Dive into the Ultimate Free Library: Your One-Stop Hub for Entertainment!

Sheger ሸገር 102.1(Sheger 102.1FM)

Description
ሸገር 102.1 መስከረም 23፣2000 ዓ.ም ሥራ የጀመረ የመጀመሪያው የኢትዮጵያ የግል ኤፍ ኤም ሬዲዮ ጣቢያ ነው፡፡

ጣቢያችን ለማንም ባለመወገን ለሁሉም በታማኝነትና በመልካም ሥነ ምግባር መልካም አገልግሎት በመስጠት የሚያምንና ለእነዚህም እሴቶች ትልቅ ክብር የሚሰጥ ሬዲዮ ጣቢያ ነው፡፡

ሸገር የእናንተ ነው!

https://bit.ly/33KMCqz
Advertising
We recommend to visit

"ይህ የቴሌግራም ቻናሌ ግንቦት1/2011ዓም የተከፈተ ነው። የእኔን የስልክ ወጪ ጨምሮ አገልግሎቴን መደገፍ የምትፈቅዱ ጓደኞቼ በ
👉🏿 https://donorbox.org/zemedemedia እና
👉🏿 https://www.paypal.com/paypalme/ZemedkunB በኩል ማገዝ ትችላላችሁ። በተረፈ ለቤተ ክርስቲያኔና ለኢትዮጵያ ሀገሬ የሚጠቅመውን ሁሉ አበረክት ዘንድ አብዝታችሁ ጸልዩልኝ።

Last updated 1 month, 1 week ago

The first Telecom operator in Ethiopia https://t.me/EthiotelecomChatBot

Last updated 1 month, 2 weeks ago

እንኳን ወደ ውዱ 4-3-3 Film ቻናላችን በሰላም መጣቹ

አዳዲስ እና የድሮ እንግሊዘኛ/አማርኛ/ህንድ/ቱርክ ፊልሞችን እና ከ1000 በላይ ተከታታይ ፊልሞችን የምታገኙበት ቻናል ነው

ለማስታወቂያ ስራ - @Abusheymc

ሃሳብ አስታየት ካሎት - @Abushecbot

Buy ads: https://telega.io/c/Films_433

Last updated 1 month ago

hace 2 días, 11 horas

ሚያዝያ  26፣2016

የባንኮች የሳይበር ጥቃት ጉዳይ!

https://youtu.be/vdTpsL9sAHU

#Ethiopia #ShegerWerewoch  #Bank_Cyber_Attack #ባንኮች #የሳይበር_ጥቃት

የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…

Telegram:  https://tinyurl.com/yc6tfzsw

Youtube: http://tiny.cc/ShegerFM1021Radio

Website: https://www.shegerfm.com/

Tiktok: https://bit.ly/44Dd6Il

YouTube

የባንኮች የሳይበር ጥቃት

ሚያዝያ 26፣2016 የባንኮች የሳይበር ጥቃት ጉዳይ! ተህቦ ንጉሴ #Ethiopia #ShegerWerewoch #Bank\_Cyber\_Attack #ባንኮች #የሳይበር\_ጥቃት የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ… Telegram: https://tinyurl.com/yc6tfzsw Youtube: http://tiny.cc/ShegerFM1021Radio Website: https://www.shegerfm.com/…

hace 2 días, 12 horas

ሚያዝያ 26፣2016

ለፍትሀዊነቱ፤ ልዩ ችሎት ወይስ ልዩ ፍርድ ቤት?

https://youtu.be/UxdLEcZ1dhA

#Ethiopia #ShegerWerewoch #የሽግግር_ፍትህ_ፖሊሲ #ልዩ_ችሎት

የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…

Telegram: https://tinyurl.com/yc6tfzsw

Youtube: http://tiny.cc/ShegerFM1021Radio

Website: https://www.shegerfm.com/

Tiktok: https://bit.ly/44Dd6Il

YouTube

ለፍትሀዊነቱ፤ ልዩ ችሎት ወይስ ልዩ ፍርድ ቤት?

