Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council

Description
የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ም/ቤት
Advertising
We recommend to visit

ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ

Last updated 2 weeks, 3 days ago

ለማንኛውም አስተያየት እና ጥቆማ ? @Esat_tv_comment_bot

??ኢሳት የኢትዮጵያ አይን እና ጆሮ??

Last updated 1 month ago

Last updated 2 months ago

2 months, 1 week ago

ሐምሌ 28፣ 2016 ዓ.ል | ሙሐረም 29፣ 1446 ዓ.ሒ
بِسْمِ ٱللَّهِ ٱلرَّحْمَٰنِ ٱلرَّحِيم
•••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••
ለክልል መጅሊስና ለዑለማ አመራሮች የተዘጋጀ ሥልጠና ተጠናቀቀ።
•••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••
አዲስ አበባ |
በኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት፣ የዑለማ ጉባዔ ጽሕፈት ቤት ለክልል መጅሊስ እና ለዑለማ አመራሮች ያዘጋጀው የ10 ቀናት ሥልጠና ተጠናቀቀ።

የዑለማው ጉባዔ ጽሕፈት ቤት ከአል ቡንያን ዓለምአቀፍ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባባር ያዘጋጀው ይህ ሥልጠና አሥተዳደራዊ እና ዲናዊ ክፍተቶችን ለማጥበብ ያለመ እንደሆነ ተነግሯል።

በሥልጠናው መዝጊያ ላይ የተገኙት የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዚደንት የክብር ዶክተር ሸይኽ ሐጂ ኢብራሂም ቱፋ ለሠልጣኞቹ ባስተላለፉት መልዕክት ይህን መሰል ሥልጠናዎች ያለንን እውቀት ለማደስ እና ከዘመን ጋር ለመራመድ አስፈላጊ ናቸው ብለዋል።

ሠልጣኞች ከሥልጠናው ያገኙት እውቀት በየሥራ መስካቸው ኃላፊነታቸውን ለመወጣት ያግዛቸዋል ብለዋል።

የሀገር አቀፉ የዑለማ ጉባዔ ምክትል ሰብሳቢ እና የፈትዋ ዐብይ ኮሚቴ ሰብሳቢው ዶክተር ጀይላን ኸድር በበኩላቸው አብዛኞቹ የሥልጠናው ተሳታፊዎች አንጋፋ ዓሊሞች ቢሆኑም ሥልጠናውን እንደ ተራ ተማሪ በትጋት መከታተላቸውን በመጥቀስ አመስግነዋል።

የሥልጠናው ተሳታፊ ዓሊሞች በሥልጠናው ብዙ ነገር የቀሰሙ በመኾኑ በአሠራራቸውም ኾነ በትምህርት አሰጣጥ ስልታቸው ላይ ለውጥ እንዲያመጡ ያግዛቸዋል ብለዋል።

የጠቅላይ ምክር ቤቱ ፕሬዚደንት ለሠልጣኞቹ የምስክር ወረቀት የሰጡ ሲኾን፣ ለሥልጠናው ስኬት የተለያዩ አካላት ላበረከቱት አስተዋጽዖ ምሥጋና አቅርበዋል።

በሥልጠናው የመዝጊያ መርኃ ግብር ላይ ከባለድርሻ አካላት የተለያዩ መልዕክቶች የተላለፉ ሲኾን፣ ለሥልጠናው ተሳታፊዎች የምስክር ወረቀት ተሰጥቷቸዋል።

