ETHIO-MEREJA®

Description
Addisababa, Ethiopia🇪🇹

News & Media Company®
.

USA : Washington

.
Buy ads: https://telega.io/c/ethio_mereja
.
ለጥቆማ እና ማስታወቂያ ለማሰራት
ከታች ያለውን ሊንክ ይጠቀሙ!!
👉 @ethio_merejabot ✔
We recommend to visit

ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ

Last updated 2 months, 3 weeks ago

Last updated 2 months, 2 weeks ago

ይህ ስለ Manchester United መረጃዎችን የሚያገኙበት የ Telegram ቻናል ነው 🇪🇹
--------------------------------------------------------------
☞︎| ስለ ማንቸስተር ዩናይትድ ትኩስ መረጃዎች
☞| ቀጥታ ስርጭቶች ከየስታድየሞቹ
☞| የዝውውር ዜናዎች
☞| ስለ ማንችስተር ዩናይትድ ታሪኮች

📩 ለማስታወቂያ ስራ DM :- @Marcoabdu

Last updated 1 month, 1 week ago

1 month, 2 weeks ago

በእስክንድር ነጋ የሚመራዉ የፋኖ ሀየረል ከመንግስት ጋር የሚያደርገዉ ድርድር በአሜሪካ ወይም በአውሮፓ እንዲሆን ጠየቀ

ከሰሞኑ ታዛቢዎች በተገኙበት ከመንግስት ጋር ውይይት እንዳደረገ እና ለድርድር ዝግጁ እንደሆነ የገለፀው በእስክንድር ነጋ የሚመራው የፋኖ ክንፍ ድርድሩ በውጭ ሀገራት እንዲሆን እየጠየቀ መሆኑ ታውቋል።

የመሠረት ሚድያ ምንጮች እንደተናገሩት ታጣቂ ክንፉ ድርድሩ በአውሮፓ አልያም በአሜሪካ እንዲደረግ ቅድመ ሁኔታ አስቀምጧል።

መንግስት በዋናነት በእስክንድር ከሚመራው የፋኖ ክንፍ  ጋር በቅርቡ በቴክኒክ ኮሚቴ ደረጃ እንደተወያየ እስክንድር ከኢትዮ 360 ጋር ባደረገው ቃለ መጠይቅ ገልፆ ነበር። አክሎም በድርድሩ ላይ የኢጋድ፣ የአውሮፓ ህብረት፣ የአፍሪካ ህብረት እና የአሜሪካ ተወካዮች መገኘታቸውን ገልፆ ነበር።

በውይይቱ ላይ በፋኖ ክንፉ በኩል የተነሱ ነጥቦች መከላከያ አካባቢውን በግዜያዊነትም ቢሆን ለቆ መውጣት፣ ክልሉን ማስተዳደር፣ በፌደራል መንግስቱ በስልጣን መወከል፣ የድሮን ጥቃት ማቆም፣ ለተጎዳው ህዝብ ለህይወት ሳይቀር ካሳ መክፈል እና የመሳሰሉት ናቸው ተብሏል።

በመንግስት በኩል ደግሞ ትጥቅ በመፍታት ወደ ማሰልጠኛ መግባት፣ ጎጃም አካባቢ ላይ ያለውን ነገር ማስተካከል፣ በየከተማው ያለውን አደረጃጀት መረጃ መቀበል፣ ተጠያቂ የሚሆኑ አባላቱን አሳልፎ መስጠት እንዲሁም በምክክር ኮሚሽኑ ውስጥ መካተት ናቸው ተብሏል።

"በመንግስት ዝግ ስብሰባ ላይ ሲያጨቃጭቅ የነበረው የነእስክንድር ክንፍ አቅም ጉዳይ ሲሆን ግምገማውም በሀገር ውስጥና በውጭ ተቀባይነትን ለማግኘት መነጋገሩ እንደ  አማራጭ ተወስዷል" ያሉን ጉዳዩን በቅርበት የሚያውቁ ምንጫችን ሸዋ ላይ ድርጅቱ የተሻለ አቅም እንዳለው፣ ነገር ግን ጎጃም ላይ የለም የሚባል ደረጃ ላይ እንደደረሰ መረጃ ቀርቦ ንግግር ተደርጎበታል ብለዋል።

