Esubalew Abera N.

Description
We recommend to visit

ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ

Last updated 2 months, 3 weeks ago

Last updated 2 months, 2 weeks ago

ይህ ስለ Manchester United መረጃዎችን የሚያገኙበት የ Telegram ቻናል ነው 🇪🇹
--------------------------------------------------------------
☞︎| ስለ ማንቸስተር ዩናይትድ ትኩስ መረጃዎች
☞| ቀጥታ ስርጭቶች ከየስታድየሞቹ
☞| የዝውውር ዜናዎች
☞| ስለ ማንችስተር ዩናይትድ ታሪኮች

📩 ለማስታወቂያ ስራ DM :- @Marcoabdu

Last updated 1 month, 1 week ago

1 month, 2 weeks ago
*የግርጌ ማስታወሻ — በፊትም፣ አሁንም በኢትዮጵያ …

*የግርጌ ማስታወሻ — በፊትም፣ አሁንም በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ኅብረት ውስጥ ያለሁ አማኝ ነኝ። የትም አልሄድሁም፣ ከየትምም አልተመለስሁም። ምናልባት ግን በቤት ውስጥ እንደ ጠፋ ድሪም ጠፍቼ (ሉቃ. 15፥8) ወይም ለብ ብዬ (ራእ. 3፥16) ነበር።

የዛሬው ፖስት እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ ከዛሬዋ ዕለት አንሥቶ በቃልም፣ በምግባርም ትጉህ (devoted) ክርስቲያን ለመሆን የማደርገውን ክርስቲያናዊ ልምምድ በይፋ አሐዱ ብዬ እንደ ጀመርሁ የሚገልጽ ነው። ያ ጉዞ ደግሞ የሕይወት ዘመን ጉዞ ነው። ክርስቲያንነት በአንዴ ሆነን የምንጨርሰው ነገር አይደለም። በዚህም የተሳሳተ አረዳድ ይመስለኛል፣ ብዙዎቻችን ቀድሞም ክርስቲያን ብንሆንም የልማድ (passive) ክርስቲያን ብቻ ሆነን የቀረነው — ለብ ያለ።

ክርስትና ግን የዕለት ተዕለት ልምምድ ነው። ያንን ልምምድ ደግሞ በግሌ ዛሬ ጀምሬያለሁ ለማለት ነው። ያጋራሁትም እንደ እኔ ባለ ስሜት ውስጥ የሚመላለስ ሰው ካለ፣ ዳግም አዲስ መሥመር አሥምሮ፣ የመንፈሳዊ ሕይወቱን ጉዞ ከእግዚአብሔር ጋር እንዲጀምር እግረ መንገድ ለማነሣሣት ነው። «I Started a Life-long Jorney to Become an Orthodox Christian » ያልኩትም በዚህ ዐውድ ነው።

«ድንግል ማርያም ክርስቲያን እንድሆን አድርጊኝ።
ድንግል ሆይ በክርስቲያን ሥርዓት እንድውል፣
በክርስቲያን ሥርዓት እንዳድር አድርጊኝ።»

— አባ ፡ ጊዮርጊስ ፡ ዘጋሥጫ።*

1 month, 2 weeks ago
Esubalew Abera N.
1 month, 2 weeks ago
4 months, 1 week ago

? የሥነ — ግጥም ዘመነኛ መልኮች | Overview

4 months, 2 weeks ago

እነሆ

ቃላት ፩፫ | 13 | Words | ኪናዊ መጽሔት

https://t.me/Words2014
.
.
ለአስተያየታችሁ :‑
[email protected]

6 months ago

በቸር ያቆየን፣ በቸር ያገናኘን።

6 months, 2 weeks ago
Esubalew Abera N.
6 months, 3 weeks ago

*1.
ዓለም ኢ-ፍትሐዊ ናት። የሰው ልጆች ሥርዓት የተዛባና ለተጠቂ ውግንና የማይሰጥ ነው። በቅርብ ጊዜ እንኳ በእኛ ሀገር ለቁጥር የሚታክቱ ጥቃቶችና በደሎች ደርሰዋል። እንደ እድል አልያም አጋጣሚ ሆኖ ካሜራ ቀርጾ ያስቀመጣቸው፣ ተበዳዮች በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ አደባባይ ወጥተው ሊጮኹ የቻሉባቸው ጉዳዮች ጎልተው ተሰምተዋል። በየቤቱ ተሸፍነውና ተድበስብሰው የቀሩትን ለአፍታ ማሰብ ደግሞ የማይሽር ሕመም ነው። ካሜራ ያላያቸው፣ ፍትሕ ያልተጠየቀላቸው፣ ያልጮኽንላቸው በደሎች ቁጥርና ስፍር የላቸውም። ማኅበራዊ ሚዲያው በዚህ ረገድ በረከት ቢሆንም ፍትሕን የምንጠይቅበት ብቸኛ አማራጭ ወደ መሆን መምጣቱን ማሰብ እጅግ በጣም ያሳዝናል።

  1. አሁን አሁን ሳስበው ማኅበራዊ ሚዲያ በአመዛኙ ከሰው ተፈጥሯዊ ሥሪት የራቀ ነገር እንደሆነ ይሰማኛል። እንደ ሰው በውስጣችን የነበረውን ክፋት መግለጥ ብቻ ሳይሆን በሆነ መንገድ እንዳባባሰው አስባለሁ። ራሳቸውን በሰዋዊ ባሕርይ ማስገዛት ያልቻሉ ሰዎች እዚያም እዚህም እያሉ ሰዎችን በአስተያየቶቻቸው ሲያቆስሉ፣ መርዛቸውን ሲረጩ ማየት ይደብታል። ማኅበራዊ ሚዲያ ላይ ሀሳብን በነጻነት በመግለጽ ስም፣ በተደበቀም ሆነ በተገለጠ ማንነት የሚንሸራሸረው ድንቁርና አስደንጋጭነቱ ብርክ ያስይዛል። ዙሪያችን የምናስበውን ያህል ጤናማ ከባቢ እንዳልሆነ ያረዳናል። አንዳንድ ነገሮችን ባለማየት ውስጥ የነበረን ተስፋ በማወቅና በማየት ተነጥቋል። ምን ያህል ክፉዎች እንደሆንን አሳብቀናል። እናም ሰው ጤነኛ ሆኖ መኖር ካለበት ከቻለ ሙሉ በሙሉ፣ በተለያየ ምክንያት ሳይችል ከቀረም በየሆነ ርቀቱ ከማኅበራዊ ሚዲያው ገለል ማለት ይኖርበታል ብዬ አስባለሁ። ምክንያቱም የቱም ሰው ይህን ያህል ዝብርቅርቅና አሰቃቂ የሆነ መረጃ ያለማቋረጥ ዓይኑ እያየ፣ ጆሮው እየሰማ ጤነኛ ሆኖ ሊዘልቅ አይችልም።*
We recommend to visit

ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ

Last updated 2 months, 3 weeks ago

Last updated 2 months, 2 weeks ago

ይህ ስለ Manchester United መረጃዎችን የሚያገኙበት የ Telegram ቻናል ነው 🇪🇹
--------------------------------------------------------------
☞︎| ስለ ማንቸስተር ዩናይትድ ትኩስ መረጃዎች
☞| ቀጥታ ስርጭቶች ከየስታድየሞቹ
☞| የዝውውር ዜናዎች
☞| ስለ ማንችስተር ዩናይትድ ታሪኮች

📩 ለማስታወቂያ ስራ DM :- @Marcoabdu

Last updated 1 month, 1 week ago