በኢትዮጵያ የአል ቡንያን ዓለምአቀፍ ዩኒቨርሲቲ ዋና ኃላፊ ዶክተር ሙሐመድ አል-ቁረይሺ፣ የጠቅላይ ምክር ቤቱ ተቀዳሚ ምክትል ፕሬዚደንት ሸይኽ አብዱልከሪም ሸይኽ በድረዲን፣ የጠቅላይ ምክር ቤቱ ምክትል ፕሬዚደንትና የሐጅ እና ዑምራ ዘርፍ ተጠሪ ሸይኽ አብዱልዓዚዝ ሸይኽ አብዱልዋሊ፣ የጠቅላይ ምክር ቤቱ ዋና ፀሐፊ ሸይኽ ሐሚድ ሙሳ፣ የጠቅላይ ምክር ቤቱ የሥራ አመራሮች፣ ዓሊሞች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።

የኢ.እ.ጉ.ጠ. ም/ቤት ሕዝብ ግንኙነት
ይከታተሉን | Follow us፡
ፌስቡክ | Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council
ቴሌግራም | t.me/eiasc1
ትዊተር | https://x.com/eiasc

Telegram

Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council

የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ም/ቤት

ሐምሌ 28፣ 2016 ዓ.ል | ሙሐረም 29፣ 1446 ዓ.ሒ
2 months, 1 week ago

ሐምሌ 25፣ 2016 ዓ.ል | ሙሐረም 26፣ 1446 ዓ.ሒ
بِسْمِ ٱللَّهِ ٱلرَّحْمَٰنِ ٱلرَّحِيمِ
•••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••
የሃይማኖት አባቶች ለዘመናት የቆዩ የአብሮነት እሴቶችን የሚሸረሽሩ ተግባራት ስር እንዳይሰዱ በጋራ እንዲሠሩ ጥሪ ቀረበ።
••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••
አዲስ አበባ |

የሃይማኖት አባቶች ለዘመናት የቆዩ የአብሮነት እሴቶቻችንን የሚሸረሽሩ ተግባራት ስር እንዳይሰድዱ በጋራ እንዲሠሩ ፕሬዚደንት ሳህለወርቅ ዘውዴ ጥሪ አቀረቡ።

ፕሬዚደንት ሳህለወርቅ ይህን ጥሪ ያቀረቡት "በጎ የዋሉልንን እናመስግን፤ ሰላማችንን እንጠብቅ" በሚል መሪ ሐሳብ በአድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም የስብሰባ አዳራሽ የተጀመረውን የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባዔ 16ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባዔና የእውቅና መርኃ ግብር በንግግር በከፈቱበት ወቅት ነው።

ፕሬዚደንት ሳህለወርቅ በዚሁ ንግግራቸው የሃይማኖት አባቶች በምዕመናን ዘንድ ከፍተኛ ተሰሚነት ያላቸው በመኾኑ፣ በሀገራችን ዘላቂ ሰላም እንዲሰፍን ጠንክረው እንዲሠሩ አሳስበዋል።

የሃይማኖት አባቶች ለዘመናት የቆዩ የአብሮነት እሴቶቻችንን የሚሸረሽሩ ተግባራት ስር እንዳይሰድዱ ተባብረው ሊሠሩ ይገባል ሲሉ ፕሬዚደንቷ አሳስበዋል።

በሰላም ሚኒስቴር የሰላም ግንባታና ብሔራዊ መግባባት ዘርፍ ሚኒስትር ዴዔታ ከረዲን ተዘራ (ዶ/ር)፣ ኢትዮጵያ የሃይማኖት ሀገር በመሆኗ፣ ስትደሰት የሚደሰቱ፣ ስትከፋ የሚከፉ ምዕመናን ሀገር መሆኗን ተናግረዋል።

በቅዱሳን መጻሕፍት ላይ በተለያዩ ቦታ የተጠቀሰችውን የሀገራችን ኢትዮጵያን ዘላቂ ሰላም ለማስጠበቅ ሚኒስቴር መሥሪያ ቤታቸው ከሃይማኖት ተቋማት ጉባዔ ጋር ተቀራርቦ እንደሚሠራ ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባዔ የሥራ አስፈጻሚ ቦርድ ሰብሳቢ የኾኑት ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ ጉባዔው የጋራ በሆኑ የሰላም ጉዳዮች ላይ እንደሚሠራ ተናግረዋል።

