ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።
@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna
#ኢትዮጵያ
Last updated 2 months, 3 weeks ago
Last updated 2 months, 2 weeks ago
ይህ ስለ Manchester United መረጃዎችን የሚያገኙበት የ Telegram ቻናል ነው 🇪🇹
--------------------------------------------------------------
☞︎| ስለ ማንቸስተር ዩናይትድ ትኩስ መረጃዎች
☞| ቀጥታ ስርጭቶች ከየስታድየሞቹ
☞| የዝውውር ዜናዎች
☞| ስለ ማንችስተር ዩናይትድ ታሪኮች
📩 ለማስታወቂያ ስራ DM :- @Marcoabdu
Last updated 1 month, 1 week ago
"ሞኖን/μόνον" ወይም "ብቻ" የሚለው ቅጽል እየገለጸ ያለው ከፊት ለፊቱ በቀጥተኛ ተሳቢ ማሰሪያ አንቀጽ የመጣውን ሐረግ ማለትም አሌቲኖን ቴዎን/ἀληθινὸν θεὸν ነው እንጂ ቀዳማዩን ተውላጠ ስም "አንተ(ሴ/σε)" የሚለውን ቃል ፈጽሞ አይደለም። ይህም ደግሞ አንዱ አካል አብ ብቻ እውነተኛ አምላክ ነው የሚለውን ሐሳብ ፈጽሞ የማይደግፍ እና እንዲያውም የመናፍቃንን (አርዮሳውያንን) እና የሙስሊም አቃቤያን ነን ባዮችን ሐሳብ መና የሚያስቀር ክፍል ነው። በመጨረሻም ሐሳባችንን ለመጠቅለል ያክል ብቸኛ እውነተኛ አምላክ(ቶን ሞኖን አሌቲኖን ቴዎን/τὸν μόνον ἀληθινὸν θεὸν) የሚለው ሐረግ ለእያንዳንዱ ግጻዌ መለኮተ አካላት አጠቃላይ ማንነታዊ መገለጫ ነው። ስለዚህ አብ እውነተኛ አምላክ እንደተባለው ሁሉ እግዚአብሔር ወልድም/ክርስቶስ ኢየሱስም እውነተኛ አምላክ ተብሏል።
**የኢየሱስ ክርስቶስ አምላክነት
ክፍል 2**
“የእግዚአብሔርም ልጅ እንደ መጣ፥ እውነተኛም የሆነውን እናውቅ ዘንድ ልቡናን እንደ ሰጠን እናውቃለን፤ እውነተኛም በሆነው በእርሱ አለን፥ እርሱም ልጁ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። እርሱ እውነተኛ አምላክና የዘላለም ሕይወት ነው።”
1ኛ ዮሐንስ 5፥20
በምድራችን ላይ አምላክ ተብለው የተጠሩ እና ራሳቸውን አምላክ ያደረጉ በአምላክ ስምና ማንነት ራሳቸውን ቀብተው እና ኮናንበው የሚገኙ ብዙ አማልክት ነን ባዮች አሉ። ነገር ግን ቅዱሱ መጽሐፍ ብዙ ጌቶች እና አማልክት ነን ባዮች በምድራችን ላይ ቢኖሩም ከአንዱ ጌታና ከአንዱ አምላክ ምንነት ውጭ ያሉት በሙሉ ሐሰተኞች እና አስመሳዮች እንጂ እውነተኛ አምላካዊ ምንነት ፈጽሞ እንደሌላቸው አስረግጦና አረጋግጦ ይነግረናል(1ኛ ቆሮ 8፥5-6)። ጌታችን እና አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ (እግዚአብሔር ወልድ) አምላክ ተብሎ መጠራትን ብቻ ሳይሆን እርሱ ራሱ እውነተኛ አምላክ አሌቲኖስ ቴዎስ/ἀληθινὸς θεὸς እንደሆነ መጽሐፍ ቅዱስ ይመሰክርልናል። ሐዋርያው ቅዱስ ዮሐንስ በወንጌሉ ላይ የእግዚአብሔር ልጅ የክርስቶስ ኢየሱስን አምላክነት አጉልቶ በማሳየት እርሱ ሰው ብቻ ሳይሆን አምላክ መሆኑን በሚገባ ገልጾልናል። በተጨማሪም የክርስቶስ ኢየሱስን አምላክነት በመልዕክቱ ላይ ሲያሳየን የጌታ ኢየሱስ አምላክነት እውነተኝነትን የተጎናጸፈ ምንነት እንደሆነ ይነግረናል፦
“የእግዚአብሔር ልጅ እንደ መጣ፣ እውነተኛ የሆነውን እርሱን እንድናውቅ ማስተዋልን እንደ ሰጠን እናውቃለን፤ እኛም እውነተኛ በሆነው በልጁ በኢየሱስ ክርስቶስ አለን። እርሱ እውነተኛ አምላክና የዘላለም ሕይወት ነው/οὗτός ἐστιν ὁ ἀληθινὸς θεὸς καὶ ζωὴ αἰώνιος/”— 1ኛ ዮሐንስ 5፥20 (አዲሱ መ.ት)
አንዳንድ ጸረ ክርስቶሳውያን 1ኛ ዮሐንስ 5፥20 እውነተኛ አምላክና የዘላለም ሕይወት የሚለውን ስማዊ ገላጭ ሐረግ አብን እንጂ ወልድን የሚገልጽ አይደለም ብለው ሲሞቱ ይስተዋላሉ። ሲጀመር ክፍሉን መመልከት ያለብን ከምዕራፉ መግቢያ(ም.5:1) ጀምረን መሆን አለበት። ምዕራፍ 5 መላው ሐሳቡን ስናነበው ሐዋርያው ቅዱስ ዮሐንስ እየተናገረ ያለው ስለ እግዚአብሔር_ልጅ እንደሆነ እንመለከታለን። በእግዚአብሔር ልጅ ላይ ስላለን እምነትና ስለ እርሱ ምንነት ምዕራፉ ያብራራል። ስለዚህ የ1ኛ ዮሐንስ መልዕክት ም.5 የምዕራፉ ትርክት ባለቤት ራሱ የእግዚአብሔር ልጅ ማለትም ክርስቶስ ኢየሱስ ነው። ይሄ ማለት ሐዋርያው ቅዱስ ዮሐንስ የእግዚአብሔር ልጅን ወይም ክርስቶስ ኢየሱስን የሐሳቡ ማዕከል አድርጎ የገለጸበት ምእራፍ ነው። ወደ ቁጥር 20 ስናልፍ ደሞ ሐዋርያው ቅዱስ ዮሐንስ ሐሳቡን የእግዚአብሔር ልጅ እንደ መጣ... ብሎ ይጀምርና እርሱ እውነተኛ አምላክና የዘላለም ሕይወት ነው። ብሎ ሐሳቡን ሲቋጨው እንመለከታለን። በዚህ ክፍል ላይ እግዚአብሔር አብ እውነተኛ ተብሎ ተጠርቷል። ነገር ግን እውነተኛ የሆነውን አብን እንድናውቅ ልቡና ወይም ማስተዋል የሰጠን ራሱ እውነተኛ አምላክ የሆነው የእግዚአብሔር ልጅ (እግዚአብሔር ወልድ) ነው። ምክንያቱም እውነተኛም በሆነው በእርሱ አለን ካለ በኋላ እውነተኛ የሆነው የእግዚአብሔር ልጅ ክርስቶስ ኢየሱስ መሆኑን ሲገልጽ እርሱም ልጁ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው በማለት ይናገራል። ክፍሉን በታትነን የአረፍተ ነገሩን ባለቤት ማን እንደሆነ በቀላሉ ለመገንዘብ ያክል፦
➞ የእግዚአብሔር_ልጅ መጣ ("...የእግዚአብሔርም ልጅ እንደ መጣ...")
