አቡ ዩስራ - ንጽጽራዊ አስተምህሮ

Description
የአቡ ዩስራ ንጽጽራዊ ሀይማኖት ላይ ያተኮሩ የፁሁፍና የድምጽ ስራዎች ይቀርቡበታል።
We recommend to visit

ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ

Last updated 2 months, 3 weeks ago

Last updated 2 months, 2 weeks ago

ይህ ስለ Manchester United መረጃዎችን የሚያገኙበት የ Telegram ቻናል ነው 🇪🇹
--------------------------------------------------------------
☞︎| ስለ ማንቸስተር ዩናይትድ ትኩስ መረጃዎች
☞| ቀጥታ ስርጭቶች ከየስታድየሞቹ
☞| የዝውውር ዜናዎች
☞| ስለ ማንችስተር ዩናይትድ ታሪኮች

📩 ለማስታወቂያ ስራ DM :- @Marcoabdu

Last updated 1 month, 1 week ago

3 weeks, 4 days ago

ጥያቄ: —
ቁርኣን በሱራ 2:7 ላይ  ያላመኑትን ሰዎች አይን ሸፍኖ፣ጆሮና ልብ ላይ  አትሞ ለምንድ ነው በእኔ አላመናችሁም ብሎ የሚቀጣቸው? ይሄ  ከኣምላክ የማይጥበቅ የፍትህ መዛባት ነው።

خَتَمَ ٱللَّهُ عَلَىٰ قُلُوبِهِمۡ وَعَلَىٰ سَمۡعِهِمۡۖ وَعَلَىٰٓ أَبۡصَٰرِهِمۡ غِشَٰوَةࣱۖ وَلَهُمۡ عَذَابٌ عَظِيمࣱ

አላህ በልቦቻቸው ላይ በመስሚያቸውም ላይ አትሞባቸዋል፤ በዓይኖቻቸውም ላይ መሸፈኛ አልለ፤ ለነሱም ታላቅ ቅጣት አላቸው፡፡

መልስ:—

1) በመጀመሪያ የአንቀፁ  ሙሉ ሃሳብ ለማግኘት ከቁጥር 6 ጀምሮ መነበብ አለበት። ሰለዚህ " እነዚያ የካዱት ሰዎች ብታስፈራራቸውም ባታስፈራራቸውም በነርሱ ላይ እኩል ነው አያምኑም " ካለ በዃላ ነው ።እንደነዚህ አይነት ሰዎች በ"ክህደታቸው " ምክንያት ነው ይህ ቅጣት የሚጣልባቸው። [ቁርኣን 4:155]

2) አላህ ሱወ ምንግዜም ቅን የሆኑ ሰዎችን ያውቃል ይመራቸዋልም። ለሰው እንጂ ለአምላክ ይህ ቀላል ነገር ነው። ከኛ ውስጥ ማን መመራትን (ቅናቻን) እንደሚፈልግ። ማን መጥመምን እንደሚፈልግ አስቀድሞ ያውቃል። ከዚህም የተነሳ  አይደለም ምድር ላይ አቆይቶን ፣ ዛሬ ፈጥሮን ዛሬውኑ ፍርድ ቢሰጥ ፍርዱ ፍትሃዊ ነው።

3) አምላክ የሰውን ልጅ ሁለት ምርጫ ሰጥቶ የፈለገውን እንዲመርጥ ከነጥቅሙና ጉዳቱ ግልፅ አድርጓል [ ቁርኣን 76:3 እኛ ወይ አመስጋኝ ወይም ከሓዲ ሲኾን መንገዱን መራነው፤ (ገለጽንለት) ] በዚህ ሒደት ውስጥ የነብያት ተልእኮ መልእክቱን ማደረስ ብቻ ነው። መመራት በአላህ ሱወ እጅ ያለ ጉዳይ ነው።እርሱ ቅኖቹን ዐዋቂ ነውና። [ቁርኣን 28:56 አንተ የወደድከውን ሰው ፈጽሞ አታቀናም፡፡ ግን አላህ የሚሻውን ሰው ያቀናል እርሱም ቅኖቹን ዐዋቂ ነው]