ተቋሙ "ሌሎች እንዲያደርጉላችሁ የምትሹትን፣ ለሌሎች አድርጉ" የሚለውን የቅዱሳን መጻሕፍት ወርቃማ መርኅ መሠረት በማድረግ፣ በጋራ ሰላምን፣ መከባበርን፣ አብሮነትን፣ ይቅርታንና መሰል በጎ ሥራዎችን በማስተማር መልካም እሴቶቻችን እንዲጠናከሩ በጋራ እየሠራ መሆኑን ሰብሳቢው ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባዔ ጥቅምት 25፣ 2003 ዓ.ል በአምስት መሥራች የሃይማኖት ተቋማት በመዲናችን አዲስ አበባ የተመሠረተ ሲሆን በአሁን ሰዓት የአባላቱ ቁጥር ወደ ሰባት ቤተ እምነቶች አድጓል።

ተቋሙ በዚሁ ጉባዔ ላይ ለ21መንግሥታዊና መንግሥታዊ ያልሆኑ ተቋማት ለሁለት ግለሰቦች ምሥጋና አቅርቧል።
.••••••••••
የኢት/እ/ጉ/ጠ ምክር ቤት ሕዝብ ግንኙነት
ይከታተሉን | Follow us፡
ፌስቡክ | Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council
ቴሌግራም | t.me/eiasc1
ትዊተር | https://x.com/eiasc1

Telegram

Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council

የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ም/ቤት

ሐምሌ 25፣ 2016 ዓ.ል | ሙሐረም 26፣ 1446 ዓ.ሒ
2 months, 1 week ago

ሐምሌ 24፣ 2016 ዓ.ል | ሙሐረም 25፣ 1446 ዓ.ሒ
بِسْمِ ٱللَّهِ ٱلرَّحْمَٰنِ ٱلرَّحِيمِ
••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••
ጠቅላይ ምክር ቤቱ ለጎፋ ዞን አደጋ ተጎጂዎች 3 ሚሊዮን ብር ግምት ያለው ድጋፍ አደረገ።
••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••
አዲስ አበባ |
ሐምሌ 24፣ 2016 ዓ.ል | ሙሐረም 25፣ 1446 ዓ.ሒ

የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ለጎፋ ዞን የመሬት መንሸራተት አደጋ ተጎጂዎች 3 ሚሊዮን ብር ግምት ያለው የደረቅ ምግብና የቁሳቁስ ድጋፍ አደረገ።

ለአደጋው ተጎጂ ወገኖች የታለመውን እርዳታ የጠቅላይ ምክር ቤቱ ፕሬዚደንት የክብር ዶክተር ሼይኽ ሐጂ ኢብራሂም ቱፋ አስረክበዋል።

በርክክቡ ወቅት ሼይኽ ሐጂ እንደተናገሩት በወገኖቻችን ላይ ይህ አደጋ ሲደርስ የጠቅላይ ምክር ቤቱ አመራሮች ለሥራ ጉዳይ ከሐገር ውጪ በመሆናቸው ምክንያት በወቅቱ በአካል በመምጣት ድጋፍ ማድረግ አለመቻላቸውን ተናግረዋል።

በዛሬው ዕለት ጠቅላይ ምክር ቤቱ ያደረገው ድጋፍ የመጀመሪያ እንጂ የመጨረሻው እንዳልኾነም ሸይኽ ሐጂ ተናግረዋል።

እሁድ ሐምሌ 14 እና ሰኞ ሐምሌ 15፣ 2016 ዓ.ል. በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል፣ በጎፋ ዞን ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሻቻ ጎዝዲ ቀበሌ በተከሰተው የመሬት መንሸራተት አደጋ ጉዳት የደረሰባቸውን ወገኖቻችን በዘላቂነት ለማቋቋም ከኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባዔ አባል ቤተ እምነቶች ጋር በመሆን በቀጣይ ድጋፍ እንዲደረግ ጥሪ አቅርበዋል።

ሼይኽ ሐጂ ኢብራሂም በአደጋው ዘመድ ወዳጆቻቸውን ላጡ ወገኖቻችን ፈጣሪያችን አሏህ ፅናቱን እንዲሰጣቸው ምኞታቸውን ገልፀዋል።

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ልዩ አማካሪ ዶክተር ብርሐኑ ጋቦ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ላደረገው ድጋፍ በራሳቸውና በክልሉ መንግሥት ስም ምሥጋናቸውን አቅርበዋል።

በቀጣይ ጊዜያት 7 መቶ አባዎራዎችን አደጋው ከደረሰበት ኬንቾ ሻቻ ጎዝዲ ቀበሌ ወደ ሌላ ቦታ ለማስፈር የክልሉ መንግሥት ሥራ መጀመሩን ልዩ አማካሪው ተናግረዋል።

በተከሰተው የመሬት መንሸራተት አደጋ 236 ሰዎች ሕይታቸውን እንዳጡ የጠቀሱት ልዩ አማካሪው፣ የአስክሬን ፍለጋው አሁንም እንደቀጠለ ተናግረዋል።

ዛሬ በተደረገው የእርዳታ ድጋፍ ርክክብ መርኃ ግብር ላይ የጠቅላይ ምክር ቤቱ ተቀዳሚ ምክትል ፕሬዚደንት ሼይኽ አብዱልከሪም ሼይኽ በድረዲን፣ የፌደራልና የክልል መጅሊስ ሥራ አስፈፃሚዎች ተገኝተዋል።
••••••••••
የኢት/እ/ጉ/ጠ ምክር ቤት ሕዝብ ግንኙነት
ይከታተሉን | Follow us፡
ፌስቡክ | Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council
ቴሌግራም | t.me/eiasc1
ትዊተር | https://x.com/eiasc1

Telegram

Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council

የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ም/ቤት

ሐምሌ 24፣ 2016 ዓ.ል | ሙሐረም 25፣ 1446 ዓ.ሒ
2 months, 2 weeks ago

ሐምሌ 19፣ 2016 ዓ.ል | ሙሐረም 20፣ 1446 ዓ.ሒ
بِسْمِ ٱللَّهِ ٱلرَّحْمَٰنِ ٱلرَّحِيمِ
••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••
ፕሬዚደንቱ ኢትዮጵያን ወክለው የተሳተፉበት 5ኛው ዓለምአቀፍ የሳይንስ እና የስነ መለኮት ጉባዔ ተጠናቀቀ።
••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••
አዲስ አበባ |

የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዚደንት የክብር ዶ/ር ሸይኽ ሐጂ ኢብራሂም ቱፋ ኢትዮጵያን ወክለው የተሳተፉበትና በሩስያ፣ የታታርስታን ዋና ከተማ ካዛን ለሁለት ቀናት የተካሄደው 5ኛው ዓለም አቀፍ የሳይንስ እና የስነ መለኮት ጉባዔ ተጠናቀቀ።

የጠቅላይ ምክር ቤቱ ፕሬዚደንት ክቡር ሸይኽ ሐጂ ኢብራሂም ቱፋ የብሪክስ (BRICS) አባል የኾነችውን ኢትዮጵያን ወክለው የተሳተፉበት ጉባዔው፣ በዛሬው ዕለት ባለ 9 ነጥብ የአቋም መግለጫ በማውጣት ተጠናቅቋል።

"Spiritual Silk Road: the importance of religious values in the space of Greater Eurasia" በሚል ርዕስ ለሁለት ቀናት በተካሄደው በዚህ ጉባዔ ላይ በታላቁ የዩሮኤዥያ ቀጠና ውስጥ ሃይማኖታዊ እሴቶች በሚኖራቸው ጠቀሜታ ላይ ያተኮሩ የተለያዩ ጽሑፎች እንደቀረቡ ከፕሬዚደንቱ ጋር ወደ ስፍራው የተጓዘው ቃል አቀባያችን ነግሮናል።