"ቢያንስ ሸዋን ማቃለሉ እንደ ጥሩ እድል በመታየቱ እና የድርድር ዝርዝር መረጃም የሚቀበሉ አለም አቀፍ ተቋማትም በመንግስት የንግግሩ ቦታ ስለተጓጓዙ ውይይቱ ተደርጓል" በማለት ሂደቱን አስረድተዋል።

"ነገር ግን አሳሳቢው ጉዳይ አሁንም ልክ እንደነ ጃል ሰኒ እንዳይሆን ነው፣ ሙሉ ሰላም ለማምጣት የተወሰነ ቡድን ሳይሆን ሁሉንም አካታች መሆን አለበት" ያሉን ደግሞ በጉዳዩ ዙርያ አስተያየት የሰጡን ተንታኝ ናቸው።

"መንግስት ነገሮችን ያቀሉልኛል ብሎ እየሄደበት ያለው ይህ ነው። ሁሉም ወደ ንግግሩ መግባት አለበት፣ አልያ እንደ  ኦሮምያ አይነት ሁኔታ ይፈጠራል፣ ይባስ ብሎም በቀረው ፋኖ ታጣቂ እና በመንግስት መካከል የሚኖረው ሁኔታ ይባስ ሊካረር ይችላል" በማለት ለሚድያችን ተናግረዋል።

Via መሠረት ሚዲያ

T.me/ethio_mereja ኢትዮ-መረጃ

1 month, 2 weeks ago
**ግብፅና ሶማሊያ ግንኙነታቸውን ለማጠናከር ስትራቴጂካዊ አጋርነት …

ግብፅና ሶማሊያ ግንኙነታቸውን ለማጠናከር ስትራቴጂካዊ አጋርነት መመስረታቸውን አስታወቁ

ትናንት ወደ ግብፅ ያቀኑት ፕሬዚዳንት ሀሰን ሼክ ሞሀመድ ሶማሊያ እና ግብፅ ግንኙነታቸውን ለማጠናከር ስትራቴጂካዊ አጋርነት መመስረታቸውን አስታውቀዋል።

ስምምነቱ ፀጥታን ለማጠናከር፣ ዘላቂ የኢኮኖሚ ልማት ለማምጣት እና በአፍሪካ ቀንድ እና በቀይ ባህር አካባቢዎች ያሉ የጋራ ተግዳሮቶችን ለመቅረፍ ያለመ ነው ተብሏል።

ሁለቱ አገራት የጋራ ስትራቴጂዎችን አፈፃፀም ለመቆጣጠር እና ለትብብር የሚሆኑ አዳዲስ መንገዶችን ለመዳሰስ በፕሬዝዳንት እና ሚኒስትሮች ደረጃ መደበኛ ምክክር ለማድረግ የሚያስችሉ አሰራሮችን ለማቋቋም ማቀዳቸው ተጠቁሟል።

ግብፅ በጎርጎሮሳውያኑ 2024ቱ ወታደራዊ ትብብር ፕሮቶኮል መሠረት ለሶማሊያ የምታደርገውን ወታደራዊ ድጋፍ ለመቀጠል ቃል የገባች ሲሆን፣ ይህም በዋነኛነት በፀረ-ሽብርተኝነት ትግል ፣ በስልጠና እና በድንበር ደህንነት ላይ እንደሚያተኩር ተመላክቷል።

በተጨማሪም ሶማሊያ የፍትህ ስርዓቷን በማሻሻል፣ አዲስ ህገ መንግስት በማዘጋጀት እና ከሀገራዊ ግቦች ጋር ተስማሚ በሆነ መልኩ ምርጫ እንድታዘጋጅ ድጋፍ ታደርጋለች ተብሏል።