➞ የእግዚአብሔር_ልጅ እውነተኛ የሆነውን እንድናውቅ ልቡናን ወይም ማስተዋልን ሰጠን ("...እውነተኛም የሆነውን እናውቅ ዘንድ ልቡናን እንደ ሰጠን እናውቃለን...")
➞ የእግዚአብሔር_ልጅ እውነተኛ ነው እኛም በእርሱ አለን (እውነተኛም በሆነው በእርሱ አለን፥ እርሱም ልጁ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው)
➞ የእግዚአብሔር_ልጅ እውነተኛ አምላክና የዘላለም ሕይወት ነው።
ስለዚህ ክፍሉ በሙሉ በእግዚአብሔር ልጅ ላይ ያነጣጠረ ሐሳብ መሆኑን እንረዳለን። በተጨማሪም የዘላለም ሕይወት የሚለው መገለጫ በዚሁ ምዕራፍ ላይ ለእግዚአብሔር ልጅ ለክርስቶስ ኢየሱስ ሲውል እንመለከታለን። በቁጥር 11-12 ላይ የዘላለምን ሕይወት በልጁ በኢየሱስ ክርስቶስ እንደሚገኝና እርሱ ራሱ የዘላለም ህይወት እንደሆነ ይናገራል፦
እግዚአብሔርም የዘላለምን ሕይወት እንደ ሰጠን ይህም ሕይወት በልጁ እንዳለ ምስክሩ ይህ ነው። ልጁ ያለው ሕይወት አለው፤ የእግዚአብሔር ልጅ የሌለው ሕይወት የለውም።
1ኛ ዮሐንስ 5፥11-12
ሐሳቡን ጠቅለል ስናደርገው እውነተኛ አምላክ ወይም በግሪኩ አሌቲኖስ ቴዎስ/ἀληθινὸς θεὸς የሚለው እና የዘላለም ህይወት ዞዌ አዮንዮስ/ζωὴ αἰώνιος የሚሉት ስማዊ መገለጫዎች እርሱ ወይም ሆውቶስ/οὗτός የሚለውን በባለቤትነት ማሰሪያ አንቀጽ የመጣው ተውላጠ ስምን የሚገልጹ ናቸው። ሆውቶስ/οὗτός የሚለው ስም ተኪ ደሞ ቀዳማዩን ስም ማለትም የሱ ክሪስቶ/Ἰησοῦ Χριστῷ የሚለውን ማንነት ተክቶ የገባ ቃል ነው። ይህም ማለት አሌቲኖስ ቴዎስ/ἀληθινὸς θεὸς እና ዞዌ አዮንዮስ/ζωὴ αἰώνιος የተባለው አካል ኢየሱስ ክርስቶስ (የሱ ክሪስቶ/Ἰησοῦ Χριστῷ) ነው።
οἴδαμεν δὲ ὅτι ὁ υἱὸς τοῦ θεοῦ ἥκει καὶ δέδωκεν ἡμῖν διάνοιαν ἵνα γινώσκομεν τὸν ἀληθινόν, καὶ ἐσμεν ἐν τῷ ἀληθινῷ ἐν τῷ υἱῷ αὐτοῦ Ἰησοῦ Χριστῷ. οὗτός ἐστιν ὁ ἀληθινὸς θεὸς καὶ ζωὴ αἰώνιος.
Ιωαννου Αʹ 5.20
ሌላው አርዮሳውያን እና የሙስሊም ኡስታዞች የሚያነሱት የሙግት ነጥብ በዮሐንስ ወንጌል ም.17 ቁ.3 ተንተርሰው እውነተኛ አምላክ የተባለው አብ ብቻ/ ነው ብለው ለመሞገት ይሞክራሉ፦
“እውነተኛ አምላክ ብቻ የሆንህ አንተን የላክኸውንም ኢየሱስ ክርስቶስን ያውቁ ዘንድ ይህች የዘላለም ሕይወት ናት።”
— ዮሐንስ 17፥3
ነገር ግን ክፍሉ ላይ የተገለጸው ሐሳብ እውነተኛ አምላክ ብቻ የሆንህ አንተን እንጂ እውነተኛ አምላክ ብቻህን የሆንህ አንተን ወይም እውነተኛ አምላክ አንተ ብቻ የሆንህ ፈጽሞ አይልም። በእነዚህ ሁለት አገላለጾች መካከል በጣም ሰፊ ልዩነት አለ። የመጀመሪያው ሐረግ የሚለው አንዱ አካል አብ ብቻ እውነተኛ አምላክ (ሞኖን አሌቲኖን ቴዎን/μόνον ἀληθινὸν θεὸν) ነው የሚልን ሐሳብ ሲያንጸባርቅ ሁለተኛው እውነተኛ አምላክ ብቻ የሆንህ አንተን የሚለው ደግሞ አንዱ አምላክ ብቸኛ እውነተኛ አምላክ ነው አብ ደግሞ የአንዱ ብቻውን እውነተኛ አምላክ የሆነው የእርሱ አንደኛው አካል እንደሆነ የሚገልጽ ሐሳብ ነው። ከላይ እንዳየነው ክርስቶስ ኢየሱስም (እግዚአብሔር ወልድ) የአንዱ ብቻውን እውነተኛ አምላክ የሆነው ሁለተኛ አካል በመሆኑ በሐዋርያው ቅዱስ ዮሐንስ መልዕክት ወልድን እውነተኛ አምላክ እንዳለው ተመልክተናል። በተጨማሪም የግሪኩ የሰዋሰው አወቃቀር በተመለከትን ጊዜ "...ሂና ጊኖስኮሲን ሴ ቶን ሞኖን አሌቲኖን ቴዎን/ἵνα γινώσκωσιν σε τὸν μόνον ἀληθινὸν θεὸν..."