በጉባዔው ላይ ከብሪክስ አባል ሀገራት በተጨማሪ ከአረብና ሙስሊም ሀገራት የተጋበዙ የበርካታ ሀገራት ተወካዮች እንደተሳተፉ ለማወቅ ተችሏል።

በሃይማኖታዊ እሴቶች ፋይዳ (አስፈላጊነት) ላይ ባተኮረውና
በዚህ ጉባዔ ላይ፣ በዚህ ዓመት የብሪክስ አባል የኾነችው ኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ በጠቅላይ ምክር ቤቱ ፕሬዚደንት የክብር ዶ/ር ሸይኽ ሐጂ ኢብራሂም ቱፉ ተወክላ ተሳትፋለች።

ጉባዔው ባለ 9 ነጥብ የአቋም መግለጫ በማውጣት የተጠናቀቀ ሲኾን፣ መንፈሳዊ እና ሞራላዊ እሴቶች የዓለም ሚዛንን ለመታደግ እጅግ አስፈላጊ መኾናቸው በአቋም መግለጫው ላይ አጽንዖት እንደተሰጠው ለማወቅ ተችሏል።

በተጨማሪም፣ ጽንፈኝነት እና አሸባሪነት ምንም ዓይነት የሃይማኖት መሠረት እንደሌለው በአቋም መግለጫው ላይ መስፈሩን ከቃል አቀባያችን የተገኘው መረጃ አመልክቷል።

ዘንድሮ ለአምስተኛ ጊዜ የተካሄደው ይህ ጉባዔ ለመጀመሪያ ጊዜ እ.ኤ.አ. በ2016 በቻይናዋ ኡሩምኪ ከተማ የተካሄደ ሲኾን፣ ከዚያ ወዲህ ታታርስታን፣ ኪርጊስታን እና ካዛክስታንን ጨምሮ በተለያዩ ሀገራት እንደተካሄደ ለማወቅ ተችሏል።

••••••••••••••••••

የኢ.እ.ጉ.ጠ. ም/ቤት ሕዝብ ግንኙነት
ይከታተሉን | Follow us፡
ፌስቡክ | Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council
ቴሌግራም | t.me/eiasc1
ትዊተር | https://x.com/eiasc

Telegram

Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council

የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ም/ቤት

ሐምሌ 19፣ 2016 ዓ.ል | ሙሐረም 20፣ 1446 ዓ.ሒ
2 months, 2 weeks ago

ሐምሌ 18፣ 2016 ዓ.ል | ሙሐረም 19፣ 1445 ዓ.ሒ
بِسْمِ ٱللَّهِ ٱلرَّحْمَٰنِ ٱلرَّحِيمِ
••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••
ፕሬዚደንቱ "ሁሉም ሃይማኖቶች በሰላም ዙሪያ ተደጋግፈው በጋራ መሥራት ይጠበቅባቸዋል" ሲሉ ተናገሩ።
••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••
አዲስ አበባ |
የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዚደንት የክብር ዶ/ር ሸይኽ ሐጂ ኢብራሂም ቱፋ በሩስያዋ የታታርስታን ግዛት መዲና፣ ካዛን በመካሄድ ላይ በሚገኘው የብሪክስ ሀገራት ጉባዔ ላይ ንግግር አደረጉ።

ፕሬዚደንቱ በጉባዔው ላይ ሁሉም ሃይማኖቶች በመደጋገፍ በሰላም ዙሪያ በጋራ መሥራት እንደሚጠበቅባቸው ተናግረዋል።

የእስልምና መሠረቱ ፍትኃዊነትና እኩልነት መኾኑን ያወሱት ሸይኽ ሐጂ ኢብራሂም፣ ሙስሊሞች በሰላም፣ በፍትኅ እና በእኩልነት አጀንዳዎች ዙርያ ከማናቸውም ሃይማኖቶች ጋር ለመሥራት ዝግጁ መኾናቸውን ተናግረዋል።

