ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።
@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna
#ኢትዮጵያ
Last updated 2 months ago
Last updated 2 months ago
ይህ ስለ Manchester United መረጃዎችን የሚያገኙበት የ Telegram ቻናል ነው 🇪🇹
--------------------------------------------------------------
☞︎| ስለ ማንቸስተር ዩናይትድ ትኩስ መረጃዎች
☞| ቀጥታ ስርጭቶች ከየስታድየሞቹ
☞| የዝውውር ዜናዎች
☞| ስለ ማንችስተር ዩናይትድ ታሪኮች
📩 ለማስታወቂያ ስራ DM :- @Marcoabdu
Last updated 3 weeks, 5 days ago
የዚህ መጽሐፍ ዐላማ መምህራን ዐደራቸው ለቃለ እግዚአብሔርና ለቃሉ ባለቤት ለእግዚአብሔር በመኾኑ፣ ለሚያስተምሩት ትምህርት ጥንቃቄ ማድረግ እንዳለባቸው ማሳየትና ማሳሰብ ነው። ሕዝበ ክርስቲያኑ ጽሑፋችንን ቢያነብብና ስብከታችንን ቢሰማ፣ እኛን ፈልጎ ሳይኾን፣ እግዚአብሔርን ናፍቆ በመኾኑ ከቅዱሱ ቃል ሳንርቅ ታላቁን እግዚአብሔርን ብቻ ማሳየት ይኖርብናል። ስለ ኾነም አገልጋዮችን ‹‹ከተጻፈው አትለፍ›› ማለት ይገባል።
እኔና እርሱ
ከአንድ ሰው ጋር የነበረኝ ውይይት በአጭሩ
እኔ፤ ስንት አዳኝ ነው ያለው?
እሱ፤ አንድ ብቻ እሱም ጌታችን ነው
እኔ፤ ማርያምስ መድኃኒት ተብላ ተጠርታ የለ? እሷስ አታድንም?
እሱ፤ የመድኃኒት እናት ስለሆነች ነው መድኃኒቱን የወለደችው እሷ ስለሆነች መድኃኒት እንላታለን
እኔ፤ መቼ ነው የወለደችው?
እሱ፤ (ይሄን አታውቅም? ከሚል ሳቅ ወይም ስላቅ በኋላ) ከዛሬ 2000 ዓመት በፊት
እኔ፤ ዛሬ ማርያም መድኃኒት ናት?
እሱ፤ አዎ ናት
እኔ፤ ለምን? አንድ አዳኝ ነው ያለው ብለኸኝ ነበርኮ
እሱ፤ ነገርኩህኮ መድኃኒቱን ስለወለደች ነው መድኃኒት የምትባለው አልኩህ አይገባህምንዴ?
እኔ፤ እሱ ገብቶኛል ስለወለደችው መድኃኒት የተባለችበት ምክንያት ነው ያልገባኝ እሱን ልታስረዳኝ ትችላለህ?
እሱ፤ ቆይ እኔ ልጠይቅህ ጌታችንን የወለደው ማነው?