---Κατα Ιωαννην 17.3----
**የኢየሱስ ክርስቶስ አምላክነት
ክፍል 1**
“እርሱ በባሕርዩ አምላክ ሆኖ ሳለ፣ ከእግዚአብሔር ጋር መተካከልን ሊለቀው እንደማይገባ አድርጎ አልቈጠረውም፤”
— ፊልጵስዩስ 2፥6 (አዲሱ መ.ት)
አንድ አካል አምላክ ነው የሚባለው ወይም እንደ አምላክ ሊመለክ የሚገባው አምላክ ነኝ ብሎ ስለተናገረ ብቻ ወይም ብዙዎች አምላክነቱን ስላወጁለት አይደለም። በመጽሐፍ ቅዱስ ላይ አምላክ ነኝ ብለው የተነሱ ነገሥታትን እንመለከታለን። ለምሳሌ፦ የጢሮስ ንጉስ እኔ አምላክ ነኝ ማለቱን(ሕዝቅኤል 28፥2-9) ስናይ ይህ ንጉሥ እኔ አምላክ ነኝ ስላለ ብቻ አምላክ ነው ብሎ መፈረጅ አግባባዊ ሙግት ፈጽሞ አይደለም። በሰውም አጀብ አንድ አካል አምላክ ስለተባለም አምላክ ሊሆን አይችልም። ምክንያቱም የግሪክ ጣዖታት እንዲሁ ተብለው ምንነታዊ ለውጥ ስላላሳዩን። ክርስቶስ ኢየሱስ አምላክ ለመሆኑ የአምላክነት ግብሩን፤ ባህሪዎቱንና ሐልዎቱን በተለያየ መንገድ መጽሐፍ ቅዱስ ሲናገር፤ ኑባሬውን ሲተርክና ሲገልጽልን እንመለከተዋለን። ከእነዚህም የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎች ውስጥ አንደኛው የፊልጵስዩስ መልእክት ም2 ቁ6-7 ነው፦
⁶ እርሱ በባሕርዩ አምላክ ሆኖ ሳለ፣ ከእግዚአብሔር ጋር መተካከልን ሊለቀው እንደማይገባ አድርጎ አልቈጠረውም፤
⁷ ነገር ግን የባሪያን መልክ ይዞ፣ በሰውም አምሳል ተገኝቶ፣ ራሱን ባዶ አደረገ"
------
ፊልጵስዩስ 2 (አዲሱ መ.ት)
ὃς ἐν μορφῇ θεοῦ ὑπάρχων οὐχ ἁρπαγμὸν ἡγήσατο τὸ εἶναι ἴσα θεῷ,
-----
Προς Φιλιππησιους 2:6
በጽርዑ ሞርፌ/μορφῇ የሚለው ቃል ኑባሬያዊ መገኘትን፣ ሁናቴን ወይም ባህሪዎተ መልክን የሚገልጽ ቃል ሲሆን ክርስቶስ ኢየሱስ (ወልድ) እም ቅድመ አለም በኑባሬው በባህሪዎተ መልኩ ራሱ አምላክ (ፈጣሪ) ሁኖ የሚኖር አካል እንደሆነ ይገልጻል። በተጨማሪም በባለቤትነት ሙያ (Nominative case) የመጣው ሁፓርኾን/ὑπάρχων የሚለው ቃል በአሁን ጊዜ አመልካች ግስ(Present participle tense) መምጣቱ ወልድ ከዘላለም ጀምሮ ከአብ ጋር አብሮ ህያው አብሮ እኩል አብሮ ዘላለማዊ እንደሆነ በሚገልጽ መልኩ እንደመጣ የክፍሉን ሰዋሰው ይነግረናል። ይህም ደግሞ ለወልድ ኑባሬ ጅማሮ አለው ፍጡር እንጂ ፈጣሪ አይደለም ለሚሉት አርዮሳውያን እና ኢብዮናውያን (Ebionite/Ἐβιωναῖοι) በተለምዶው አዶፕሽኒስቶች የሚባሉት የምን*ፍቅና የአስተምህሮቶችን መሰረታቸውን የሚንድ ክፍል ነው። ሙግታችንን ጠበቅ ለማድረግ ያክል ከተመለከትን ደግሞ ኢየሱስ ክርስቶስ (ወልድ) አምላካዊ ባህሪ(መልክ) ከጥንተ ዘላለም ጀምሮ በዚሁ ባህሪ ሲኖር የነበረው አምላክ ወደ ፈጠራት ጠባበ አለም የሰውን ወይም የባሪያን ባህሪ(መልክ) ይዞ መምጣቱ "ከእግዚአብሔር አብ ጋር መተካከልን ሊለቀው እንደማይገባ አድርጎ አልቈጠረውም" በማለት ብርሃነ አለም ቅዱስ ጳውሎስ ፍንትው አድርጎ የወልድን መለኮታዊ ባህሪዎት ከእግዚአብሔር አብ ጋር እኩል እንደሆነ ያሳየናል።
ከአምላክ ጋር እኩል መሆን ወይም በጽርዑ ቶ ኢናይ ኢሳ ቴኦ/τὸ εἶναι ἴσα θεῷ የሚለው ሐረግ እግዚአብሔር ወልድ ከእግዚአብሔር አብ ጋር በባህሪው እኩል ወይም አንድ አይነት ሆሙስዮስ/ὁμοούσιος እንደሆነ በግልጽ ሁኔታ ሲነግረን የአርዮሳውያንን መርሆተ ቃል የሆነውን ተመሳሳይ ወይም ተቀራራቢ ባህሪዎት #ሆሞዮስዮስ/ὁμοιούσιος የሚለውን ምንፍቅና አፈር ከመሬት የሚደባልቅ ክፍል እንደሆነ እንመለከታለን። በቁጥር ሰባትን አንድ በአንድ ስንመለከተው "የባሪያን መልክ ይዞ" የሚለው ሐረግ በፊት የተገለጠበት ቅድመ ኑባሬያዊ ባህሪዎት እንደነበረው ቁልጭ አድርጎ ያሳየናል፤ እርሱም በቁጥር 6 ላይ እንዳየነው የወልድ አምላካዊ መልክ (ባህሪ) ከጥንተ ዘላለም ጀምሮ ገንዘቡ የሆነ ምንነት ነው። "በሰውም ምሳሌ ሆኖ" የሚለው አገላለጽ ደሞ ወደ ምድር በመጣ ጊዜ ፈጣሪ በፍጡራን ምሳሌ ሆኖ ሰዋዊ ባህሪዎትን እንደተላበሰ ያሳየናል። ቀጥሎም "ራሱን ባዶ አደረገ" የሚለው ደሞ አንድ ነገር ባዶ ሆነ የሚባለው ያ ነገር መጀመሪያውኑ የሆነ ነገር ሲኖረው ነው። ክርስቶስ ኢየሱስ ደግሞ ራሱን ባዶ አደረገ ሲባል አምላካዊ ሙሉነት የነበረው አካል ወደ ፈጠረው፣ ወዳዘጋጀው፣ ሰዋዊ ባህሪዎት ዝቅ ብሎ በመምጣቱ ነው። ስለዚህ ክርስቶስ ኢየሱስ ሰው ሁኖ ከመምጣቱ በፊት በአምላካዊ ሙሉነት የሚኖር አምጻኤ ኩሉ አምላክ እንደሆነ እንመለከታለን።
በመጨረሻም የሙግት ኩረጃ የማይሰለቻቸው ኡስታዞች የጸረ ክርስቶሳውያንን ሐሳብ በማንጠልጠል፦"...ክርስቶስ ኢየሱስ (ወልድ) በእግዚአብሔር ወይም በአምላክ መልክ መኖሩ አዳም በእግዚአብሔር መአልክና ምሳሌ በተፈጠረበት ሒሳብና ቀመር ነው..." ብለው ይሞግታሉ። ነገር ግን የሁለቱን ክፍሎች የጽርዑን የቃላት አገባብ እና አውዳዊ ምልከታ ባደረግን ጊዜ ፈጽመው የየቅል ሐሳብ እንደሆነ እንረዳለን፦
እግዚአብሔርም አለ፦ ሰውን በመልካችን እንደ ምሳሌአችን እንፍጠር/καὶ εἶπεν ὁ θεός Ποιήσωμεν ἄνθρωπον κατ᾽ εἰκόνα ἡμετέραν καὶ καθ᾽ ὁμοίωσιν...>>
— ዘፍጥረት 1፥26
በዘፍጥረት 1፥26 መልክ ብሎ የገባው የግሪኩ ቃል ኤይኮና/εἰκόνα ሲሆን ምሳሌ የሚለው ደሞ ሆሞዮሲን/ὁμοίωσιν በሚለው የቃላት አገባብ እንደተሰደረ እንመለከታለን። ኤይኮና/εἰκόνα የሚለው ቃል ኤይኮን/εἰκών ማለትም ምስለ መልክን መመሳሰል ወይም መቀራረብ(በውጫዊ ማንነት መገለጫ) የሚል ትርጉም አለው። እግዚአብሔር አምላክ ሰውን በእኛ መልክ(ኤይኮና ሄሜቴራን/εἰκόνα ἡμετέραν) እንፍጠር ሲል በጽድቅና ቅድስና(ኤር 4:24)፤ እንዲሁም በመገንዘብ ችሎታንና እውቀትን(ቆላ 3:10) የመሳሰሉትን የምስስሎሽ መገለጫዎች በሚገልጽ አገባብና አግባብ መምጣቱ ቅብል ነው። ነገር ግን የሰው ልጅ በእግዚአብሔር መልክና አምሳል መፈጠሩ በእርግጥ የሚካፈለው ባህሪ እንዳለው ሁሉ የማይካፈለው ባህሪ አለ። በዛው በፊልጵስዩስ መልእክት 1:7 እና 2ኛ ጴጥሮስ 1፥4 ላይ የእግዚአብሔር የባህሪው ተካፋዮች እንደሆንን ይናገራል፦
“ስለ ክፉ ምኞት በዓለም ካለው ጥፋት አምልጣችሁ ከመለኮት ባሕርይ ተካፋዮች(κοινωνοὶ φύσεως) በተስፋ ቃል እንድትሆኑ፥ በእነዚያ ክብርና በጎነት የተከበረና እጅግ ታላቅ የሆነ ተስፋን ሰጠን።”
2ኛ ጴጥሮስ 1፥4
ተካፋይ ወይም በግሪኩ ኮይኖኖስ/κοινωνός የሚለው ቃል የሰው ልጅ ከእግዚአብሔር ፈጽሞ የማይካፈለው ወይም የቀረበት ነገር እንዳለ አመላካች ነው። ይህንን ሐሳብ በሌላ ክፍል በስፋት እንመለከተዋለን። ነገር ግን ክርስቶስ ኢየሱስ ከእግዚአብሔር አብ ጋር የማይጋራው ሆነ የማይካፈለው ባህሪ የለም። ከላይ በፊልጵስዩስ መልእክት 2:6 ከአብ ጋር በመለኮተ ባህሪዎት እኩል ወይም አንድ እንደሆነ ተመልክተናል። ስለዚህ አምላክ ክርስቶስ ኢየሱስ በአምሳለ ሰውነት መገለጡ (እንደ ሰው መብላት መጠጣቱ፤ መተኛት መነሳቱ፤ መወለድ ማደጉ ወዘተ) መለኮታዊ ክብር እንደሌለው የሚያሳየን ተግባር አይደለም። እርሱ ወደዚች ወደ ፈጠራት አለምና ሰውነት ከመገለጡ በፊት አምላካዊ ምንነት፤ ክብርና መለኮታዊ ኑባሬ ከጥንተ ዘላለም ጀምሮ ገንዘቡ ያደረገ ሐያል አምላክ ነው።
@Yeshua_Apologetics_Ministry
«ወደ ጥንታዊያን አበው
ሐይማኖት እንመለስ »
-------
"ንግባእኬ ኀበ ሃይማኖተ
አበዊነ ጥንታውያን።"
ትምህርተ ሥላሴና የቤተክርስቲያን ታሪክ
ረዘም ባለ ዝግጅ የተዘጋጀ ነው(የ1ሰዓት ከ25 ደቂቃ ትምህርት) ገብታችሁ ኮምኩሙ እንግዲህ?
?https://youtu.be/lQ84Tf3OGag?si=2nXrA5AARiP4QYXF
በቪዲዮ ላይ የተዳሰሱት፦
ቃሉን ለምን? ፣ ምሥጢር ማለትስ?
የቤተክርስቲያን አባቶች? ፣ ኒቂያ ጉባኤ?
እና ሌሎችም.... ሼር አድርጓት።
ታንቆ ወይስ ተሰቅሎ?
