ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።
@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna
#ኢትዮጵያ
Last updated 2 months, 3 weeks ago
Last updated 2 months, 2 weeks ago
ይህ ስለ Manchester United መረጃዎችን የሚያገኙበት የ Telegram ቻናል ነው 🇪🇹
--------------------------------------------------------------
☞︎| ስለ ማንቸስተር ዩናይትድ ትኩስ መረጃዎች
☞| ቀጥታ ስርጭቶች ከየስታድየሞቹ
☞| የዝውውር ዜናዎች
☞| ስለ ማንችስተር ዩናይትድ ታሪኮች
📩 ለማስታወቂያ ስራ DM :- @Marcoabdu
Last updated 1 month, 2 weeks ago
የኒሂሊዝም (Nihilism) ፍልስፍና መሰረቱ ጥቅሙስ ምንድን ነው?.
(አለማየሁ ገላጋይ ኢትዮጵያዊው ኒሂሊስት)
ኒሂሊዝም የሚባለው ፍልስፍና በአውሮፓ በ19ኛው ክፍለ ዘመን የተነሳ ርዕዮት ነው። ኒሂሊዝም እንደሚገለፅበት አውድ እና ዲሲፕሊን የተለያዩ መልኮች ቢኖሩትም ማጠንጠኛው ሃይማኖት፣ ዕምነት፣ ባህል፣ እውቀት፣ ሕግ፣ ሥነ ምግባር ወዘተን መካድ ነው። ኒሂሊዝም መሠረቱ ጥርጥር (skepticism) ነው። ጥርጥር ዓላማው ውሸትን ለይቶ እውነት ጋር መድረስ ነው። ጥርጥር ግን በወለደችው ኒሂሊዝም የተሰኘ ልጅ ዓላማዋንም፣ ትርጉሟንም አጥታ እየሞተች ነው። ጥርጣሬ ጫፍ ሲይዝ እና ጨለምተኛነት የሚባል ቅመም ተጨምሮበት ሲበስል ኒሂሊዝምን ይወልዳል። ኒሂሊዝም ሁሉንም ነገር ያለምህረት መካድ ነውና። በኔ በኩል ጥቅም አለው ብዬ አላስብም። የአብዘርድ አቀንቃኙ አልበርት ካሙዩ እንኩዋን፣ እውነት ነው ህይወት ትርጉም የላትም፣ ግን ትርጉም የላትም ብለን ልንተዋት አይገባም፣ ትርጉም ልንፈጥርላት ግድ ነው ይለናል። አይሁዲው ቪክተር ፍራንክል ከአልበርት ካምዩ በተቃራኒ በሕይወት ለመኖር የሚያነሳሳን ነገር ትርጉም ፍለጋችን መሆኑን ቢያስረዳም።
"""""
እሴቶች: —
የሰው ልጅ በማህበራዊ ኑሮ ዉስጥ ህልውናውን የሚያስጠብቅባቸው፣
ባህሉን የሚያስከብርባቸውና ለትውልድ የሚያስተላልፍባቸው፣
ዕውቀቱን የሚያሰፍርባቸው፣