ሚያዝያ 26፣2016 ለፍትሀዊነቱ፤ ልዩ ችሎት ወይስ ልዩ ፍርድ ቤት? ትዕግስት ዘሪሁን #Ethiopia #ShegerWerewoch #የሽግግር\_ፍትህ\_ፖሊሲ #ልዩ\_ችሎት የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ… Telegram: https://tinyurl.com/yc6tfzsw Youtube: http://tiny.cc/ShegerFM1021Radio Website: https://www.shegerfm.com/…

hace 2 días, 13 horas

ሚያዝያ 26፣2016

እርድ፤ እንዴት ነው መከወን ያለበት?

https://youtu.be/hNQP7ma9tKQ

#Ethiopia #ShegerWerewoch #ቅርጫ #በሬ #እርድ #ፋሲካ

የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…

Telegram: https://tinyurl.com/yc6tfzsw

Youtube: http://tiny.cc/ShegerFM1021Radio

Website: https://www.shegerfm.com/

Tiktok: https://bit.ly/44Dd6Il

YouTube

እርድ እንዴት ነው መከወን ያለበት?

ሚያዝያ 26፣2016 እርድ እንዴት ነው መከወን ያለበት? ምንታምር ፀጋው #Ethiopia #ShegerWerewoch #ቅርጫ #በሬ #እርድ #ፋሲካ የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ… Telegram: https://tinyurl.com/yc6tfzsw Youtube: http://tiny.cc/ShegerFM1021Radio Website: https://www.shegerfm.com/ Tiktok:…

hace 1 semana, 5 días

ሚያዝያ 16፣2016

ወባ እና ተቅማጥ የመሳሰሉ በአየር ንብረት ለውጥ የተነሳ የሚደርሱ በሽታዎች ያላቸውን የተጽዕኖ መጠን የሚያስረዳ የዳሰሳ ትንተና ሊሰራ መሆኑ ተሠማ፡፡

https://tinyurl.com/m3x42b8y

ንጋቱ ሙሉ

#Ethiopia #ShegerWerewoch #ወባ #ተቅማጥ #አየር_ንብረት_ለውጥ

የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…

Telegram: @ShegerFMRadio102_1

Youtube: http://tiny.cc/ShegerFM1021Radio

Website: https://www.shegerfm.com/

Tiktok: https://bit.ly/44Dd6Il

hace 1 semana, 5 días

ሚያዝያ 16፣2016

በአዲስ አበባ በአፈር እና ግንብ መናድ አደጋ ስድስት ሰዎች ሞቱ፡፡

አደጋው ያጋጠመው በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ወረዳ 12 ልዩ ስሙ ጠሮ መስጅድ እየተባለ በሚጠራው አካባቢ ዛሬ ሌሊት 11:00 ሰዓት ላይ ነው ተብሏል፡፡

የግለሰብ መኖሪያ ቤት አፈርና ግንብ ተንዶ በደረሰው በዚህ አደጋ ህይወታቸው ያለፉ ሰዎች በመኖሪያ ቤታቸው ተኝተው የነበሩ ናቸው ተብሏል።

በአደጋው ምክንያት በሰው ህይወት እና በንብረት ላይ የደረሰውን ተጨማሪ ዝርዝር መረጃ ወደፊት እናሳውቃለን ሲሉ የአዲስ አበባ አደጋ ስጋትና ስራ አመራር ኮሚሽን የህዝብ ግንኙነት ባለሙያ አቶ ንጋቱ ማሞ ተናግረዋል።

ንጋቱ ረጋሳ

#Ethiopia #ShegerWerewoch #አደጋ #ጠሮ_መስጅድ #የቤት_መናድ

የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…

Telegram: @ShegerFMRadio102_1

Youtube: http://tiny.cc/ShegerFM1021Radio

Website: https://www.shegerfm.com/

Tiktok: https://bit.ly/44Dd6Il

hace 1 semana, 6 días

ሚያዝያ  15፣2016

አዲሱ የካላዛር ህክምና ወደ ምዕራፍ ሁለት የክሊኒካል ሙከራ መሸጋገሩ ተሰማ፡፡

ካላዛር  ከወባ ቀጥሎ በዓለም ላይ በጥገኛ ተህዋሲያን የሚተላለፍ ገዳዩ በሽታ ነው፡፡

በሽታው  ትኩሳት፣ የክብደት መቀነስ፣ ከልክ ያለፈ የጣፊያና የጉበት እድገት ያስከትላል፣  በጊዜው ካልታከመም ለሞት ሊዳርግም ይችላል፡፡

ፈውስ ትኩረት ለተነፈጉ በሽታዎች ኢኒሺዬቲቭ ወይንም ዲ ኤን ዲ የጤና ምርምር የተባለ ተቋም እና አጋሮቹ  ለዚህ በሽታ የሚያደርጉት የመድሃኒት ፍለጋ ምእራፍ ሁለት የክሊኒካል ሙከራ ደረጃ መሸጋገሩን ተናግሯል፡፡