ሙስሊም ወገኖች ኢየሱስ አልተሰቀለም በማለት ሲሞግቱ ይስተዋላል። ነገር ግን እንደ ፓሪሽ ሳንደርስ የመሳሰሉ ሙህራን የክርስቶስን ታሪክ ዙሪያ ገባውን ሁሉ ካጠና በኋላ <<ጥርጣሬ አልቦ ወይም የማይካዱ ሐቆች>> ብሎ ከዘረዘራቸው 8 ነጥቦች መካከል አንደኛው የኢየሱስ ክርስቶስ የመስቀል ሞት እንደሆነ ይገልጽልናል[1]። ጆን ዶሚኒክ ክሮሳን የተባለው ምሁር ደግሞ በጴንጤናዊው ጲላጦስ ዘመን የክርስቶስ የመስቀል ላይ ሞት ታሪክ እንደ ማንኛውም እውናዊ ታሪካዊ ክስተት እርግጠኛ የምንሆንበት ክስተት እንደሆነ ይነግረናል[2]። በነገረ መለኮት ትንታኔውና በምንባባዌ ህያሴው የሚታወቀው ስመጥሩ ኤቲስቱ ባርት ኧርማን የክርስቶስ ሞትን በተመለከተ በመጽሐፉም ሆነ በቃለ መጠይቆቹ ሞቱ እውነተኛ ታሪካዊ ሀቅ መሆኑን ይናገራል(ከአፖስቴት ፕሮፌት ጋር ያደረገውን ቃለ መጠይቅ መመለልከት ያሻል)[3]። ነገር ግን የሀገራችን ሙስሊም አቃቤያን በእነ አህመድ ዲዳት እና መሰሎቻቸው ሙግት እስከዛሬ ሲሞግቱ ይስተውላል። አንድ አብዱል እንዲህ ሲል ይጽፋል፦
አብዱል፦
" እናንተ በእንጨት ላይ ሰቅላችሁ የገደላችሁትን ኢየሱስን የአባቶቻችን አምላክ አስነሣው፤" (የሐዋርያት ሥራ 5: 30)
የአማርኛ ተርጓሚዎች ይህንን የመፅሀፍ ቅዱስ ክፍል ሲተረጉሙ በአማኙ ላይ ማታለያ ፈፅመዋል። የእንግሊዝኛውም ሆነ የግሪኩ ቃል "ሰቅላችሁ" አይልም። ይልቅስ የሚለው "አንቃችሁ" ወይንም "Hanged" አልያም በግሪከኛው "κρεμάννυμι" ነው። ለማስረጃነት ከታች ሁለቱንም ትርጉሞች አስቀምጥላችኃለው።"
መልስ
በመጀመሪያ ደረጃ፣ "ታንቆ መሞት" ለሚለው ቃል የምንጠቀመው የጽርዕ(የግሪክ) ቃል κρεμάννυμι(ክሬማኑሚ) ሳይሆን ἀπάγχω (አፓግኾ) ነው። ለምሳሌ ስለ ይሁዳ ሲያወራ:-
" ብሩንም በቤተ መቅደስ ጥሎ ሄደና #ታንቆ ሞተ።" የማቴዎስ ወንጌል 27:5
καὶ ῥίψας τὰ ἀργύρια εἰς τὸν ναὸν ἀνεχώρησεν, καὶ ἀπελθὼν #ἀπήγξατο.(አፔግሳቶ) የሚለውን ይጠቀማል።
ነገር ግን κρεμάννυμι/ክሬማኑሚ የሚለው ቃል ብዙ ትርጉም አለው። መስቀል(ለምሳሌ፦ ጃኬቴን እንጨቱ ላይ ሰቀልኩት ማለት ከፈለግኩ በጽርዕ(በግሪክ) ይህን ቃል ነው የምጠቀመው(ጃኬቴን እንጨት ላይ አነቅኩት አይባልም) ምናልባት ሙስሊሙ ወዳጄ ጃኬቴን አነኩት ይለን ይኾን?
ሌላው ኢየሱስም የተሰቀለው እንጨት ላይ ተንጠልጥሎ ነው(κρεμάννυμι) እንጂ እንጨት ላይ እንደ አልጋ ተኝቶ አይደለም። ለዛ ነው ይህን ቃል የተጠቀመው። ስለዚህ κρεμάννυμι "depend" (የተመረኮዘ) (hangs on) የሚል ትርጉምም ሊሰጠን ይችላል።
ይሄንንም በምሳሌ ስንመለከተው፦
" በእነዚህ በሁለቱ ትእዛዛት ሕጉም ሁሉ ነቢያትም ተሰቅለዋል(κρέμαται/ክሬማታይ)።"
"40 On these two commandments the whole law #hangeth(depends), and the prophets."
(Matthew 22:40)
ስለዚህ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተሰቀለው በእንጨት ላይ ተንጠልጥሎ ስለሆነ(κρεμάννυμι/ክሬማኑሚ) ተብሎ ተነገረ እንጂ እንጨት ላይ እንደ አልጋ ተኝቶ ነው ብለን ስለማናምን ግዴታ አነቀው ማለት አይቻልም። ለዚህም ነው ይህን የጽርዕ ቃል የተጠቀመው። ስለዚህ κρεμάννυμι/ክሬማኑሚ "depend" በአማርኛው የተመረኮዘ(hangs on) የሚል ትርጉምም ሊሰጠን ይችላል።
በመጨረሻም ሙስሊም ወገኖቼ ይሄን አይነቱን ተራና ለሙግት የማይቀርብን ሙግት እየቀዳችሁ ባታቀርቡና ለእውነተኛው ጌታ ኢየሱስ ነብሳችሁን አሳልፋችሁ ብትሰጡ እያልን እንዘጋለን።
ማጣቀሻዎች
[1] E.P Sanders, Jesus & Judaism, p.11
[2] John Dominic Crossan, Jesus:A Revolutionary Biography, p.145
ይህም ልዩነት ቤተ ክርስቲያንን የከዱት (referred to as the lapsi) የቀደሙት ክርስቲያኖች በአንዱ ጎራ ቢመለሱም ችግር የለውም ሲሉ በአንዱ ጎራ በፍጹም እነዚህ ከሐዲያን ወደ ቅድስት ቤተክርስቲያን መመለስ የለባቸውም ብለው ራሳቸውን በአቋመ ተአቅቦ አገለሉ። በተለይም Novatian የተባለ የRoman presbyter የዚህ እንቅስቃሴ ጠንሳሽ ነበር። እሱ እና ተከታዮቹ (Novatianists) ከቤተ ክርስቲያን ራሳቸውን በመለየት የራሳቸውን የእምነት ተቋም መሰረቱ። Novatian በሶስት ጳጳሳት ተሹሞ ራሱን እውነተኛ የቤተ ክርስቲያን ጳጳስ መሆኑን እንዲታወጅለት አስደረገ። የዛኔ ነው ቅዱስ ቆጵርያኖስ ብዕር እና ብራናውን በማገናኘት የቤተ ክርስቲያን ከፋፋይ ቡድኖች ማለትም Novatianistsቶች ላይ የግሳጼ እና የውግዘት ጡመራ በድርሳኑ ላይ የተገለጠው። የሮሜ ቤተ ክርስቲያንም Novatianistsቶችን መናፍቃን ብላ በመጥራት አዋጅን በሮሜ ባለው synod አሳወጀች። ይህንን ሐሳብ በመደገፍ በአራተኛው መቶ ክፍለ ዘመን የሚላኑ ቅዱስ አምብሮስ ተቃውሞውን በNovatianistsቶች ላይ ገልጿል። ወደ ዋናው ነጥባችን ስናልፍ schismatics ራሳቸውን በፈቃዳቸው ከክርስቶስ አካል ቆርጠው ማውጣታቸው ድነታቸውን እንዲሁ መተዋቸውን የሚያሳይ ነው በማለት ይናገራል (በምዕራፍ 5 ላይ ይመልከቱ) እንደ Novatians