AHADU RADIO FM 94.3

Description
አሐዱ ራድዮ 94.3
Your source for top local and international news and analysis.
"Voice of Ethiopian"
የአሐዱ የቴሌግራም ቻናል ቤተሰብ በመሆን ወቅታዊና እውነተኛ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ
Advertising
Tags
We recommend to visit

ለማንኛውም አስተያየት እና ጥቆማ ? @Esat_tv_comment_bot

??ኢሳት የኢትዮጵያ አይን እና ጆሮ??

Last updated 1 month, 1 week ago

Last updated 2 months, 1 week ago

እንኳን ደህና መጡ‼

✔ማስታወቂያ ለማሰራት እና ጥቆማ ለመስጠት በዚህ ይጠቀሙ ☞https://t.me/WasuMohammed

✔ ቻናሉን ለመቀላቀል Join ☞http://t.me/Wasulife

ከልብ አመሰግናለሁ♥?

Last updated 2 months ago

1 month, 2 weeks ago
ነሃሴ 23 - 2016 ዓ.ም

ነሃሴ 23 - 2016 ዓ.ም

የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የቀድሞ ፕሬዝዳት ፕሮፌሰር አንድርያስ እሸቴ ባደረባቸው ህመም በህክምና ሲረዱ ቆይተው ዛሬ ነሐኔ 23 ቀን 2016 ዓ.ም ከዚህ ዓለም ድካም አርፈዋል።

የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በቀድሞ ፕሬዝዳንቱ ህልፈተ ህይወት የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን እየገለፀ ለቤተሰቦቻቸው፣ ለባልደረቦቻቸው እንዲሁም ለወዳጅ ዘመዶቻጆቻቸው መጽናናትን ይመኛል።

1 month, 2 weeks ago
መልካም ቀን !

መልካም ቀን !
አሐዱ ሬድዮ 94.3 የኢትዮጵያውያን ድምፅ !

1 month, 3 weeks ago

ወጋገን ባንክ ዓለም አቀፍ የቅድመ ክፍያ ቪዛ ካርድ አገልግሎት ይፋ አደረገ !

መቐለ፣ ነሐሴ 15 ቀን 2016 ዓ.ም፡- ወጋገን ባንክ ከቪዛ ኢንኮርፖሬትድ ጋር በመተባበር ወደ ውጪ ሀገር ጉዞ ለሚያደርጉ የባንኩ ደንበኞች፣ የኤምባሲዎች እና የዓለም አቀፍ ድርጅት ሰራተኞች ጥሬ ገንዘብ መያዝ ሳያስፈልጋቸው በየትኛውም የዓለም ክፍል ክፍያ መፈፀም የሚያስችላቸውን ዓለም አቀፍ የቅድመ ክፍያ ቪዛ ካርድ አገልግሎት መስጠት መጀመሩን በመቐለ ከተማ በፕላኔት ሆቴል ባካሄደው ይፋዊ የአገልግሎት ማብሰሪያ ስነስርዓት ላይ አስታወቀ፡፡

4 months, 1 week ago
ሰኔ 1 - 2016 ዓ.ም

ሰኔ 1 - 2016 ዓ.ም
አሜሪካ ተጨማሪ ወታደራዊ ድጋፏን ለዩክሬን መስጠቷን አስታውቃለች፡፡

ፈረንሳይ ውስጥ ተገናኝተው ፊት ለፊት የመከሩት የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን እና የዩክሬኑ አቻቸው ቮሎድሚር ዜሌንስኪ በዩክሬን ዝርዝር ጉዳይ መምከራቸው ነው የተገለጸው፡፡

የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን ዩክሬን ከሩሲያ ጋር የምታደርገውን ጦርነት በአምባገነኖች ላይ የሚደረግ ጦርነት ነው ሲሉ በተደጋጋሚ መፈረጃቸው ይታወሳል፡፡

ባይደን በዚያ ከዜለንስኪ ጋር በነበራቸው ውይይት ሀገራቸው አሜሪካ ለዩክሬን ሁለት መቶ ሃያ አምስት ሚሊየን ዶላር ወታደራዊ ድጋፍ ለመስጠት መዘጋጀቷን ገልጸውላቸዋል፡፡
ዘገባው፡-የኢንዲፔንደንት ነው፡፡

አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
አሐዱ ራድዮ 94.3 እና ቴሌቪዥን #አሐዱ_2

4 months, 1 week ago
ሰኔ 1 - 2016 ዓ.ም

ሰኔ 1 - 2016 ዓ.ም
በሱዳን የሀገር ውስጥ ተፈናቃዮቹ ብቻ ከአስር ሚሊየን በላይ መድረሳቸው ተገልጿል፡፡

በሱዳን ከአውሮፓውያኑ 2023 ሚያዚያ ወር አጋማሽ ከጀመረው ጦርነት ወዲህ ከአስራ ሁለት ሚሊየን በላይ ሰዎች መፈናቀላቸው ሲገለጽ ሁለት ሚሊየን ሱዳናውያን ከሀገራቸው ርቀውና አቋርጠው ወደ ግብጽና ቻድ መግባታቸውም ታውቋል፡፡

