
☞| ስለ ማንችስተር ዩናይትድ ታሪኮች
📩 ለማስታወቂያ ስራ DM :- @Marcoabdu
Last updated 1 month, 1 week ago