1 month, 2 weeks ago

📍አዲስ አበባ😭

የሰው ስጋን የከተፈው ተከሳሽ በሞት እንዲቀጣ ተወሰነበት

ፀሃዬ ቦጋለ በየነ የተባለ ተከሳሽ ከነሐሴ 27 ቀን 2014 ዓ.ም በግምት ከቀኑ 5፡00 እስከ ነሐሴ 28 ቀን 2014 ዓ.ም ከምሽቱ 12፡30 ድረስ ባለው ጊዜ በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 04 አርሴማ ፀበል አከባቢ ባለቤቱ የነበረችውን ሟች ወንበር ላይ ተቀምጣ እያለ ሳታየው ከኋላዋ በመምጣት በሊጥ ማዳመጫ ዱላ ማጅራትዋን በመምታት እራሷን እንድትስት ካደረገ በኋላ እዛው ትቷት ከቤት ወጥቶ በመሄድና ከተወሰነ ሰዓታት በኋላ ተመልሶ በመምጣት ሟች እራሷን ስታ ከወደቀችበት መሬት ለመሬት በመጎተት እቤት ውስጥ ወደሚገኘው መታጠቢያ ቤት በማስገባት አንድ እግሯን ከዳሌዋ ጀምሮ በመቁረጥና ሙሉ የእግሯን ስጋ አጥንቷ ባዶ እስኪሆን ድረስ መልምሎ በማውጣት ስጋዋን አድቅቆ በመክተፍና በመቆራረጥ ሽንት ቤት ውስጥ በመጨመር የቆረጠውን እግሯ ለሁለት በመስበርና በፌስታል በመቋጠር ፀጉሯን በመቀስ በመቁረጥ ቀሪ አስከሬንዋ ላይ ጨርቅና የተለያየ መዘፍዘፊያ በመጫን እዛው መታጠቢያ ቤት ውስጥ በማስቀመጥ እስከ 30/12/2014 ዓ.ም ድረስ ምንም እንዳልተፈጠረ እቤት ውስጥ እያደረ ከቆየ በኋላ ከ1/13/2014 ዓ.ም ጀምሮ እስከ 16/1/2015 ዓ.ም ድረስ ቤቱን ዘግቶ በመሰወሩ ምክንያት በአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ምርመራ ተጣርቶ በፍትህ ሚኒስቴር የጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ ዘርፍ በሴቶችና ህጻናት ላይ ሚፈፀሙ ወንጀሎች ዐቃቤ ሕግ ዳይሬክቶሬት በወ/ሕ/አ539/1/ሀ/ መሰረት በፌዴራል ከፍተኛ ፍ/ቤት ልደታ ምድብ 2ኛ የሰው ግድያና ከባድ ውንብድና ወንጀል ችሎት ክስ ቀርቦበት ክርክር ሲደረግ ቆይቷል፡፡

በክርክሩ ሒደትም የዐቃቤ ሕግ ማስረጃ ከተሰማ በኋላ ተከሳሽ እንዲከላከል ብይን ቢሰጥም የመከላከያ ማስረጃ አቅርቦ የቀረበበትን ክስ ሊከላከል ባለመቻሉ ፍ/ቤቱ በተከሳሽ ላይ የጥፋተኛነት ፍርድ በመስጠት በዕድሜ ልክ ፅኑ እስራት እንዲቀጣ የወሰነ የነበረ ቢሆንም ዐቃቤ ሕግ ባቀረበው ይግባኝ መሰረት የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የፌዴራል ከፍተኛ ፍ/ቤት የወሰነውን የእድሜ ልክ ጽኑ እስራት ውሳኔ በመሻር ተከሳሹ በሞት እንዲቀጣ ወስኖበታል፡፡