4.  ሰለዚህ ከላይ የተገለፁ ሰዎች [ ከሃዲዎች] ከክህደታቸው ከተመለሱ ወደ ቅኑ  መንገድ ይመራሉ ምክንያቱም ። አላህ ሱወ ለባሮቹ ክህደትን አይሻምና።[ቁርኣን 49:7]

እንዲህማ ባይሆን ትላንት የሌላ እምነት ተከታይ  የነበሩ ሰዎች በዚህ አንቀፅ እያሳበቡ ባልሰለሙ ነበር። ለእውነት ያደረጉት ጥረት ፍሬ እያፈራ በየግዜው ሰዎች ወደ እስልምና ይገባሉ።

ቁርኣን 8:38 ለነዚያ ለካዱት በላቸው፡- ቢከለከሉ ለእነሱ በእርግጥ ያለፈውን (ሥራ) ምሕረት ይደረግላቸዋል።

4 weeks, 1 day ago

If you tell the truth, you don't have to remember anything.

©Mark Twain

1 month ago

ክርስቲያኖችና ሦስት ቁጥር ያላቸው ጠብ

"ልክ ስላሴ ለመረዳት እንደሚቸግረው ሁሉ ኢየሱስ ሦስት ቀንና ሦስት ሌሊት በምድር ሆድ ውስጥ ቆይቷል የሚለው ሌላኛው ስላሴ ነው"

ሁለቱም ለመረዳት የሚቸግሩ ናቸው።

3 months ago

ዛሬ ማታ በወንድማችን አብዱልከሪም ቤት የነበረን የላይቭ ፕሮግራም በመብራት ችግር ምክንያት ለሌላ ቀን ተራዝሟል። ኢንሻአላህ ቀኑን እናሳውቃለን።

3 months, 1 week ago

ሙሉ ቁርኣን በአንድ ገፅ

3 months, 1 week ago

"አምላክ" አይደለሁም ያለበት ቦታ!

አንዱ ነብይ ነኝ ብሎ ተነሳ፣ ህዝቡ ግን አላመነበትም። ስለዚህ ሰበሰባቸውና ዛሬ እኔ ነብይ መሆኔ በአደባባይ አረጋግጥላችዃለው አላቸው።

በል ማስረጃህን አቅርብ ሲሉት።

እሱ: እኔ በአሁን ሰአት በአዕምሮአቹ  የምታስቡትን አውቃለው አላቸው።

ህዝቡ ማጉረምረም ጀመር ፣ በል ንገረንና እንመንህ አሉት።

እሱ፦ አሁን በዚህ  ሰአት እያሰባቹ ያላችሁት ይህ ሰው ቀጣፊ  ነው እያላቹ ነው አላቸው ይባላል።

እኛ ሙስሊሞች ክርስቲያኖችን ኢየሱስ  "እኔ አምላክ ነኝ" የሚል ስለራሱ የተናገረበት ንግግር መፅሀፍ ቅዱስ ላይ የለም ብለን ስንጠይቅ መልሱ እንደሌለ የሚያውቁ ሰዎች የሚሰጡን ምላሽ፦

① አምላክነቱን ሊገልፅ አልመጣም ይላሉ

ሰው የሆነው ለእኛ ብሎ እስከሆነ ድረስ ፣ አምላክነቱን ለመግለፅ ምንድ ነው የሚያስፈራው?  ምን እንዳይሆን ነው ሚስጢሩን የደበቀበት ምክንያት?  ሞት ከሆነ እንደ እናንተ አስተምህሮ አልቀረለትም። ከግዜው በፊት እንዳይገሉት ፈርቶ ነው እንዳይባል "አምላክ ነው"  ያለ ግዜው ቢገሉትም መነሳት ይችላል። ይህ ምላሽ አሳማኝ አይደለም።

②  ነብያቶች ሲመጡ ነብይነታቸውን እንደሚገልፁ ሁሉ አምላክነቱን መግለፁ እና ማብራራቱ የሚጠበቅና ተገቢ ነው። ነብያቶቹን ግልፅ አድርጎ ራሱ ሲመጣ ግን "ተደብቆ " ለምን መጣ?