ወደ ምእራፍ ሁለት የክሊኒካል ሙከራ መሸጋገሩ የተነገረው መድሃኒቱ ኢትዮጵያ ውስጥ አዲስ፣ አስተማማኝ፣ ለአጠቃቀም ቀላል እና ለህሙማን ምቹ የሆነ በአፍ የሚወሰድ ነው ተብሏል፡፡

የካላዛር መድሃኒት ለማስገኘት የሚያካሂዱት ምርምር አዲሱ የካላዛር ህክምና በእጅጉ ትኩረት የተነፈገውንና ለማከምም አስቸጋሪ የሆነውን የካላዛር በሽታ ለማዳን በሚደረገው ርብርብ ስር ነቀል ለውጥ ለማምጣት ያግዛል ተብሎለታል፡፡   

በአፍሪካ አሁን እየተሰጠ የሚገኘው የካላዛር ህክምና በሆስፒታል ውስጥ በየቀኑ ለ17 ቀናት የሚወሰድ ከፍተኛ ህመም የሚፈጥር ክትባት ሲሆን ልብን፣ጉበትን እና ቆሽትን በመጉዳት ለህይወት አስጊ የሆኑ የጎንዮሽ ጉዳቶችን ሊያስከትል ይችላል።

በአንፃሩ በኢትዮጵያ በምርምር ላይ የሚገኘው አዲሱየ“LXE408”በአፍ  የሚወሰድ መድሀኒት አሁን ከሚሰጠው ህክምና የበለጠ ፈዋሽና አስተማማኝ እንደሚሆን ይጠበቃል ተብሏል።

“ኢትዮጵያ እንደ አንድ ካላዛር የተንሰራፋበት አገር፣አዳዲሶቹ ኬሚካላዊ ምርምሮች ወደሚካዱበት ምእራፍ ሁለት ክሊኒካዊ ሙከራ መግባቷ ትልቅ እምርታ ነው ሲሉ በጎንደር ዩኒቨርሲቲ የካላዛር በሽታ ጥናትና ህክምና ማዕከል ውስጥ በሚካሄደው በዚህ ክሊኒካል ሙከራ ተባባሪ ተመራማሪ የሆኑት ዶ/ር እሌኒ አየለ አስረድተዋል፡፡

“አሁን ላይ በኢትዮጵያ ያሉት የካላዛር ህክምና አማራጮች ከፍተኛ የሆነ ውስንነት ያለባቸው፣ ጎጂ ክትባትን ግዴታ የሚያደርጉ፣ እጅግ ቀዝቃዛ የህክምና ቁሳቁሶች ጥቅም ላይ የሚውሉባቸው እንዲሁም ህሙማን አገልግሎቶቹን ፍለጋ የረጅም ርቀት ጉዞ የሚጠይቁ እና ለረጅም ጊዜም ሆስፒታል ውስጥ ተኝተው የሚታከሙባቸው ናቸው" ሲሉም ተመራማሪዋ ጠቅሰዋል፡፡

በምርምሩ ከሰመረ ላይ ህክምናው ፈዋሽ፣ የጎንዮሽ ጉዳቱ አነስተኛ የሆነና ህሙማን በመኖሪያ ቤታቸው ፣አቅራቢያ በሚገኙ የመጀመሪያ ደረጃ የጤና ተቋማት ማግኘት ይትላሉ ሲሉ ተመራማሪዋ አስረድተዋል፡፡

ከምንም በላይ በሽታውን እስከወዲያኛው ለማስወገድ የሚደረገውን ጥረት በእጅጉ ያግዛል ተብሏል፡፡

አዲሱ ህክምና በኢትዮጵያ የመድሃኒትሙከራ መስፈርት መሰረት የሚካሄድ ሲሆን በየቀኑ የሶዲየም ስቲቦግሉኮኔት እና ፓሮሞማይሲን ድብልቅ መርፌዎች ለ17 ቀናት ይሰጣል።