በየትኛውም ማህበረሰብ ውስጥ ባህል አለ። ማህበረሰብ ለባሕል ያለው አመለካከት የተለያዬ ቢሆንም ለዕሴቶቹ እውቅናን መስጠት ብቻ ሳይሆን አስፈላጊነታቸውንም ያምናል፡፡ ነገር ግን ኒሂሊዝም እነዚህን ሰዋዊ እሴቶች ይክዳል፤ አላስፈላጊነታቸውንም ይሰብካል፡፡ መሰረት የሌላቸውና አንዳችም ጥቅም የማይሰጡ መሆናቸውን በመግለጽ በሰው ልጅ ህላዌ ውስጥ ያላቸውን ህልውና ይክዳል። ኒሂሊዝም ሕይወት ትርጉም የለሽ እንደሆነ በማመን፣ ሁሉንም ሃይማኖታዊ እና ሥነ ምግባራዊ መርሆች አለመቀበል ነው፣ ልቅ የሆነ ነፃነት ይኑርም፣ ሁሉንም ከዜሮ እንጀምረው ይላል። «ነባሩ እሴት፣ ወግ፣ ባህል፣ እምነት በአጠቃላይ ምድራዊ ህግጋትና ማህበራዊ ትብታቦች የሠውን ልጅ ነፃነት ተጋፍተዋል፤ ስለዚህ የሠው ልጂ ከእነዚህ ትብታቦችና ሠው ሠራሽ ሠንሠለቶች እስር ነፃ መውጣት አለበት» ይላል።
የሰውን ተፈጥሯዊ ምንነት ካለማወቅ የሚመነጭ የጥፋት መንገድም ይመስላል። ሰው በcognitive evolution ያገኘውና ከሌሎች እንሰሳት የለየው ነገር ቢኖር የሌለን ነገር በ association በአዕምሮው መፍጠር መቻሉ ነው። ነገር ግን ኒሂሊስቶች በዚህ መንገድ የተፈጠረው ይጥፋና በሌላ ተጨባጭ እውነት ይተካ ይላሉ። በመጀመሪያ ይህን የማይጨበጥ እውነት እንዴት ለማጥፋት ይቻለናል? ከተቻለስ፣ ሰው እራሱ መልሱ እንደማይፈጥረው ምን እርግጠኛ አደረገን? ሃይማኖት የራሱ ችግር እንዳለበት ብስማማም፣ እንደምንለው ስላሰብን የሚጠፋ አይደለም። የጠፋ ቢመስለንም ቅርጹን ቀይሮ ይቀጥላል። የተሻለው፣ ችግርንና መንስኤዎችን መለየት፣ መፍትሔን መዘየድ ነው። ችግሩ፣ ከችግሮች ከአንዱ ላይ ፊጥ ስላልን ችግር የፈታን መስሎናል።
"ጠርጥር! ፣ ጠርጥር! አንዳንዴ ከገንፎም አይጠፋም ስንጥር" ይላል ያገሬ ሰው! በ17ኛው ክፍለ ዘመን በፈረንሳይ ገኖ የወጣ አፍቃሬ−አመክንዮ ፈላስፋ ነው፤ ዴካርት። በዓለም የፍልስፍና ታሪክ ውስጥም የዘመናዊ ፍልስፍና አባት ተደርጎ ይቆጠራል። ገና በጠዋቱ እናቱ እንደወለደችው የሞተችበት ዴካርት፣ የህይወት ውጣ-ውረዱን ዘመዶቹ ቤት በማደግ መወጣት የቻለ ሲሆን አልፎ ተርፎም እውቅ የሒሳብ ልሂቅ፤ ፈላስፋ…
"ጠርጥር! ፣ ጠርጥር! አንዳንዴ ከገንፎም አይጠፋም ስንጥር" ይላል ያገሬ ሰው!
