Abdurahim Ahmed

Description
We recommend to visit

ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ

Last updated 4 months, 1 week ago

Last updated 4 months ago

ይህ ስለ Manchester United መረጃዎችን የሚያገኙበት የ Telegram ቻናል ነው 🇪🇹
--------------------------------------------------------------
☞︎| ስለ ማንቸስተር ዩናይትድ ትኩስ መረጃዎች
☞| ቀጥታ ስርጭቶች ከየስታድየሞቹ
☞| የዝውውር ዜናዎች
☞| ስለ ማንችስተር ዩናይትድ ታሪኮች

📩 ለማስታወቂያ ስራ DM :- @Marcoabdu

Last updated 2 months, 4 weeks ago

3 months ago
Abdurahim Ahmed
3 months ago

linked in ላይ የቀጥታ ስርጭት events በማዘጋጀት በተለያየ ዘርፍ ላይ ከፍተኛ ልምድ ያላቸው ሰዎችን በመጋበዝ ልምዳቸውን የሚያካፍሉበት፣የተሻለ ትብብር እና ኔትወርክ መፍጠር የምንችልበትን መንገድ አስቤ የጀመርኩ ቢሆንም ላይቭ ኢቨንት ለማዘጋጀት 500 connection እና 15 ሺ ፎሎወር የሚያስፈልግ መሆኑን ለመረዳት ችያለሁ ። በናንተ በኩል ያየሁት ተነሳሽነት ትልቅ መነሳሳት ፈጥሮብኛል ። እናም ይህ ቁጥር እንዲሞላ የlinked in አካውንቴን ፖስት ሼር በማድረግ እንድታስተዋውቅልኝ በአክብሮት እጠይቃለሁ ።

https://www.linkedin.com/in/abdurahim-ahmed-3458a72a1/

3 months ago

Exciting News! 🎉

After a period of inactivity, I’ve revitalized my LinkedIn profile to actively connect and engage with professionals across various industries. I’m eager to share insights, collaborate on innovative projects, and expand my professional network.

I’m also thrilled to announce that I’ll be hosting live conversations and programs on LinkedIn, covering a range of topics and featuring diverse professionals. These sessions aim to foster meaningful discussions and knowledge sharing.

If we’re not already connected on LinkedIn, let’s change that! Click the link below to visit my profile and send a connection request. Together, we can explore new opportunities and foster meaningful professional relationships.

https://www.linkedin.com/in/abdurahim-ahmed-3458a72a1?utm_source=share&utm_campaign=share_via&utm_content=profile&utm_medium=ios_app

Looking forward to connecting with you!

#ProfessionalNetworking #LinkedInLive #CareerGrowth

5 months ago

የደረሰኝ መልእክት እንቅልፍ የሚነሳ እና የሚረብሽ ነበር። አቅመ ደካማ የሆኑ አይነ ስውራን፦

''በይፋ ሶላት ተከልክለናል፤ መስገድ አልቻልንም። እየተደብቅን ነው ለመስገድ የምንሞክረው። መጅሊሱም በዚህ ጉዳይ ላይ መፍትሄ እንድናገኝ አላደረገም። ጓደኞቻችንም ትምህርት ቤቱን ትተው ወጥተዋል። እኛም ከዛሬ ነገ ይስተካከላል በሚል በትግል በለቅሶ ነው ያለነው። እስካሁን መፍትሄ አላገኝንም። በአዳሪ ት/ቤት እየተማርን ሶላት ተከልክለን ዝም በማለታችሁ ነገ አላህ ፊት እንጠይቃችኋለን'' የሚል ነበር፣ መልዕክቱ በለቅሶ የታጀበና እንቅልፍ የሚነሳ ነበር።

ይህ መልዕክት ከደረሰኝ ጊዜ ጀምሮ ተከታታይ ፕሮግራሞችን ከባልደረቦቼ ጋር እያደርስናችሁ ነው። ነገር ግን በሚያሳዝን መልኩ የነሱን አጀንዳ ጉዳዩ አድርጎ የሚንቀሳቀስ ቀርቶ መረጃውን እንኳን በማዳረስ የሚያግዝ የለም። ያለንበት ተጨባጭ እጅግ የሚያስደንግጥ ነው።
ማየት የተሳናቸው ወገኖቻችንን ጉዳይ ችላ በማለታችን እንደ ዑማ ያለንበትን ቁልቁለት ቁልጭ አድርጎም የሚያሳይ ነው።

በፋጢማ ቢንት ሙባረክ ወይም በቀየሩት ስሙ በብርሃን የአይነ-ስውራን ት/ቤት የሚማሩ ሙስሊሞች በሶላታቸው ተፈትነው ፈትነውናል። ተመዝነንም ቀለናል። ለማንኛውም ነገ አላህ ፊት የምንጠየቀው እንደ ግል ነውና በአቅማችን ልክ ቅንጣት ወደኃላ ሳንል ወደፊት ጉዟችን እንቀጥላለን! በጌታችን ፍቃድ በዳዮችንም እንቅልፍ እንነሳለን! ያለንበት ሁኔታ ግን እጅግ ያሳዝናል። ለዚህ ቁልቁለት እንዴት ነበር የፈጠንነው..?!

