ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።
@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna
#ኢትዮጵያ
Last updated 2 months, 3 weeks ago
Last updated 2 months, 2 weeks ago
ይህ ስለ Manchester United መረጃዎችን የሚያገኙበት የ Telegram ቻናል ነው 🇪🇹
--------------------------------------------------------------
☞︎| ስለ ማንቸስተር ዩናይትድ ትኩስ መረጃዎች
☞| ቀጥታ ስርጭቶች ከየስታድየሞቹ
☞| የዝውውር ዜናዎች
☞| ስለ ማንችስተር ዩናይትድ ታሪኮች
📩 ለማስታወቂያ ስራ DM :- @Marcoabdu
Last updated 1 month, 1 week ago
ቤቲንግ በተደጋጋሚ እየተበሉ ተቸግረዋል ?
100% Sure/እርግጠኛ የሆኑ የጨዋታ ጥቆማ በመፈለግስ ደክመዋል ?
እንግዲያውስ አይጨነቁ እጅግ አስደናቂ ቻናል እንጦቅማችሁ አሁኑኑ ተቀላቀሉና አሸናፊ ይሁኑ
የየእለቱን የቅዱሳንን ዜና ገድል ስንክሳር ማንበብ ይፈልጋሉ እንግዲያውስ ከታች ያለውን linkun ነክቸው join ይበሉ
ተማሪ ነህ ?
የ125 ብር ካርድ ሊለቀቅ ነው 9 ደቂቃ ብቻ ነው የቀራው። ቶሎ ከስር JOIN ሚለውን ነክታቹ JOIN REQUEST ላኩ ?♀️?♂️
የሰዎች ሃሳብ መማሪያችን እንጅ መደገፊያችን አይሁን
አንዱ ሰውዬ ወንዝ ዳር ቁጭ ብሎ ያለቅሳል።ይህንን የተመለከተ አንድ?♂ ሰው ወደ እርሱ ይመጣና"ለምንድነው የምታለቅሰው?" በማለት ይጠይቀዋል።ሰውዬውም " አንድ ማንኪያ ሙሉ ስኳር እዚህ ወንዝ ውስጥ ጨምሬ የወንዙን ውሃ ብቀምሰው ምንም አይጣፍጥም" በማለት ይነግረዋል ፤ሌላኛው ሰውዬ በሳቅ ፍርስ ይላል፡፡ ሰውዬው ግራ ተጋብቶ እንዴ"ምን ሆነህ ነው የምትስቀው?"በማለት ይጠይቀዋል።ሌላኛው ሰውየም በሳቁ መሃል አንተ ጅል! መጀመሪያ አታማስለውም ነበር! በማለት ይመልስለታል?
አንዳንድ ሰዎችም እንደዚህ ናቸው ከአእናንተ የባሰ ስህተት ውስጥ እያሉ የተሻሉ እየመሰላቸው በትንሿ ስህተታችሁ ይስቁባችኋል፤ይሳለቁባችኋል፣ያጣጥሏችኋል።አንዳንድ ሰወች ሀሳብና አስተያየት ሲሰጡን ትክክለኝነቱ ሀሳባቸውን በነፃነት መግለፃቸው ብቻ የሚሆንበት ጊዜ አለ።የሚያውቁትን ስለነገሩን ብቻ ለእኛ ይጠቅመናል ወይም ከእኛ የተሻለ አውቀዋል ማለት አይደለምና የተነገረንን ሁሉ ለመተግበር እና ለመቀበል ከመቸኮል ባለፈ ቆም ብለን ማሰብና መመርመር አለብን።ምክንያቱም የአንዳንድ ሰዎች ምክር እና አስተያየት ከእኛ የባሰ ስህተት ውስጥ መሆናቸውን እንድናውቅ ያደርገናልና ከስህተታቸው እንድንማር ይረዳናል እንጅ ለችግራችን መፍትሄ ላይሆን ይችላል።
እግዚአብሔር ማስተዋልን ጥበብን እውቀትን ከፍቅር ጋር ይስጠን አሜን? እግዚአብሔር ብርሃኔና መድሃኒቴ ነው።
"የዳዊት ልጅ የአብርሃም ልጅ የኢየሱስ ክርስቶስ ትውልድ መጽሐፍ" ቅዱስ ማቴዎስ ጌታችንን "የዳዊት ልጅ የአብርሃም ልጅ "በማለት ለምን ጠራው ? !ከሁሉ አሰቀድሞ እነርሱን ለምን አነሳ ?