ለዚህም ይረዳ ዘንድ ከ18 እስከ 44 ዓመት … https://tinyurl.com/yck2pa6y

#Ethiopia #ShegerWerewoch  #የካላዛር_ህክምና #ወባ #የካላዛር_በሽታ

የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…

Telegram:  @ShegerFMRadio102_1

Youtube: http://tiny.cc/ShegerFM1021Radio

Website: https://www.shegerfm.com/

Tiktok: https://bit.ly/44Dd6Il

hace 2 meses, 2 semanas

የካቲት 14፣2016

በዘመን ባንክ በኩል ለሚደረጉ አለም አቀፍ ንግዶች የአለም አቀፉ የፋይናንስ ኮርፖሬሽን(IFC) የ30 ሚሊዮን ዶላር መተማመኛ ለመስጠት ተስማማ።

ስምምነቱም በዛሬው ዕለት በዘመን ባንክ ዋና መስሪያ ቤት በባንኩ ዋና ስራ አስፈፃሚ ደረጀ ዘበነ እና በአለም አቀፉ የፋይናንስ ኮርፖሬሽን የኢትዮጵያ ቢሮ ሃላፊ ማዳሎ ሚኖፉ ተፈርሟል።

በዓለም አቀፍ ንግድ ውስጥ የግብይት ስርዓት መዛባት ሲያገጥም፣ በሽያጭ እና ገዢ መካከል አለመተማመን ሲኖር ባንኮች እምነት እንዲጣልባቸው ጥሬ ገንዘብ በመመደብ ጭምር ድጋፍ ያደርጋሉ ተብሏል።

ይህ ደግሞ በባንኮች ላይ ጫና እንደሚፈጥር ያስረዱት የዘመን ባንክ ስራ አስፈፃሚ ደረጀ ዘበነ ይህ በኢትዮጵያ የፀጥታ ችግር ባጋጠመባቸው ወቅቶች ጎልቶ ታይቷል ብለዋል።

በዚህ ስምምነት መሰረት የአለም አቀፉ የፋይናንስ ኮርፖሬሽን የዘመን ባንክን የትሬድ ፋይናንስ (የወጪና ገቢ ንግድ ገንዘብ አቅርቦት) እንቅስቃሴ ለማጠናከርና በኢትዮጵያ ላሉ የወጪ ንግድ ላይ ለሚሰሩ ድርጅቶች አዲስ የንግድ ትስስርን ለመፍጠር የ30 ሚሊዮን ዶላር ዋስትና ያቀርባል ተብሏል።

ፕሮግራሙ ለባንኩ የንግድ ፋይናንስ ድጋፍ በማቅረብ የኢትዮጵያን የወጪና ገቢ ንግድ ለመደገፍ ብሎም አህጉራዊ ንግድን ማበረታታትን አላማው ያደረገ ነው ሲባል ሰምተናል።

ስምምነቱ ዓለም አቀፋዊ የኢኮኖሚ አለመረጋጋት በሚኖርበት ወቅት በገቢና ወጪ ንግድ ላይ የተሰማሩ የንግድ አጋሮችንም ሆነ የባንኩን ስጋት በእጅጉ እንደሚቀንስ የዘመን ባንክ ዋና ስራ አስፈፃሚ የሆኑት አቶ ደረጀ ዘበነ አስረድተዋል፡፡

ይሀ ፕሮግራም የወጪ ንግድ ፋይናንስ እንዳይስፋፋ የሚገድቡ እከሎችን ወይም ለዘርፉ ፈታኝ የሆኑ ስጋቶችን ለመቀነስ የሚረዳ ነው ተብሎለታል።

ለወጪና ገቢ ንግድ ዘርፍ ፋይናንስ የማቅረብ አቅምንም ያሰፋል ሲባልም ሰምተናል።

ዘመን ባንክ ባንክ ከዓለም አቀፉ የፋይናንስ ኮርፖሬሽን ያገኘው የ30 ሚሊዮን ዶላር የአለም አቀፍ ንግድ ዋስትና፤ ኮርፖሬሽኑ ለአፍሪካ ሀገራት መሰል ስራ ብሎ የያዘው 1 ቢሊዮን ዶላር አካል መሆኑ ተነግሯል።

ከዘመን ባንክ ጋር በአጋርነት ለመስራት የተፈራረመው አለም አቀፉ የፋይናንስ ኮርፖሬሽን፤ የዓለም ባንክ አባል ሲሆን በማደግ ላይ ያለውን የግል ዘርፍ ላይ የተለየ ትኩረት በማድረግ የሚደግፍ የልማት ተቋም መሆኑን ሰምተናል፡፡