በሀገር ውስጥ ደግሞ ከአስር ሚሊየን በላይ ተፈናቃዮች መኖራቸው ነው የተገለጸው፡፡ ትናንት ሱዳንን በተመለከተ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ያወጣው መግለጫ እንደሚያሳየው ሱዳን በዓለም ላይ ትልቋ የመፈናቀል አደጋ የተመዘገበባት ሀገር ሆናለች ሲል ገልጿል፡፡
ዘገባው የቴሌግራፍ ኦንላይን ነው፡፡

አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
አሐዱ ራድዮ 94.3 እና ቴሌቪዥን #አሐዱ_2

4 months, 1 week ago
ሰኔ 1 - 2016 ዓ.ም

ሰኔ 1 - 2016 ዓ.ም
የዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ የጦር ፍርድ ቤት በመፈንቅለ መንግስት ሙከራ በተጠረጠሩ አካላት ላይ የፍርድ ውሳኔ ሊሰጥ መሆኑ ተገልጿል፡፡

በዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ኮንጎ በቅርቡ ተሞክሮ ከሽፏል በተባለው የመፈንቅለ መንግስት ሴራ ተሳትፈዋል የተባሉ ሶስት አሜሪካውያንን ጨምሮ በሃምሳ ሶስት ሰዎች ላይ የፍርድ ውሳኔ ለመስጠት እንደሚቀመጥ የሀገሪቱ ጦር ሀይል ፍርድ ቤት አስታውቋል፡፡

የዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ኮንጎ ፕሬዝዳንት በካቢኔያቸው የሹም ሽር ማድረጋቸውና የማስተካከያ እርምጃ መውሰዳቸው ይታወቃል ሲል የኒውስ 24 ዘገባ ያስረዳል፡፡

አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
አሐዱ ራድዮ 94.3 እና ቴሌቪዥን #አሐዱ_2

4 months, 2 weeks ago
ግንቦት 26 - 2016 ዓ.ም

ግንቦት 26 - 2016 ዓ.ም
የቻይናው ሻንጋይ ጂአዎ ቶንግ ዩኒቨርስቲ አይነ ስውራንን መንገድ የሚመራ አዲስ የሮቦት ቴክኖሎጂ አስተዋውቋል።

ባለ 6 እግሩ ሮቦት መንገድ ጠቋሚ ሴንሰር፣ የሌዘር ራዳር ቴክኖሎጂ እና የናቭጌሽን ሲስተም የተገጠመለት ሲሆን ከሰው በሚሰጠው የድምጽ ትዕዛዝ ካሰቡት ቦታ ያለምንም ችግር ማድረስ የሚችል ነው ተብሏል። ከቴክኖሎጂው ፈጣሪዎች መካከል አንዱ የሆኑት ፕሮፌሰር ጃው ፌንግ ሮቦቱ በተለይ ለጉዞ አይንን ተክቶ ማገልገል የሚችል ነው ብለውታል።

የትራፊክ መብራቶችን እና ሌሎች የደህንነት ማስጠንቀቂያዎችን ጠንቅቆ የሚያውቀው ሮቦት በተጨማሪም አስቸጋሪ የመንገድ ላይ ሁኔታዎችን በመለየት አይነስውራን በመንገድ ላይ ከሚያጋጥማቸው አደጋ ይከላከላል ተብሎለታል።

ሮቦቱ በሚኖርበት ከተማ ላይ ያሉ ቤተመጽሀፍቶች፣ የመንግስት ተቋማት፣ ቤተእምነቶችን እና ሌሎችንም በኢንተርኔት አማካኝነት መዝግቦ የሚያስቀምጥ ሲሆን ከሰዎች በሚሰጠው ትዕዛዝ መሰረት መጓዝ የሚችል ነው። ከዚህ ባለፈም በተመጠነ የጉዞ ፍጥነት በሰከንድ 3 ሜትሮችን መጓዝ የሚችል ሲሆን እንደ አስፈላጊነቱ ባለቤቱ በሚፈልገው የጉዞ መጠን እንዲፈጥን አልያም እንዲዘገይ የሚነገረውን ትዕዛዝ ይቀበላል።

በተጨማሪም አይነ ሰውራን የጤና ችግር እና ድንገተኛ አደጋ ሲያጋጥማቸው በተገጠመለት አላርም የእርዳታ ጥሪን ማድረግ ይችላል።

ሮቦቱ በአሁኑ ወቅት የመስክ ሙከራ ላይ ሲሆን ዩኒቨርስቲው ለገበያ ገና ባያቀርበውም 20 ትእዛዞችን መቀበሉን ገልጿል።

አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድረገጽ፡-https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
አሐዱ ራድዮ 94.3 እና ቴሌቪዥን #አሐዱ_