③ሌላኛው አምላክነቱን በግልፅ ለምን አልተናገረም? ተብለው ሲጠየቁ። "አምላክ አይደለሁም" ያለበትን ቦታ አምጡ  አይደለሁም ካላለ ነው ማለት ነው የሚል አሲቂኝ  መከራከሪያ  ያመጣሉ።

እንዲያማ ከሆነ "አብርሀምም አምላክ አይደለሁም" ብሎ ቃል በቃል ስላልተናገረ አምላክ ነው ማለት ነው? ይሄ እጅና እግር የሌለው ሙግት ነው።

እናም እባካችሁ እንደ ሀሰተኛው "ነብይ ነኝ" ባይ የራሳችሁን መልስ ሳይሆን መሠረታዊ ሙግቱን ተከትላችሁ መልስ ስጡ!

https://t.me/Abuyusra3

3 months, 2 weeks ago

ኢየሱስ "አምላክ ነው!" እና ሰሞነኛ ወሬው!

ስራ ሲቀዘቅዝበት ማስታወቂያ እንደሚያበዛ ነጋዴ "ኢየሱስ አምላክ ነው" ብሎ ለሙስሊሞች ለማስረዳት ክርስቲያኖች ሰበብ በተገኘ ቁጥር ሁሉ ይደክማሉ።  ከዛሬ 20 አመት በፊት የተደረገ ጥናትን በማቅረብ ሰሞኑን በሙስሊሞች ላይ ሊሳለቁ ከርመዋል።

ጉዳዩን እንደ አዲስ በማራገብ "ኢየሱስ አምላክ መሆኑን የሚያሳይ የተቀረፀ ፅሁፍ ነብያችሁ ሙሐመድ ከመወለዱ በፊት  እስራኤል ውስጥ በቁፋሮ ተገኝቷል" በማለት ስሁት ሀተታ እየሰሩ  ይገኛሉ። የስነ ቁፋሮ ባለሙያዎቹ እስራኤል ውስጥ በሚገኝ ሜጊዶ ወህኒ ቤት ላይ ባደረጉት ጥናት እስር ቤቱ ወለል ላይ በግሪክ ቋንቋ የተቀረፀ ፅሁፍ አግኝተዋል ¹