ባለፈው ዓመት ብቻ በማደግ ላይ ባሉ ሀገሮች ለሚካሄዱ የግል ኩባንያዎችና የገንዘብ ተቋማት 43.7 ቢልዮን የአሜሪካ ዶላር አበርክቷል ተብሏል፡፡

#Ethiopia #ShegerWerewoch #ዘመን_ባንክ #IFC

የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…

Telegram: https://tinyurl.com/yc6tfzsw

Website: https://www.shegerfm.com/

Tiktok: https://bit.ly/44Dd6Il

hace 2 meses, 2 semanas
የካቲት 14፣2016 - የገበያ ቅኝት

የካቲት 14፣2016 - የገበያ ቅኝት

በአዲስ አበባ ከተማ የሸቀጦች ዋጋ መናር የነዋሪውን ህይወት እንደፈተነው ተደጋግሞ ይነገራል።

ከቅርብ ጊዝ ወዲህ ጤፍን ጨምሮ ሌሎች ሸቀጦች በአንድ ጀንበር ዋጋቸው ከፍ ማለቱ የሚታወቅ ነው፡፡

ነገር ግን ከሰሞኑ የሽንኩርት እና የቲማቲም ዋጋ እቀነሰ ቢሆንም የጤፍ ዋጋ ጨምሯል፡፡

ጤፍ ከወራት በፊትም ከስድስት ሺህ ብር ወደ አስራ ሁለት ሺህ፣ አስራ ሶስት ሺህ እና አስራ አራት ሺህ ብር በአንድ ጊዜ የዋጋ ጭማሪ አሳይቷል።

ሸገር በአንዳንድ ወፍጮ ቤቶች ተዘዋውሮ ጤፍ ሲገበያይ የሰነበተበትን ዋጋ ተመልክቷል፡፡

በዚህም በየደረጃው ከ135 ብር እስከ 145 ብር በኪሎ እየተሸጠ መሆኑን አይቷል፡፡

እዚሁ በሀገር ቤት ተመርቶ የሚቀርበው ጤፍ ለምን በዚህ ልክ ተወደደ?

ለምንስ የአቅርቦት እና የፍላጎት አለመጣጣም ሊያጋጥም ቻለ?

ሸገር የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ንግድ ቢሮን ጠይቋል።

http://tinyurl.com/yurvzthc

ፋሲካ ሙሉወርቅ

#Ethiopia #ShegerWerewoch #ሽንኩርት #ቲማቲም #የጤፍ_ዋጋ

የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…

Telegram: https://tinyurl.com/yc6tfzsw

Website: https://www.shegerfm.com/

Tiktok: https://bit.ly/44Dd6Il

hace 2 meses, 2 semanas

የካቲት 14፣2016

ወጋገን ባንክ “ወጋገን ሞባይል” የተሰኘ የሞባይል ባንኪንግ አገልግሎት መተግበሪያ በይፋ ስራ አስጀመረ፡፡

ባንኩ አገልግሎቱን በይፋ ያስጀመረው በድሬደዋ ከተማ ባዘጋጀው ስነ ሥርዓት ላይ ነው፡፡

በዝግጅቱ ላይ ንግግር ያደረጉት የወጋገን ባንክ ኢንተርፕራይዝ አገልግሎቶች ምክትል ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ የኋላሸት ዘውዱ ወጋገን ሞባይል መተግበሪያ ፈጣን እና ደህንነቱ የተጠበቀ መሆኑን አስረድተዋል፡፡

መተግበሪያው ደንበኞች ከባንክ ወደ ባንክ ገንዘብ ማስተላለፍ እና ክፍያዎችን በምቹ ሁኔታ ለመፈፀም ያስችላል ብለዋል፡፡

ደንበኞች የወጋገን ሞባይል መተግበሪያን ከፕሌይ ስቶር ወይም አፕ ስቶር በማውረድ አገልግሎቱን ማግኘት ይችላሉ ተብሏል፡፡

መተግበሪያው በአምስት ቋንቋዎች ማለትም በአማርኛ፣ እንግሊዝኛ፣ ኦሮምኛ፣ ትግርኛ እና በሶማልኛ ይሰራል ተብሏል፡፡

ባንኩ እንደ አማራጭ ደንበኞች በማንኛውም ዓይነት ስልክ ወደ *866# በመደወል በአማርኛና በእንግሊዝኛ የሞባይል ባንኪንግ አገልግሎቱን ያለ ኢንተርኔት መጠቀም እንደሚችሉ ምክትል ዋና ስራ አስፈፃሚው አስረድተዋል፡፡