በጉባዔው መክፈቻ ላይ የሩስያው ሙፍቲ ባደረጉት ንግግር የጉባዔውን ጠቀሜታ አስረድተዋል።

ሙፍቲው ሙስሊሞች ከሃይማኖታችንና ከማንነታችን አኳያ ምን ማድረግ አለብን? በብሪክስ ማዕቀፍ ለሚፈጠረው የሀገራት አጋርነትስ ምን ማድረግ ይጠበቅብናል? የሚል መጠይቃዊ ሐሳብ ማንሳታቸውን በስፍራው የተገኘው ቃል አቀባያችን ነግሮናል።

የሩስያው ሙፍቲ የብሪክስ ጉባዔ ዘንድሮ ለ5ኛ ጊዜ መካሄዱን አስታውሰው፣ ኢትዮጵያ እና ኤምሬትስ በዘንድሮው ጉባዔ ላይ ለመጀመሪያ ጊዜ መሳተፋቸውን ጠቅሰዋል።

ኢትዮጵያን የወከሉት የጠቅላይ ምክር ቤቱ ፕሬዚደንት ሸይኽ ሐጂ ኢብራሂም ቱፋ ከተለያዩ ዓለማት ከመጡ ታላላቅ የእስልምና ልሂቃንና ሙፍቲዎች ጋር በሰላም ሐሳብና አብሮነትን በማጎልበት ዙርያ ውይይት አድርገዋል።

የጠቅላይ ምክር ቤቱ ፕሬዚደንት በጉባዔው ላይ ካገኟቸው ከተለያዩ የሃይማኖት መሪዎች፣ ዲፕሎማቶችና የሙስሊም ሀገራት ተወካዮች ጋር በሰላም ጉዳይ ላይ በጋራ በመሥራት አስፈላጊነት ዙርያ ሐሳብ ተለዋውጠዋል።

ጉባዔው በነገው ዕለት እንደሚጠናቀቅ ለማወቅ ተችሏል።

የኢ.እ.ጉ.ጠ. ም/ቤት ሕዝብ ግንኙነት
ይከታተሉን | Follow us፡
ፌስቡክ | Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council
ቴሌግራም | t.me/eiasc1
ትዊተር | https://x.com/eiasc

Telegram

Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council

የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ም/ቤት

ሐምሌ 18፣ 2016 ዓ.ል | ሙሐረም 19፣ 1445 ዓ.ሒ
2 months, 2 weeks ago

ኢንና ሊላሂ ወኢንና ኢለይሂ ራጅዑን

የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት በደቡብ ኢትዮጵያ፣ ጎፋ ዞን፣ ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሻቻ ጎዝዲ ቀበሌ በድንገተኛ የመሬት ናዳ በወገኖቻችን ላይ በደረሰው የሞት አደጋ የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን ይገልጻል።

በተለይም በመጀመሪያው የመሬት ናዳ ጉዳት የደረሰባቸውን የአካባቢውን ነዋሪዎች ለመታደግና የጉዳቱን መጠን ለመቀነስ የአካባቢው ማኅበረሰብ በስፋት በመውጣት ጥረት እያደረገ በነበረበት ሰዓት በተከሰተው ሁለተኛ ዙር የመሬት ናዳ ምክንያት ተጨማሪ የዜጎች ሕይወት መጥፋቱና ከፍተኛ የንብረት ውድመት መከሰቱ ሐዘናችንን የከፋ አድርጎታል።