ያሉ ቅዱስ ቆጵርያኖስ ለቤተክርስቲያኗ አላማ እና ለነፍሳት ድነት አስፈላጊ እንደሆነ የተገነዘበውን የቤተክርስቲያንን ለተመላሾች ምህረትን የማድረግ እና የመስጠት ስልጣንን ክደው የቤተክርስቲያንን አንድነት የአወኩትን ሁሉ መናፍቃን በማለት ይጠራቸዋል። በዚህም ምክንያት ቤተ ክርስቲያንን እናት ያልሆነችላቸው ከፋፋይ ቡድኖች እግዚአብሔርም አባት እንደማይሆንላቸው በምዕራፍ 6 ላይ ሲናገር እንመለከተዋለን። በ3ኛው መቶ ክ/ዘ የአርጌንስ ደቀመዝሙር እንደነበር የሚነገርለት የቂሳርያው ጳጳስ ፊርሚሊያኖስ እነዚህ ከቤተ ክርስቲያን ራሳቸውን የቆረጡ መናፍቃን መንፈስ ቅዱስ የሌላቸው እና ከሌሎች አብያተ ክርስቲያናት ጋር ምንም አይነት መንፈሳዊ ግንኙነት እንደማይኖራቸው ይናገራል (Firmilian, Bishop of Caesarea in Cappadocia, to Cyprian, Against the Letter of Stephen, Epistle 74)
ስለዚህ የቅዱስ ቆጵርያኖስ ሐሳብ በቀጥታ ስለ Ecclesiological Exclusivism ወይም salvation is attainable only within the visible bounds of a specific institutional Church እያለ ሳይሆን ድነት ከእውነተኛው፣ ከሐዋርያት አስተምህሮ እና ከቃሉ ባፈነገጠ መልኩ ሊገኝ እንደማይችል እና እነዚህ ሐይሎች ራሳቸውን ሲቆርጡ ከሆነች specific institutional Church ብቻ ሳይሆን በምንፍቅናቸው እና በከፋፋይነታቸው ከክርስቶስ አካልም ራሳቸውን እንዳገለሉ የሚገልጽ ሐሳብ ነው። በዛው ክፍል ላይ ቅዱስ ቆጵርያኖስ ሁሉን አቀፋዊቷ በኖህ መርከብ በተመሰለችው ቤተ ክርስቲያን (mystical assembly) እንኳን እንደማይኖሩ የሚያስረዳ ሐሳብ የያዘ ነው። ስለዚህ የNovatianistsቶች ጥምቀት ሆነ ቅዱስ ቁርባን validity እንደሌለው የሚያሳይ ድርሳን ሁኖ እናገኘዋለን።
ይቀጥላል.......
« ከቤተ ክርስቲያን ውጪ ድነት የለም/extra Ecclesiam nulla salus »
ድነት ከቤተክርስቲያን ውጭ የለም የሚለውን ሐሳብ ከመመልከታችን በፊት ቤተ ክርስቲያን የሚለውን አገላለጽ መመልከቱ ጥሩ ነው። በAugsburg Confession(Part 11 Articles VII and VIII: Of the Church) ላይ ቸርች የቅዱሳን ስብስብ ወይም ጉባኤ እንደሆነች ይናገራል። ነገር ግን ይቺ ቤተ ክርስቲያን የምትታይ ወይም የማትታይ ልትሆን ትችላለች። የምትታየዋ ቤተክርስቲያን earthly manifest ያደረገች እና የእግዚያብሔር means of grace proclaimed የሚሆንባት እና administered የሆነች ነች። የማትታየዋ ቤተክርስቲያን ግን መንፈሳዊ የሆነች እና በእግዚአብሔር ብቻ የተገለጠች በ denominational lines በgeography ወይም time bound ያልተደረገችም ጭምር ናት። ቃሉ እና ቅዱሳት ምስጢራቶቹ ውጫዊ እና የሚታዩ ስለሆኑ የማትታየዋ ቤተክርስቲያን የምትመሠረትው እና የምትጸናው በምትታየዋ ቤተክርስቲያን ነው። ይህም ደግሞ በሁለቱ ስብስቦች መሐል ያለውን ጥብቅ ትስስር የሚያሳይ ሁኖ እናገኘዋለን። ሉተራኑ ቴዎሎጂያን Johann Gerhard ቤተክርስቲያንን በሁለት አይነት መገለጫዎች ይጠራታል። አንደኛ ሚስጥራዊ ወይም መንፈሳዊ አካል ያላት ወይም corpus mysticum እና ቅልቅላዊ አካል ወይም corpus permixtum በማለት ለሁለት አይነት መደቦች ያስቀምጣታል። የማትታየዋ ቤተክርስቲያን (corpus mysticum) ፍጹማዊት እና ከክርስቶስ ጋር እውነተኛ ህብረት ያላት ስትሆን ምትታየዋ ቤተክርስቲያን (corpus permixtum) ግን የእውነተኛ አማኞች እና የግብዞች (hypocrites) ወይም የከሐዲያን ቅልቅል ልትሆን ትችላለች። ስለዚህ ድነት necessarily በምትታየዋ ቤተክርስቲያን ብቻ አባል በመሆን ነው ማለት አይቻልም። በምትታየዋ ቤተክርስቲያን አባል መሆን ለድነት ዋስትና አይሰጥም። በምትታየዋ ቤተክርስቲያን ሁለቱም አባል ሊሆኑ ይችላሉ (both true believers and hypocrites) በማቴዎስ ወንጌል 13:24–30 ላይ እንክርዳዱም ሆነ ስዴውም በአንድ ቦታ ሲበቅሉና የእርሻው ባለቤት በቁጥር 30 ላይ "እስከ መከር ጊዜ አብረው ይደጉ" ሲል እንመልከታለን። ነገር ግን የሚለዩበት ዘመን በደረሰ ጊዜ እንክርዳዱን በእሳት አቃጥሉት ስንዴውን ግን ለይታችሁ በጎተራ አስገቡት በማለት ጌታች ኢየሱስ ክርስቶስ ስለፍርድ ቀን ሊሆን የሚችለውን በParable of the Wheat and Tares analogy ሰርቶ ሲያስረዳቸው እንመለከታለን። ይህም ማለት በአንዲት በምትታይ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ያሉ ሰዎች ሁሉ True Believers አይደሉም። ባጭሩ Just because someone is a member of a visible congregation does not guarantee they belong to the invisible Church (the true community of believers). Therefore, church membership should be viewed as a step toward Christian maturity, not a guarantee of salvation.