ባንኩ በመተግበሪያው ማስመረቂያ ስነስርዓት ላይ  ማህበራዊ ኃላፊነቱን ለመወጣት በድሬደዋ ከተማ ለሚገኙት አሰገደች አስፋው የአረጋውያን መንከባከቢያ ማቋቋሚያ ድርጅት እና ዳዊት ለአረጋውያን በጎ አድራጎት ማህበር ለተሰኙ የበጎ አድራጎት ድርጅቶች ለእያንዳንዳቸው የብር 250,000 በድምሩ ብር 500,000 ድጋፍ አድርጓል፡፡

በ1989 ዓ.ም  በ30 ሚሊዮን ብር የተከፈለ ካፒታል የተመሰረተው ወጋገን ባንክ በአሁኑ ወቅት የተከፈለ ካፒታሉ  4.5 ቢሊዮን ብር ፣ አጠቃላይ ካፒታሉ ከ 8.2 ቢሊዮን ብር በላይ እንዲሁም አጠቃላይ ሀብቱ ደግሞ ከ 58 ቢሊዮን ብር በላይ ደርሷል ብሏል::

#Ethiopia #ShegerWerewoch #ወጋገን_ሞባይል

የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…

Telegram: https://tinyurl.com/yc6tfzsw

Website: https://www.shegerfm.com/

Tiktok: https://bit.ly/44Dd6Il

hace 2 meses, 3 semanas

የካቲት 7፣2016

ኢትዮጵያ ከዚምባብዌ እና ከአንጎላ መንግስት ጋር አብሮ ለመስራትና ለመልማት የሚያስችላትን ውል አሰረች፡፡

የውጪ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ ከሁለቱ ሀገራት ጋር በተለያዩ የስራ ዘርፎች አብሮ ለመስራት የሚያስችላቸውን ስምምነት አዲስ አበባ ላይ ከሁለቱ ሀገራት ከአቻቸው ጋር ተፈራርመዋል፡፡

ስምምነቱ በንግድ፣ በቱሪዝም እና በግብርና የስራ መስክ አብሮ ለመስራት ያስችላል ተብሏል፡፡

ስምምነቱ የተደረገው እየተካሄደ ባለው የአፍሪካ ህብረት ጉባኤ በተደረገ የጎንዮሽ ምክክር ላይ ነው።

አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ ከዚምባቡዌ አቻቸው አምባሰደር ፍሬድሪክ ሻቫ ጋር ባደረጉት ውይይት ላይ ኢትዮጵያ የባህር በር ለማግኘት በቅርቡ ስለተፈራረመችው የመግባቢያ ሰነድም መምከራቸውን ሰምተናል፡፡

#Ethiopia #ShegerWerewoch #አምባሳደር_ታዬ_አፅቀስላሴ #ዚምባቡዌ #አንጎላ

የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…

Telegram: https://tinyurl.com/yc6tfzsw

Website: https://www.shegerfm.com/

Tiktok: https://bit.ly/44Dd6Il

We recommend to visit

"ይህ የቴሌግራም ቻናሌ ግንቦት1/2011ዓም የተከፈተ ነው። የእኔን የስልክ ወጪ ጨምሮ አገልግሎቴን መደገፍ የምትፈቅዱ ጓደኞቼ በ
👉🏿 https://donorbox.org/zemedemedia እና
👉🏿 https://www.paypal.com/paypalme/ZemedkunB በኩል ማገዝ ትችላላችሁ። በተረፈ ለቤተ ክርስቲያኔና ለኢትዮጵያ ሀገሬ የሚጠቅመውን ሁሉ አበረክት ዘንድ አብዝታችሁ ጸልዩልኝ።

Last updated 1 month, 1 week ago

The first Telecom operator in Ethiopia https://t.me/EthiotelecomChatBot

Last updated 1 month, 2 weeks ago

እንኳን ወደ ውዱ 4-3-3 Film ቻናላችን በሰላም መጣቹ

አዳዲስ እና የድሮ እንግሊዘኛ/አማርኛ/ህንድ/ቱርክ ፊልሞችን እና ከ1000 በላይ ተከታታይ ፊልሞችን የምታገኙበት ቻናል ነው

ለማስታወቂያ ስራ - @Abusheymc

ሃሳብ አስታየት ካሎት - @Abushecbot

Buy ads: https://telega.io/c/Films_433

Last updated 1 month ago