በዚህ የከፋ አደጋ ውስጥ፣ ኢትዮጵያዊነት አንዱ ለሌላው ችግር ፈጥኖ የመድረስና ለወንድም እህቶቹ ሕይወት እስከ መክፈል የሚደርስ መስዋዕትነት የታየበት ክስተት ኾኖ አልፏል።

በእንዲህ ዓይነት ድንገተኛ አደጋ ወቅት ሕዝባችን እርስ በርሱ የመረዳዳት ባህሉን እንደቀድሞው በማድረግ ጉዳት ከደረሰባቸው ወገኖቹ ጎን በመቆም የተለመደ የአብሮነት ባህሉን እንዲያዳብር ጠቅላይ ምክር ቤታችን በዚህ አጋጣሚ ጥሪውን ያስተላልፋል።

ምክር ቤቱ በአደጋው ቤተሰቦቻቸውንና ወዳጅ ዘመዶቻቸውን ላጡ በሙሉ ፈጣሪያችን አሏህ ጽናቱን እንዲሰጣቸው ይለምናል።

የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት

4 months, 4 weeks ago

ግንቦት 7፣2016 ፣ዙል ቂዳህ 7፣ 1445 ዓ.ሂ.

بِسْمِ ٱللَّهِ ٱلرَّحْمَٰنِ ٱلرَّحِيمِ

ከ ሐጅ ቪዛ ውጪ ሐጅ ማድረግ እንደማይፈ ቀድ የሳውዲ የሐጅ ሚኒቴር አስጠነቀቀ።

ግንቦት 7፣ 2016( አ ዲስ አበባ) የሳውዲ አረቢያ የሐጅና ዑምራ ሚኒስቴር ፣ ከሐጅ ቪዛ ዉጪ በማንኛውም የቪዛ አይነቶች ሐጅ ማድረግ እንደ ማይፈቀድ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ገለፀ።

የጉብኝት ፣ የቱሪስት ፣ የትራንዚት : የስራና መሰል በሳውዲ አረቢያ የሚሰጡ ቪዛዎችን በመጠቀም ሐጅ ለማድረግ የሚሞክሩ ከዚህ ተግባራቸው እንዲቆጠቡ ከወዲሁ የሚኒስተር መስሪያ ቤቱ አስጠንቅቋል።

ሐጅ ለማድረግ ሳዑዲ አረቢያ ከመገባቱ በፊት የሐጅ ቪዛ ማግኘት የግድ አስፈላጊ መኾኑን የጠቀሰው ሚኒስቴሩ፣ በጉብኝት ቪዛ፣ በሥራ ቪዛ፣ በቱሪስት ቪዛ፣ በትራንዚት እና በመሳሰሉት ቪዛዎች ሳዑዲ አረቢያ በመግባት ሐጅ ማድረግ እንደማይቻል አሳስቧል።

ሚኒስቴሩ አክሎም፣ ሐጅ ማድረግ የሚቻለው ጉዳዩ የሚመለከተው የሳዑዲ አረቢያ ሚኒስቴር በየሀገራቱ የሐጅና ዑምራ ጉዳይ ከሚመለከታቸው ተቋማት ጋር በመተባበር በሚሰጠው የሐጅ ቪዛ እና፣ እነዚህ ተቋማት በሌሉባቸው ሀገራት ደግሞ "ኑሱክ ሐጅ" በሚሰኘው ፕላትፎርም አማካይነት ብቻ መኾኑን መረዳት ያስፈልጋል ብሏል።

ሐጅ ለማድረግ፣ ሳዑዲ አረቢያ ከመገባቱ በፊት ራሱን የቻለ የሐጅ ቪዛ ማግኘት የግድ አስፈላጊ እንደኾነ የጠቀሰው የሚኒስቴሩ መግለጫ፣ ከሳዑዲ የሐጅና ዑምራ ሚኒስቴር ጋር ግንኙነት ካላቸው የየሀገራቱ የሐጅና ዑምራ ተቋማት ውጪ የሐጅ ቪዛን ማግኘት እንደማይቻል በመግለጽ ምዕመናን ከመታለል እንዲጠነቀቁ አሳስቧል።