ይሄን ያህል ስለ ቤተ ክርስቲያን ካየን አሁን ደግሞ አከራካሪ ስለሆነው ጉዳይ ማለትም “extra Ecclesiam nulla salus” ("outside the Church there is no salvation") የሚለውን መርህ ጠለቅ ባለ ዳሰሳ ለመመልከት እንሞክር። ይህ አይነቱ ሐሳብ ለመጀመሪያ ጊዜ explicitly articulated የሆነው በካርቴጁ ቆጵርያኖስ (Cyprian of Carthage ድርሳን መሰረት ነው። ቅዱስ ቆጵርያኖስ ስለ ቤተ ክርስቲያን አንድነት በተሰኘው ድርሳኑ (De Unitate Ecclesiae) ምዕራፍ 6 ላይ « ቤተ ክርስቲያን እናት ያልሆነችለት እግዚአብሔር አባቱ ሊሆን አይችልም »
« No one can have God for his Father, who does not have the Church for his mother » -—De Unitate Ecclesiae, Chapter 6—-
ይሄንን ክፍል በመውሰድ አንዳንድ የቤተ ክርስቲያን ተቋማት (በተለይ የCatholic እና የEastern Orthodox Church) dogmatic interpretation ሲሰሩበት ይስተዋላሉ። «ከቤተ ክርስቲያን ውጪ ድነት የለም/ extra Ecclesiam nulla salus» የሚለው term በራሱ አከራካሪ እና አወዛጋቢ ሐሳብን የያዘ term ነው። An Introductory Dictionary of Theology and Religious Studies በሚለው መጽሐፍ ገጽ 439 ላይ Gary Macy የተባለ scholar ቤተ ክርስቲያን የሚለውን የቅዱስ ቆጵርያኖስን ሀረግ ለብዙ መቶ ዘመናት ቤተክርስቲያን ከድነት ጋር ያላትን ግንኙነት ለመግለጽ በተለይ በሁለት አይነት ፍታቴ ሲጠቀሙበት እንደቆዩ ይናገራል። ቅዱስ ቆጵርያኖስን እየተናገረ ያለው ስለ "Body of the Saved" ወይም the mystical assembly of all who are saved by God's grace ነው ወይስ The Church as a Specific Institution ነው እየጠቀሰልን ያለው የሚለው ሐሳብ እንደተጠቃሚው እየተተረጎመ የመጣ ሐሳብ ነው ይለናል። ስለዚህ አንዳንዶች Ecclesiam ወይም ቤተክርስቲያን የሚለው ሐሳብ የምትታየዋ ቤተክርስቲያን የሚገልጽ ነው ሲሉ አንዳንዶች ደግሞ የለም የማትታየዋ ቤተክርስቲያን ነው የሚገልጸው ብለው ያምናሉ። ይሄንን ውዝግብ ለጊዜው እናስቀምጠው እና ቅዱስ ቆጵርያኖስ ምን ለማለት ፈልጎ ነው የሚለውን ለመመልከት እንሞክር፣
ቅዱስ ቆጵርያኖስ ይህንን ድርሳን ሲከትብ በ3ኛው መቶ ክፍለ ዘመን በሮም ግዛት በክርስቲያኖች ላይ ከፍተኛ ስደትና በቤተክርስቲያን ውስጥ በተፈጠሩ ግጭቶች ወቅት ነበር። ቅዱስ ቆጵርያኖስ የቤተ ክርስቲያን አንድነት እጂጉን ያሳሰበው ጉዳይ ነበር። ከዚህም ረገድ አንድ እምነት ነበረው እሱም ከቤተ ክርስቲያን ተለይቶ መውጣት ማለት ልክ ከክርስቶስ አካል እንደመለየት መሆኑን ይናገራል። በዛን ዘመን Schism አንዱ አስጊ እና የቤተ ክርስቲያን አንድነት ላይ ትልቅ ቁርሾ ፈጣሪ እንቅስቃሴ እንደሆነ ያምንም ነበር። በተለይ 249–251 ዓ.ም በንጉሠ ነገሥት Decius የግዛት ዘመን ክርስቲያኖች ከባድ ስደት ገጥሟቸው ነበር፣ ይህም በብዙዎች ላይ የደረሰው መከራ እና ስደት ብዙ ክርስቲያኖች ወደ ክህደት መንገድ እንዲያመሩ አድርጓቸዋል። ስደቱ ከቀዘቀዘ በኋላ ቤተ ክርስቲያን በዘመኑ ትልቅ መናወጥን አስከትሎ ነበር።
ያለ ፍቃዷ የተደፈረች ሴት እና መጽሐፍ ቅዱስ?
ሙስሊም ወገኖች መጽሐፍ ቅዱስን ለመተቸት እና የአምላክ ቃል ላለማድረግ በብዙ ሲሟገቱ ይስተዋላል። ይሄን ሰሞን አንድ ኡስታዝ ከአንዲት ክርስቲያን ጋር ሙግት ሲያደርግና በዛው በሚወያዩበት ጥቅስ ላይ በመመርኮዝ የተጻፈ ጽሑፍ በማህበራዊ ድረገጾች ላይ ሲዘዋወር አየሁ። ሙግቱ በብዙ ወፍሮ ከውስጥ የከሰመ ሙግት እንደሆነ የጠያቂያችንን ሙግት ያየ ሰው የሚያስተውለው ነገር ነው። እንዲህ ሲል ይጀምራል፦
ጠያቂው
መጽሐፍ ቅዱስ ሴቶችን ዝቅ ያደርጋል። እንደ እቃም ያያቸዋል። ለምሳሌ፦ በዘዳግም መጽሐፍ ላይ ስለ አንዲት የታጨች ሴት ያወራናል። እንዲህ ይላል፦
ዘዳግም 22
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
²⁷ በሜዳ ባገኛት ጊዜ የታጨችው ልጃገረድ ጮኻለችና፥ የሚታደጋትም አልነበረምና።
²⁸ ማናቸውም ሰው ድንግልና ያላትን ያልታጨች ልጃገረድ ቢያገኝ፥ ወስዶም ቢደርስባት፥ ቢያገኙትም፥
²⁹ ያ የደረሰባት ሰው አምሳ የብር ሰቅል ለብላቴናይቱ አባት ይስጥ፤ አስነውሮአታልና ሚስት ትሁነው፤ በዕድሜውም ዘመን ሁሉ ሊፈታት አይገባውም።
➨በዚህ ክፍል ላይ እንደምናየው ከሆነ ይህቺ ልጅ ቆንጆ ብትሆንና ያሰው ደግሞ ብር ኖሮት ሊያገባት ተመኝቶ ቢደርስባት ያለ ምንም የቤተስብ ፍቃድ ይህ ሰው ልጅቷን ያገባል። እርሷንም ለመውሰድ ገንዘቡን ብቻ ለቤተሰቧ ሰጥቶ ያገባታል። እውነት ይህ የአምላክ ፍትህ መጽሐፍ ቃል ነው ወይ? ይህቺ ልጅ ከተደፈች በኋላ ታገባዋለች አልፈልግም የማለትም ብቃት የላትም? ፍትህ የለበትም ይገርማል!?