ስለ እነርሱ ብዙ ትንቢት ተነግሯል
ለአብርሃም "የምድር አሕዛብ ሁሉም በዘርህ ይባረካሉ " ለዳዊትም "ከሆድህ ፍሬ በዙፍንህ ላይ አስቀምጣለሁ " ተብሎ ተነግሮላቸዋል ። ዘፍ 22፥18 መዝ 141-11 ሌሎቹ ትንቢት ቢነገርም ተደጋግሞ የተነገረላቸው ለአብርሃምና ዳዊት በመሆናቸው ከእነርሱ ይጀምራል ። (ኪዳነ ጽድቅ ገጽ-16)
ተርእዮ (የመታየት ጉጉት)
አሁን ለደረስንበት "ኹለንተናዊ ውድቀት" ተጠያቂው "ዘመኑ" ወይም ማኅበራዊ ሚዲያው አይደለም። ተጠያቂው "ዘመኑ" ሳይሆን እኛው ነን - በዘመኑ ውስጥ የምንሠራ ነንና። ሚዲያውም ቢሆን የኛን የልብ ጥመትና ክፋት ገለጠብን እንጂ በራሱ መጥፎ አይደለም። ከጥቂት ዓመታት በፊትና በአሁኑ ዘመን መካከል በተለይ በክርስቲያናዊ አኗኗር ላይ ብዙና ሰፊ ለውጦች የታዩ ይመስለኛል። ከሁሉ ከሁሉ ግን ዕለት ዕለት የሚገርመኝ የተርእዮ ፍላጎታችን መጋሸብ ነው። አሁን ላይ ግሽበት ለኢኮኖሚው መስክ ብቻ የሚነገር አይደለም። ከእርሱ ሌላ ኢጎ ("የእኔነትና - የለኔነት") ከፍተኛ ሁኔታ ጋሽቧል። የመታየት አምሮትም ከዚህ የሚለይ አይደለም። የአሁን ሰው ዛሬን መኖር ረስቷል። ዛሬን (አሁንን) ከመኖር ይልቅ ለትዝታ የሚሆነው ላይ ይታትራል። ቤተ ክርስቲያን (ንግሥ፣ ማኅሌት፣ ቅዳሴ ... ) በእግሩ መጥቶ፤ በልቡ ግን ከሥርዓተ አምልኮቱ ውጪ ይሆናል። ነገ ራሱና ሌሎች የሚያዩትን በፎቶና በቪዲዮ ለማስቀረት "ይተጋል"። በአምልኮቱ ጊዜ በልዩ ሁኔታ የተገኘውን ክርስቶስን (Divine Presence) ሳያገኝ፤ ሌሎች ለሚያዩት፣ በቲክቶክ ለሚለቀው ቪዲዮ ይደክማል።
በቤተ ክርስቲያን ሥርዓተ አምልኮት ላይ ማን እንዴትና ለምን እንደሚገኝ የምናውቀው ይመስለናል እንጂ ፈጽሞ አላወቅነውም። ክርስቶስ እኛን ለማግኘት ይመጣል፤ እኛ በኢጎአችን ተመርተን የሠራነውን ለሌሎች Broadcast ለማድረግ እንፋጠናለን። ስለዚህም ጸጋ እግዚአብሔር ከብዙዎቻችን ጋር ሳይዋሐድ የሚመለስ ይመስለኛል። Divine Presence ሊዋሐደው የሚሻ እውነተኛ (ልባዊ) human presence ይፈልጋልና። እኛ ሰማያዊውን ለሰው መታያ አደረግነው። መዝሙሩ ብዙዎች የሚኩነሰነሱበት መታያ ሆነ፤ ትምህርቱም ብዙዎች የጸሎትና የቅዳሴ መንፈስ የራቀው፡ እርስ በእርስ መሸነጋገያ ሆነ። ምስጋና እና ክብርን መጠማት በዛ። "የራስ ሥራን" በሰው ክብር መሸጫ መለወጫ ገበያዎች ብዙ ሆኑ። "ሌላው ሰው" ለክርስትናችን አስፈላጊያችን መሆኑ ተረሳ። ዓለም እርሱን በእጁ ስለያዘው ገንዘብ ምክንያት እንደምትፈልገው፤ እንዲሁ እኛም እርሱን ለመውደድ በእርሱም ከእግዚአብሔር ጋር መገናኘትን ሳይሆን ስለ ገንዘቡና ስለሚሰጠን attention ብቻ እንፈልገዋለን። ታዲያ ክርስትናውን መቼ መኖር እንጀምር ይሆን? መቼ ከራሳችን ጋር የእውነት እንተያይ? መቼ እውነተኛ ንስሐን እናግኝ? መቼ እግዚአብሔርን እና ሌላውን ሰው የእውነት እንወድ ይሆን?
"ኦ እግዚእየ ኢየሱስ ክርስቶስ ወልደ እግዚአብሔር ሕያው ወልደ ማርያም ሥግው መሐረኒ!"
( ዲያቆን ሚክያስ አስረስ )
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።
@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna
#ኢትዮጵያ
Last updated 2 months, 3 weeks ago
Last updated 2 months, 2 weeks ago
ይህ ስለ Manchester United መረጃዎችን የሚያገኙበት የ Telegram ቻናል ነው 🇪🇹
--------------------------------------------------------------
☞︎| ስለ ማንቸስተር ዩናይትድ ትኩስ መረጃዎች
☞| ቀጥታ ስርጭቶች ከየስታድየሞቹ
☞| የዝውውር ዜናዎች
☞| ስለ ማንችስተር ዩናይትድ ታሪኮች
📩 ለማስታወቂያ ስራ DM :- @Marcoabdu
Last updated 1 month, 1 week ago