በ17ኛው ክፍለ ዘመን በፈረንሳይ ገኖ የወጣ አፍቃሬ−አመክንዮ ፈላስፋ ነው፤ ዴካርት። በዓለም የፍልስፍና ታሪክ ውስጥም የዘመናዊ ፍልስፍና አባት ተደርጎ ይቆጠራል። ገና በጠዋቱ እናቱ እንደወለደችው የሞተችበት ዴካርት፣ የህይወት ውጣ-ውረዱን ዘመዶቹ ቤት በማደግ መወጣት የቻለ ሲሆን አልፎ ተርፎም እውቅ የሒሳብ ልሂቅ፤ ፈላስፋ እና ሳይንቲስት እንዲሁም የዘመናዊ ፍልስፍና አባት ሊሆንም ችሏል።
ዴካርት እድሜውን የፈጀው የእውቀት መጀመሪያ ምን እንደሆነ ሲያስስ ነው፡፡ ይህ እሱ የፈለገው ቀዳማይ-እውቀት እያንዳንዱ ሰው የግሉን ህይወት ሊመሠርት የሚችልበት የማይናወጥ እውቀት ነው፡፡
ለመጠራጠር ማሰብ ያስፈልጋል፤ ከተጠራጠርን ማሰብ እንችላለን፤ ካሰብን ደግሞ ያ ያሰብነውን እንሆናለን፡፡ ጥርጣሬ መጀመሪያ ላይ ነገሮችን በሙሉ ወደ ጥያቄ ይለውጣል ኋላ ላይ ደግሞ ይገለብጥና የእርግጠኝነት ምንጭ ይሆናል፡፡
በዚህች ዓለም ላይ የማንጠረጥረው ነገር ምን አለ? ለሚለው ጥያቄ ቁጭ ብሎ ሲቆዝም ዴካርት ያገኘው መልስ ቢኖር “I think, therefore I am” የሚለውን ዓረፍተ-ነገር ነው፡፡
ሁሉን እጠራጠራለሁ፤ እኔ ራሴ በሕይወት እየኖርኩ ስለመሆኔ ግን ልጠራጠር አልችልም፤ ምክንያቱም አስባለሁ፤ ለመጠራጠር ራሱ መጀመሪያ መኖር አለብኝ፤ አሁን እያሰብኩ ነው፤ ስለዚህም እየኖርኩ ነው፡፡ (I think, therefore I am) የሚለው የዴካርት አባባል፣ ለፈላስፎች ጥልቅ የሆነ ትርጉም አለው፡፡ የጥንቱና የመካከለኛው ዘመን ሰው፣ እውቀትንና እውነትን ለማግኘት ከራሱ ውጭ ባለው ሰፊ ዓለም ውስጥ ሲባዝን ነበር፡፡ በዴካርት ፍልስፍና ውስጥ ግን የውጭውን ዓለም መዳሰሱ ቀርቶ የምርምሩ ጅማሮ ከራስ ሕልውና ሆነ፡፡
የዚህን ዓለም እውነት ለማግኘት መጀመር ያለብን “ከራሳችን” ነው የሚለው የዴካርት ፍልስፍና፤ የዕውቀትንና የእውነትን መለኪያ መስፈርትን ለማግኘት ባደረገው ጥረት ውስጥ “ተፈጥሮን” ከእውነት ምንጭነት አስወገደው! ... ለነገሩ እሱዬ መጀመሪያ መጠራጠር የጀመረው እሱ-ራሱ ነበር፡፡
እፊታችን እያየን ከምናወራቸው ተጨባጭ ነገሮች ጀምሮ የምናምናቸው ነገሮች እርግጠኞች ልንሆን አንችልም የሚለው ዴካርት ሁሉንም ነገር፤ የሚያየውን፣ የሚዳስሰውን፣ የሚያሸተውን፣ የሚቀምሰውን በአጠቃላይ በስሜት ህዋሳቱ አማካኝነት የሚያገኘውን መረጃ በሙሉ ከመቀበል ይልቅ በጥያቄና በጥርጣሬ ያዋክባቸዋል።
እርግጠኛ የሆነ እውቀትን ለማግኘት ዴካርት የተጠቀመበት ዘዴ ደግሞ፤ ከዚህ በፊት እርግጠኛ የሆንባቸውን ነገሮች ሁሉ በመጠራጠር እና ባለመቀበል ነው። እናውቀዋለን የምንለውን ነገር ሁሉ በጥያቄ ማብጠርጠር ማለት ነው።”
ዘላቂና የማይናወጥ እውቀትን መመስረት ካለብኝ፣ እስከዛሬ በሕይወት ዘመኔ የሰበሰብኩትን እውቀት ተብዬ ሁሉ ድምጥማጡን ማጥፋት እንዳለብኝ ተገንዝቤአለሁ” ይለናል፤ “ቀዳማዊ ተመስጦ” በተባለው ድርሳኑ በአካባቢያችን ያሉ ነገሮችን ሁሉ እየበረቃቀስን እና እያብጠረጠርን መፈተሽ እንዳለብን ያሳስባል፤ ዴካርት።
ይህንንም ተከትሎ ሦስት አፈንጋጭ ሙግቶችን