እኔ፤ ማርያም
እሱ፤ በቃሃ ለዚህ ነው መድኃኒት የምትባለው
🤔😳🤔😳🤔😳🤔
እኔ ግራ ገባኝ የገባቹ አስረዱኝ አልገባኝም
ከዛሬው ንባቤ ላቅምሳቹ ብዬ ነው
እስኪ ሐሳብ ስጡበት
ዛሬ ማርያም ለአባ ጊዮርጊስ ጽዋዕ ያጠጣችው ቀን ነው ተብሎ ይታሰባል። ታሪኩ የሚከተለውን ይመስላል፦
ከሰባት ቀናት የሱባዔ ቆይታ በኋላም፤ ‹‹እንደተለመደው በሥዕለ ማርያም ሥር ተደፍተው ሲያለቅሱ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም የመላእክት አለቃ ቅዱስ ዑራኤልን አስከትላና ጽዋዓ እሳት አስይዛ መጥታ የሕይወት ጽዋዕ አጠጣቻችው፡፡ አባ ጊዮርጊስም የሕይወት ጽዋዕን ከጠጡ በኋላ የሰማይና የምድር ምስጢር ሁሉ ተገለጸላቸው››፡፡ ከዚህም በኋላ ከአርባ በላይ መጻሕፍትን ለመጻፍ ችሏል፡፡
የሕይወት ጽዋዕ›› የተባለውን መጠጥ በተመለከተ ገድሉ ላይ ‹‹የመረጥሁህና የልጄ ወዳጅ ጊዮርጊስ ብላ በስሙ ጠራችው፡፡ ከዕውቀት ወንዝ የመጣና ከጥበብ ምንጭ የተገኘ ከመለኮት ባሕር የተቀዳ ይህን ንጹሕ ጽዋ /እንካ/ ንሣ ጠጣ፡፡ ለስም አጠራርዋ ሰጊድ ይሁንና የዓለም ሁሉ ንግሥት እመቤታችን ያን ጊዜ በቀኝ እጅዋ ሰጠችው፡፡ ሳይጠጣውም ወደ ውስጡ ተመለከተ ይህን ጽዋ የጠጣ አይኰነንም ከሕይወት ባሕር ተቀድቶአልና የሚል መጽሐፍ አገኘ፡፡… ይህም በዮሴፍ ቤት በርሐ ጽዮን ሐዋርያት የጠጡት መንፈሳዊና ሰማያዊ መጠጥ ነው፡፡ በበዓለ ሃምሳ ከጠጡት ያልተለየ ነው፡፡ ይኸውም የሚናገር እሳት፣ የሚያድን እሳት መለኮታዊ እሳት ነው›› የሚል ተጽፎ ይገኛል (የደብረ ባሕርይ ጋስጫ አባ ጊዮርጊስና አቡነ በጸሎተ ሚካኤል አንድነት ገዳም፣ ገድለ አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ እና ገድለ አቡነ በጸሎተ ሚካኤል - ግእዝና አማርኛ፤ (ታኅሣሥ 2004) ገጽ 34 - አጽንዖት የግል)፡፡ በዚህ ታሪክ ውስጥ ‹‹ሐዋርያት የጠጡት መንፈሳዊና ሰማያዊ መጠጥ ነው›› ተብሎ የተጠቀሰው በሐዋርያት ሥራ ምዕራፍ ሁለት ላይ ‹‹በሁሉም መንፈስ ቅዱስ ሞላባቸው›› የተባለው ቅዱሱ መንፈስ ነው፡፡ ‹‹ማርያም›› ለአባ ጊዮርጊስ ያጠጣችው መንፈስ ቅዱስን እንደ ሆነ በገጽ 44 ላይ ‹‹እመቤታችን ማርያምም የገለጠችለት የመጻሕፍትን ዕውቀት ብቻ አይደለም፡፡ የመንፈስ ቅዱስ ኀይልንም አለበሰችው እንጂ›› ተብሎ የተጻፈውን መመልከት ይቻላል፡፡ በገድሉ ትረካ መሠረት መንፈስ ቅዱስን የምትሰጠው ማርያም ናት ማለት ነው፡፡ በገድለ አባ ጊዮርጊስ እንደተጠቀሰው መንፈስ ቅዱስ ‹‹… ከዕውቀት ወንዝ የመጣና ከጥበብ ምንጭ የተገኘ…››፣ ‹‹… ከሕይወት ባሕር …›› የተቀዳ ሳይሆን ራሱ ዕውቀት ሰጪ፣ ራሱ የጥበብ ባለቤት የሆነና ራሱ የሕይወት ምንጭ የሆነ ቅዱስ መንፈስ ነው፡፡ በፍጡር እየተቀዳና በዕቃ እየተጨለፈ የሚወሰድ ሳይሆን እሱ በዓለሙ ሁሉ የመላ ለሁሉ እንደ ወደደ የሚሠራ ገናና አምላክ ነው፡፡
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።
@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna
#ኢትዮጵያ
Last updated 2 months ago
Last updated 2 months ago
ይህ ስለ Manchester United መረጃዎችን የሚያገኙበት የ Telegram ቻናል ነው 🇪🇹
--------------------------------------------------------------
☞︎| ስለ ማንቸስተር ዩናይትድ ትኩስ መረጃዎች
☞| ቀጥታ ስርጭቶች ከየስታድየሞቹ
☞| የዝውውር ዜናዎች
☞| ስለ ማንችስተር ዩናይትድ ታሪኮች
📩 ለማስታወቂያ ስራ DM :- @Marcoabdu
Last updated 3 weeks, 5 days ago