መልስ
ይህ ኡስታዝ ያነሳው ሙግት የመጽሐፍ ቅዱስን የአውድ ሥነ-አፈታት መርሖን ካለማወቅ የተፈጠረበት ጥያቄ መሆኑን እናያለን። የእርሱም ጥያቄ በእውነቱ ከጠቀሰው ጥቅስ ጋር ይያያዛልን? የሚለውን ራሱ የጠቀሰውን የመጽሐፍ ክፍል በማብራራት እንጀምራለን። ክፍሉ እንዲህ ይላል፦
ዘዳግም 22
¯¯¯¯¯¯¯¯¯
²⁷ በሜዳ ባገኛት ጊዜ የታጨችው ልጃገረድ ጮኻለችና፥ የሚታደጋትም አልነበረምና።
²⁸ ማናቸውም ሰው ድንግልና ያላትን ያልታጨች ልጃገረድ ቢያገኝ፥ ወስዶም ቢደርስባት፥ ቢያገኙትም፥
²⁹ ያ የደረሰባት ሰው አምሳ የብር ሰቅል ለብላቴናይቱ #አባት#ይስጥ፤ #አስነውሮአታልና ሚስት #ትሁነው፤ በዕድሜውም ዘመን ሁሉ #ሊፈታት አይገባውም።
➨ይህ ክፍል እየተናገረ ያለው ከእርስዋም ጋር የተኛ ሰው ልጅቷን አስነውረሯታል። ታዲያ ስላስነወራት ለአባቷ አምሳ ሰቅል(ማለት 800 ግራም ብር ማለት ነው። ይህ ክፍያ በዚያ ዘመን ለነበረ ሰው እጅግ ውድ ክፍያ ነው፡፡) ይሄ ክፍያ ግን የሚተገበረው ለአባቷ ስም መጥፋት እንጂ እርሱ ሀብታም ሆኖ ልጅቷን ለመውሰድ (ለማግባት) የሚደረግ ክፍያ አይደለም። ለዛም ነው በጥቅሱ ላይ <<“ያ የደረሰባት ሰው አምሳ የብር ሰቅል ለብላቴናይቱ አባት ይስጥ፤>> ብሎ አስደንግጎ ነገረን። ታዲያ ይህ ክፍያ በዚያን ዘመን ለነበረና በህጉ ለሚተዳደር ሰው ግዴታ ለአባቷ ሴት ልጁን ስለደረሰባት ይሄን ያህል ብር ይሰጥ ነበር። የክፍሉ ጥቅስ ክፍያው ለአባቷ ነው ብሎ ሳለ፤ ለጋብቻ ፍቃድ ለልጅቷ ነው ክፍያው ማለት ትዝብት ውስጥ አይከተንም ወይ ኡስታዝ?
?ሁለተኛው ጥያቄው፦
ሙሉ የመጽሐፍ ቅዱስን አስተምሮ ካለማገናዘብ እንደመነጨ እንመለከታለን። ሚስት ትሆነዋለች የሚለው አገላለፅን በተመለከተ በህጉ መሠረት አባቷ እና እሷ ከተስማሙ ብቻ እንደሆነ በሌሎች ተመሳሳይ ክፍሎች ላይ እንመለከታለን። ለፍትህ ፍትህ እንደሚባለው ይህንን ክፍል ከዛው ከሙሴ መጽሐፍ ህግ ከሆነው ዘጸአት 22:16-17 ጋር በማነፃፀር እንመልከት።እንዲህ ይላል፦
ዘጸአት 22
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹⁶ ሰው ያልታጨችውን ድንግል ቢያስታት፥ ከእርስዋም ጋር ቢተኛ፥ ማጫዋን ሰጥቶ ሚስት ያድርጋት።
¹⁷ አባትዋም እርስዋን እንዳይሰጠው ፈጽሞ እንቢ ቢል እንደ ደናግል ማጫ ያህል ብር ይክፈላት።
➨ከዘዳግም 22፥27-29 ጋር ተመሳሳይ ድርጊት በዘጸአት መጽሐፍ ላይ እንመለከታለን። በጥንት ዘመን አንድ ሰው አንዲትን ድንግል ሴት ለማግኘት ብሎ ያለ ጋብቻ ቢገናኛት የስም ካሳ ገንዘብ ለወላጆቿ ይከፍላል፤ ከዛም በፍቃድ እንደ ስርአቱ ይጋባሉ። ይሄ ህግ ግን የሚፀናው የአታላዩ ጉዳይ ተመርምሮ በቤተሰቡ ውስጥ የፈቃደኛነት ስሜት ከተፀባረቀ ብቻ ልጅቷን በአባት በኩል እንዲያገባ ይደረጋል፥ ምክንያቱም አባት የቤቱ ራስ ነበረና። ለምሳሌ፦ አንዲት ሸጋ ድንግል ሴት አይቶ ቢደርስባት ለስም መካሻ ይሆን ዘንድ የሀገሩ ሽማግሌዎችና ታላላቅ የሐይማኖት አባቶች ተሰብስበው እንደ ባህሉ እና እንደ ወጉ መቀጫውን እንዲከፍል ለአባቷም እንዲያቀርብ ያደረጋሉ። ውሳኔውም የልጅቷ ፍቃድ በአባቷ በኩል ይጠየቃል፤ በመጨረሻ በህዝቡ ዘንድ ይነገራል። ይህ ስርአት በሀገሬ ገጠራማው አካባቢ ላይ ይገኛል።
➨ታዲያ ክፍሉ እንደሚለው ከሆነ ጋብቻው የልጅቷ ፍቃድ በአባቷ በኩል እንደሚገኝ ነግሮን ሃቁ ይህ ሆኖ ሳለ የኡስታዙ ቅጥፈት ምን የሚሉት ነው?..የልጅቷም ፍቃድ የለበትም ማለቱስ ኪስ ወለድ ሙግት አይሆንበትምን? ትዝብቱን ለአንባቢው ተዋለሁ።
"እኛ ግን እግዚአብሔር ልባቸው ለታወረባቸው ሰዎች ብርሃኑን ይገልጥላቸው ዘንድ እንጸልይ።"
ተባረኩ።
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።
@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna
#ኢትዮጵያ
Last updated 2 months, 3 weeks ago
Last updated 2 months, 2 weeks ago
ይህ ስለ Manchester United መረጃዎችን የሚያገኙበት የ Telegram ቻናል ነው 🇪🇹
--------------------------------------------------------------
☞︎| ስለ ማንቸስተር ዩናይትድ ትኩስ መረጃዎች
☞| ቀጥታ ስርጭቶች ከየስታድየሞቹ
☞| የዝውውር ዜናዎች
☞| ስለ ማንችስተር ዩናይትድ ታሪኮች
📩 ለማስታወቂያ ስራ DM :- @Marcoabdu
Last updated 1 month, 1 week ago