5 months ago

45 የበደል ቀናት
"..የሌሎችም እጣፈንታ ይህ ከመሆኑ በፊት ድረሱላቸው.."
ተማሪ ጀማል በፋጢማ ቢንት ሙባረክ የአይነ ስውራን ት/ቤት ለመማር ሲመጣ ትልቅ ስንቅን አንግቦ ነበር። የአይነ ስውራን ት/ቤት እምብዛም በሌለበት የሀገራችን ሁኔታ ውስጥ መሠል ት/ቤት ማግኘት ከእድልም በላይ ነበር።
ህልሙ ሁሉ እንደተጨናገፈ ለመረዳት ግን 45 የመከራ ቀናት በቂ ነበሩ። ከሶላት ክልከላ እስከ ሀይማኖት ጫና ድረስ ቢደራረብበት ት/ቤቱን ለቆ ለመውጣት ተገደደ። በት/ቤቱ ውስጥ ያሳለፋቸውን የሰቆቃ ቀናት በዚህ ፕሮግራም ውስጥ ዘርዝሮ ተናግሯቸዋል። ከጋዜጠኛ አብዱረሒም አህመድ ጋር ያደረጉትን ይህንን ቆይታ ዛሬ ምሽት 3:00 ጀምሮ ወደ እናንተ የምናደርስ ይሆናል።
ይጠብቁን...

5 months ago

''ሱረቱል አበሰ'' የቁርኣን ምእራፍ የወረደው አይነ-ስውር በሆነው አብደላ ኢብን ኡሙ መኽቱም ምክኒያት ነው። ዛሬ ማየት የተሳናቸው ወገኖቻችን መሃል ከተማ ላይ በአዳሪ ት/ቤት ሶላት እንዳይሰግዱ ሲከለከሉ ለነሱ ያሳየነው ቸልተኝነት ለኛ ማስተማሪያ ነው።
ረሱል ሶለሏሁ አለይሂ ወሰለም የቁረይሽ መሪዎች ሒዳያ ቢያገኙ ለዲኑ ይጠቅማል ብለው አስበው አይነ-ስውር የሆነው አብደላ ኢብን መኽቱምን ችላ ብለዋል ተብለው የተገሰጹበት ምዕራፍ ነው።

እስኪ አንቀጹን ተመልከቱት፧

ሱረቱ ዐበሰ

عَبَسَ وَتَوَلَّىٰٓ
ፊቱን አጨፈገገ፤ ዞረም፡፡
أَن جَآءَهُ ٱلۡأَعۡمَىٰ
ዕውሩ ስለ መጣው፡፡
وَمَا يُدۡرِيكَ لَعَلَّهُۥ يَزَّكَّىٰٓ
ምን ያሳውቅሃል? (ከኀጢአቶቹ) ሊጥራራ ይከጀላል፡

أَوۡ يَذَّكَّرُ فَتَنفَعَهُ ٱلذِّكۡرَىٰٓ
ወይም ሊገሠጽ ግሠጼይቱም ልትጠቅመው (ይከጀላል)፡

أَمَّا مَنِ ٱسۡتَغۡنَىٰ
የተብቃቃው ሰውማ፤
فَأَنتَ لَهُۥ تَصَدَّىٰ
አንተ ለእርሱ (ለእምነቱ በመጓጓት) በፈገግታ ትቀበለዋለህ፡፡
وَمَا عَلَيۡكَ أَلَّا يَزَّكَّىٰ
ባይጥራራ (ባያምን) ባንተ ላይ ምንም የሌለብህ ስትኾን፡

5 months ago

ይህ ልብ የሚነካ መልእክት ደረሰኝ ! ይህን ወንድማችንን አውቀዋለሁ ካሁን ቀደም ኡስታዝ በድሩ ሁሴንም ቪዲዮ ሰርቶለታል :: የህክምና ብሩ አልሞላለትም :: የቻልነውን እንተባበረው
------
As. Wr.wb
ሰላም ወንድሜ? መቼም በጣም እንዳስቸገርኩህ አውቃለሁ ፣ከብዙ ሰዎች ጋር የመገናኘት እድሉ ስላለህ ባገኘኸው አጋጣሚ የኩላሊት ንቅለ ተከላ እንዳደርግ ሚረዳኝ ግለሰብ / ድርጅት ብትጠይቅልኝ ብዬ ነበር
ይህ እንኳን ባይሳካ ትንሽ ሚረዳኝ ሰው ባገኝ
አቅሜም ተዳከመ ደያላይሲስ ላይ ያለ ሰው ብዙ ፕሮቲን ሉዝ ስለሚያደርግ በምግብ መተካት አለበት አለበለዚያ መቋቋም አይችልም፣አሁን ላይከአላህ በቀር ማንም ሚረዳኝ አጣው ባልናግርህ ደስ ይለኝ ነበር ግን አቅም በላይ ሆነብኝ
ለብዙ ሰው መድረስ የምችለው ሰው ዛሬ ላይ ለራሴ ሆድ ራሱ መድረስ አቃተኝ

እኛ ማናውቀው ትልቁ ነገር ጤናችን ነበር ለካ
አላኩሊሃል አልሃምዱሊላህ ...

ማግኘት ለሚፈልገኝ
ስልክ ቁጥር: +251-911791452

ለመርዳት: ስም ‐ ተማም ጀማል አህመድ
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ: 1000040276053

ኦሮሚያ ህብረት ባንክ (COOP): 1000036464837

አቢሲኒያ ባንክ: 89064503

We recommend to visit

ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ

Last updated 4 months, 1 week ago

Last updated 4 months ago

ይህ ስለ Manchester United መረጃዎችን የሚያገኙበት የ Telegram ቻናል ነው 🇪🇹
--------------------------------------------------------------
☞︎| ስለ ማንቸስተር ዩናይትድ ትኩስ መረጃዎች
☞| ቀጥታ ስርጭቶች ከየስታድየሞቹ
☞| የዝውውር ዜናዎች
☞| ስለ ማንችስተር ዩናይትድ ታሪኮች

📩 ለማስታወቂያ ስራ DM :- @Marcoabdu

Last updated 2 months, 4 weeks ago