4 months, 2 weeks ago
ግንቦት 26 - 2016 ዓ.ም

ግንቦት 26 - 2016 ዓ.ም
በሀገሪቱ ያጋጠመውን ከፍተኛ ሙቀት ተከትሎ 33 ገደማ ሰዎች በሰሜናዊዋ ኡታህ ፓርዴሽ ክልል ውስጥ ህይወታቸው ያለፈ ሲሆን፤ በኦዲሻ ደግሞ 20 ገደማ ሰዎች በሙቀት ሳቢያ ህይወታቸው አልፏል።

በህንድ በየዓመቱ በከፍተኛ ሙቀተ ከሚጠቁ ሀገራት መካከል ስትሆን፤ የዘንድሮው ግን ከዚህ ቀደም ከነበሩት ክብረወሰን የሰበረ ነው ተብሏል።

የህንድ ጤና ሚኒስቴር ባወጣው መግለጫ፤ በሀገሪቱ የተለያዩ አካባቢዎች ባጋጠመተው ከፍተኛ ሙቀት ሳቢያ ከ56 በላይ ሰዎች በስትሮክ ተጠቅተው ህይወታቸው አልፏል።

ጤና ሚኒስቴር ይህንን ቢልም በሙቀት ሳቢያ በስትሮክ የተጠቁ እና ህይወታቸው ያለፈ ሰዎቸ ቁጥር ከዚህም ሊልቅ እንደሚችል ተነግሯል።

በሙቀቱ ሳቢያ በርካታ የምርጫ አስፈጻሚዎችም ህይወት አልፏል የተባለ ሲሆን፤ በተለይም በኡታህ ፓርዴሽ ፖሊስ፣ የምርጫ ጣቢያ ኃላፊ እና የምርጫ ጣቢያ ሰራተኞች በስራ ላይ እያሉ ከሞቱት መካከል ናቸው።

ባለፈው አመት ከ62 ሺህ በላይ ሰዎችን ህይወት የቀጠፈው ከባድ ሙቀትና ወበቅ በዚህ አመትም ከፍተኛ ጉዳት እያስከተለ ነው ተብሏል።

አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድረገጽ፡-https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
አሐዱ ራድዮ 94.3 እና ቴሌቪዥን #አሐዱ_

4 months, 2 weeks ago
ግንቦት 26 - 2016 ዓ.ም

ግንቦት 26 - 2016 ዓ.ም
በፖርቹጋል የአየር ትርዒት ላይ በተፈጠረ ግጭት የስፔን ዜግነት ያለው ፓይለት ህይወቱ ማለፉን የፖርቹጋል አየር ሀይል አስታውቋል፡፡

እንደ አየር ሀይሉ መረጃ÷ ከፖርቹጋል መዲና ሊዝበን ከተማ በ178 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በምተገኘው የቤጃ ከተማ ላይ እየተካሄደ በነበረው የአየር ትርዒት ላይ አውሮፕላኖች ተጋጭተው አደጋ ተከስቷል፡፡

በግጭቱ አንደኛው አውሮፕላን ከቤጃ አየር ማረፊያ ክልል ውጭ ሲከሰከስ ሌላኛው አውሮፕላን ደግሞ በአየር ማረፊያው አቅራቢያ መከስከሱ ተገልጿል፡፡

በአደጋው አንድ ፓይለት ህይወቱ ሲያልፍ ሌላኛው ፖርቹጋላዊ ፓይለት ክፉኛ ተጎድቶ ወደ ቤጃ ሆስፒታል መግባቱ ነው የተገለፀው፡፡

የፖርቹጋል አየር ሀይል በተፈጠረው ክስተት ማዘኑን ገልፆ በአደጋው ሕይዎቱን ላጣው አብራሪ ቤተሰቦች መፅናናትን ተመኝቷል፡፡

አደጋውን ተከትሎ በስፔን እና ፖርቹጋል ኤሮቦቲክ ቡድኖች ሲካሄድ የነበረው የአየር ላይ ትርኢት እንዲቋረጥ መደረጉን ዩ ፒ አይ ዘግቧል፡፡

አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድረገጽ፡-https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
አሐዱ ራድዮ 94.3 እና ቴሌቪዥን #አሐዱ_

6 months, 2 weeks ago
መልካም ቀን !

መልካም ቀን !

We recommend to visit

ለማንኛውም አስተያየት እና ጥቆማ ? @Esat_tv_comment_bot

??ኢሳት የኢትዮጵያ አይን እና ጆሮ??

Last updated 1 month, 1 week ago

Last updated 2 months, 1 week ago

እንኳን ደህና መጡ‼

✔ማስታወቂያ ለማሰራት እና ጥቆማ ለመስጠት በዚህ ይጠቀሙ ☞https://t.me/WasuMohammed

✔ ቻናሉን ለመቀላቀል Join ☞http://t.me/Wasulife

ከልብ አመሰግናለሁ♥?

Last updated 2 months ago