ያቀርባል፤ በዘልማድ የተቀበላቸውን ነገሮች ሁሉ ለማስወገድ እንዲረዱትና እርግጠኛ የሆነ እውቀት ለመመስረት እንዲችል። እያንዳንዱን እምነቱን አንድ በአንድ በመጨፍለቅ ሳይሆን መሰረታዊ የእምነቱን መርሆዎችን ማንገራገጭ እንደስልት ይጠቀማል፤ ዴካርት።
በመሰረታዊነት የተጠቀመባቸውን ሦስቱን ሙግቶች እንደሚከተለው ማየት ይቻላል።
ሀ) ማንኛውንም ያልተመረመረ ሀሳብ እና በስምምነት የተቀበልነውን ሁሉ በተደራጀና መመሪያዎችን በተከተለ መልኩ በጥርጣሬ መፈተሽ። ወይም ባጭሩ አፈንጋጭነት ልንለው እንችላለን። ይህ በየዋህነት የተቀበልናቸውን አስተሳሰቦች ለማጥቃት የተጠቀመበት ሙግት ነው። “ከጊዜ ወደ ጊዜ የስሜት ህዋሶቼ እያጭበረበሩኝ እንደ ሆነ ደርሸበታለሁ።” የሚለው ዴካርት፤ “ለአንዲት ጊዜ እንኳን ያታለለችኝን የስሜት ህዋሴን አለማመኔ ሁነኛ እርምጃ ነው” ይላል።
ለ) ያልጠራ፣ እራሱን ያልቻለ እና ግጭቶች/መፋለሶች ያሉበትን ሐሳብ አለመቀበል። ይሄኛው የዴካርት ሙግት "የህልም ሙግት" (The Dream Argument) እየተባለ ይጠራል።
ሐ) እራስን በማወቅ፤ ከዓለት በጠነከረ መሰረት ላይ ሐሳባችንን መስርተን፤ በማንኛውም ጥርጣሬ የማይነዋወጥ ከራስ ከውስጥ የመነጨ “እያሰብኩ ስለሆነ እኔ ኅልው ነኝ” የሚል ግለሰባዊነት ላይ መድረስ። (“Cogito, ergo sum”) “የስሜት ህዋሳት አንዳንዴ ያጭበረብሩናል።
ይቀጥላል ✍️
https://t.me/lucky_gems_official_bot/app?startapp=27VfMTud77nY6YSbKMaQgHX6v6ZDFuCKhLk2N84y1UHyXCX
? I've won 0.6 USDT! Click the link to help me earn more! You can also play & win money! ?
? Join now and let's earn more together! ?
መልካም ዕድል
I am inviting you to download telebirr SuperApp, register and make a transaction to get reward. https://superapp.ethiomobilemoney.et:38443/customer/mgm/index0902.html#/?notoolbar=true&CampaignId=MGM1635518748044544&inviterId=1181454320153601&language=en&time=Sept-03-2024-Dec-02-2024
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።
@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna
#ኢትዮጵያ
Last updated 2 months, 3 weeks ago
Last updated 2 months, 2 weeks ago
ይህ ስለ Manchester United መረጃዎችን የሚያገኙበት የ Telegram ቻናል ነው 🇪🇹
--------------------------------------------------------------
☞︎| ስለ ማንቸስተር ዩናይትድ ትኩስ መረጃዎች
☞| ቀጥታ ስርጭቶች ከየስታድየሞቹ
☞| የዝውውር ዜናዎች
☞| ስለ ማንችስተር ዩናይትድ ታሪኮች
📩 ለማስታወቂያ ስራ DM :- @Marcoabdu
Last updated 1 month, 2 weeks ago