"ሐጅ እናስደርጋለን" በሚሉ አጭበርባሪ ኩባንያዎች መታለል ከሚያስከትለው የገንዘብ ኪሳራ በተጨማሪ፣ የጓጉለትን ሐጅ ለማድረግ አለመቻልን በማስከተል ከባድ ሐዘን ላይ ሊጥል እንደሚችል ሚኒስቴሩ አሳስቧል።

  • ዙል ቂዳህ 7፣ 1445 ዓ.ሂ.
    *​
    የኢት/እ/ጉ/ጠ ምክር ቤት ሕዝብ ግንኙነት።
    ይከታተሉን | Follow us፡
    ፌስቡክ | Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council
    ቴሌግራም | t.me/eiasc1
    ትዊተር | https://x.com/eia

Telegram

Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council

የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ም/ቤት

ግንቦት 7፣2016 ፣ዙል ቂዳህ 7፣ 1445 ዓ.ሂ.
5 months ago

سْمِ ٱللَّهِ ٱلرَّحْمَٰنِ ٱلرَّحِيمِ

ማስታወቂያ ለ1445 የሐጅ ተጓዦች

የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠ ቅላይ ምክር ቤት የ1445 ዓ.ሒ የሐጅ ተጓዦችን የመሔጃና የመመለሻ ቀን የጉዞ መርሐ ግብር ከወዲሁ ጠቅላይ ምክር ቤቱ በከፈተው የመረጃ ማግኛ ማስፈንጠሪያ (ሊንክ) https://hajj.et/hajj-status አማካኝነት ማሳወ ቃችን ይታወቃል።

በመረጃ ማግኛ ማስፈንጠሪያዉ (ሊንክ) ላይ ከተቀመጠው መርሐ ግብር ውጪ ጉዟችሁን የምትሰርዙ ሑጃጆች የበረራ ቦታ ከተገኘ ብቻ አየር መንገዶቹ ያስቀመጡትን ቅጣት ከፍላችሁ የምትስተናገዱ ሲሆን በተጨማሪም በዞን አደረጃጀቱ መሰረት በተያዘላችሁ የማረፊያ ቦታ ላይ አሉታዊ ችግር የሚፈጥርባችሁ መሆኑን ከ ወዲሁ ተገንዝባችሁ በተያዘላችሁ የጉዞ መርሐ ግብር መሰረት ብቻ ጉዟችሁን እንድታከናውኑ ይህ ማስታወቂያ አየር ላይ ከዋለበት ሰዓት ጀምሮ በምዝገባ ጣቢያችሁ በመገኘት የጉዞ መርሐግብራችሁን እንድታረጋግጡ እያሳወቅን ። በተቀመጠላችሁ የጉዞ መርሐ ግብር መሰረት የማትስተናገዱ ሐጃጆች ለሚደርስባችሁ እንግልት ጠቅላይ ምክር ቤቱ ኅላፊነት የ ማይወስድ መሆኑን ከወዲሁ እናሳዉቃለን።

የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት

ግንቦት 4/2016 ዓ.ል
ዙል ቃይዳ 4/1445

5 months ago

የሃጅ ቪዛ የተሰራላችሁ ሃጃጆች በዚህ ሊንክ የፓስፖርት ቁጥር እና ስም በማስገባት የቪዛ ኮፒ ማውረድ ትችላላችሁ።
https://visa.mofa.gov.sa/visaservices/searchvisa

5 months ago
We recommend to visit

ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ

Last updated 2 weeks, 3 days ago

ለማንኛውም አስተያየት እና ጥቆማ ? @Esat_tv_comment_bot

??ኢሳት የኢትዮጵያ አይን እና ጆሮ??

Last updated 1 month ago

Last updated 2 months ago