በዚህ ጥናት ወለል ላይ ሶስት ፁሁፎችን ያገኙ ሲሆን እነሱም፦

  1. The Gaianus Inscription - ወለሉ እንዲሰራ ክፍያ የፈፀመውን ወታደር ስም እና የሰራው ባለሞያ ስም

  2. The Akeptous Inscription - አምላክ ወዳድ የሆነችው አኬፕቶስ አምላክ ለሆነው ለኢየሱስ ክርስቶስ መታሰቢያ ይሆን ዘንድ ይህን ጠረፔዛ አቅርቧል - የሚል እና

  3. The Women Inscription - ፕሪሚላ እና ሳይሪያካ እና ዶሮቲያ፣ እና በተጨማሪ ክረስቴን አስታውሱ - የሚል ፁሁፎች ተገኝተዋል።

ጥናቱ  ያደረጉ ሰዎች በመጽሀፋቸው ሲያጠቃልሉ በገፅ 54 እንዲህ ይላሉ፦

“በከፋር ‘ኦትናይ’ የሚገኘው የክርስቲያን የጸሎት አዳራሽ መገኘቱ ከቆስጠንጢኖስ ዘመን በፊት በእስራኤል ምድር ክርስቲያን መገኘቱንና እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ በዋናነት በሥነ ጽሑፍ ምንጮች ሲዳሰስ በነበረበት ወቅት፣ በእስራኤል ምድር ለነበረው ክርስቲያን መገኘት ትልቅ ጠቀሜታ ያለው አርኪኦሎጂያዊ ማስረጃ ነው። በተጨማሪም የሕንፃው ጥናት በሦስተኛው መቶ ክፍለ ዘመን ከክርስቶስ ልደት በኋላ ከአይሁድ እምነት ይልቅ አረማዊ የሆነ የክርስቲያን ማኅበረሰብ መኖሩን ያረጋግጣል” 

ልብ በሉ! ይሄ ኢየሱስ ካረገ ከ200 አመታት በሗላ ነው!!! በዚያን ወቅት ታዲያ “ኢየሱስ አምላክ ነው” የሚል ፅሁፍ መገኘቱ ምን ያስገርማል  ታዲያ? ይህ ጥናት ምን አዲስ ነገር ኖሮት ነው? ከ 1800 አመት በፊት በክርስትያኑ ዘንድ የሚታወቁ የቤተክርስቲያን አባቶች/Church Fathers/ "ኢየሱስ አምላክ ነው" ብለው መጻፋቸው የሚታወቅ ነው። ታዲያ ምኑ ይሄ ይገርማል?

ምናልባት ከኒቂያ ጉባኤ (325) ጋር ተያይዞ ከሆነ ወቀሳው በኒቂያ ጉባኤ ወልድ “አምላክነቱ” በድምፅ ብልጫ ከመፅደቁ በፊት በአርዮስ እና ተከታዮቹ የነበረ ሃሳብ መኖሩን ከመግለፅ ውጪ የተለየ ትርጉም አይሰጥም።

አርዮስ ብቸኛ አምላክ አብ ነው ወልድ ግን የተወለደ፤ መጀመሪያ ያልነበረ ነው ሲል ያምናል። አባት ልጁን እንደማይቀድመው ሁሉ ወልድም አብን አይቀድምም የሚለው ሙግት የአርዮስ ሙግት ነበር። ስለዚህ በዚህ ጉባዔ አሪዮስን ተሳስተሃል፤ ከመጀመሪያም ጀምሮ ነበረ ፤ ከአብም ጋር እኩል አምላክ እንጂ ሁለተኛ አምላክ  አይደለም ብለው ነው በድምፅ ብልጫ ያፀደቁት።

እናም "ኢየሱስ አምላክ ነው" የሚል ፅሁፍ በተገኘ ቁጥር ሙስሊሞች ላይ መሳላቁ ትርጉም አልባ የሆነና እናንተንም ትዝብት ውስጥ የሚከታችሁ ነው።

1- A CHRISTIAN PRAYER HALL OF THE THIRD CENTURY CE AT KEFAR ‘OTHNAY (LEGIO) Excavations at the Megiddo Prison 2005)

3 months, 2 weeks ago

ክፍል ሁለት

3 months, 2 weeks ago

ከአራት አመት በፊት 26 አይነት ቁርዓን ሙስሊሞች አላችሁ በሚል ለቀረበ ጥያቄ የተሰጠ ምላሽ ክፍል አንድ

We recommend to visit

ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ

Last updated 2 months, 3 weeks ago

Last updated 2 months, 2 weeks ago

ይህ ስለ Manchester United መረጃዎችን የሚያገኙበት የ Telegram ቻናል ነው 🇪🇹
--------------------------------------------------------------
☞︎| ስለ ማንቸስተር ዩናይትድ ትኩስ መረጃዎች
☞| ቀጥታ ስርጭቶች ከየስታድየሞቹ
☞| የዝውውር ዜናዎች
☞| ስለ ማንችስተር ዩናይትድ ታሪኮች

📩 ለማስታወቂያ ስራ DM :- @Marcoabdu

Last updated 1 month, 1 week ago