(የፍትህ ሚኒስቴር)

T.me/ethio_mereja ኢትዮ-መረጃ

1 month, 2 weeks ago
በየመን ባህር ዳርቻ በጀልባ መስመጥ አደጋ …

በየመን ባህር ዳርቻ በጀልባ መስመጥ አደጋ የ20 ኢትዮጵያውያን ህይወት አለፈ

ጥር 10 ቀን 2017 ዓ.ም ቅዳሜ ምሽት ላይ 35 ኢትዮጵያውያን ስደተኞችን ከየመናዊ ካፒቴን እና ረዳት ካፒቴን ጋር የያዘች ጀልባ ከጂቡቲ ተነስታ በባኒ አል-ሃካም ከተማ አል-ሃጃጃህ አቅራቢያ መስጠሟን በየመን የዓለም አቀፉ የስደተኞች ድርጅት አስታውቋል።

በአደጋው የዘጠኝ ሴቶች እና የአስራ አንድ ወንዶች ህይወት በድምሩ የ20 ኢትዮጵያውያን ስደተኞችን ህይወት አልፏል።

ከአደጋው የቀሩት 15 ኢትዮጵያውያን እና ሁለት የየመን የበረራ ሰራተኞች መትረፍ ችለዋል።

ህገ-ወጥ ስደትን ለመከላከል በርካታ ጥረቶች ቢደረጉም፣ እ.ኤ.አ. በ2024 ብቻ ከ60,000 በላይ መደበኛ ያልሆኑ ስደተኞች የመን መድረሳቸውን ድርጅቱ አመልክቷል።

በጅቡቲ የኢትዮጵያ ኤምባሲ ከባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን በርካታ መደበኛ ያልሆኑ ስደተኞችን በየጊዜው ከጂቡቲ ወደ አገር ቤት የመመለስ ስራ እየሰራ ቢሆንም በህገ-ወጥ ስደት ምክንያት የበርካታ ዜጎች አካል ከመጉደሉም በላይ የብዙዎች ህይወት እያለፈ ይገኛል ተብሏል። በመሆኑም ህብረተሰቡ እና የሚመለከተው መንግስታዊ አካል ይህን ህገ-ወጥ ተግባር ለመከላከል እና የዜጎችን ህይወት ለመታደግ በጋራ መስራት እንደሚያስፈልግ መልእክት መተላለፉን ከኤምባሲው የተገኘው መረጃ ያመለክታል።

T.me/ethio_mereja ኢትዮ-መረጃ

1 month, 2 weeks ago
2ተኛ ዙር

2ተኛ ዙር
የ 5 in 1 Digital Marketing Package ስልጠና

ለ6 ወር የሚቆይ ስልጠና !
-Basic to advanced digital marketing
- Graphic design
-Video editing
-Content Creation
- Wordpress Development

?ኢንተርናሽናል የኢንተርንሺፕ ፕሮግራም እናመቻቻለን
በምዝገባ ላይ ነን :
☎️
0989747878
0799331774

በመራህያን የወደፊት ብሩህ ተስፋዎን የሚዘሩ ክህሎቶችን ይማሩ !!

አድራሻ፡ ሃያ ሁለት ፣ ከጐላጐል ወደ ቦሌ ሚወስደው 4ተኛ ፎቅ ከ Hanan K Plaza አጠገብ ቢጫ ፎቅ ግራውንድ ፍሎር 10B

ለበለጠ መረጃ ቴሌግራም ቻነላችንን ይቀላቀሉ : @merahyan

1 month, 2 weeks ago

?አዲስ አበባ እና አቅራቢያ ለምትገኙ በሙሉ!!

የTikTokና የOnline እቃዎችን በቅናሽ ዋጋ?

? https://telegram.me/AddisEka1 (Join)

? https://telegram.me/AddisEka1

? https://telegram.me/AddisEka1

? https://telegram.me/AddisEka1 (Join)

? https://telegram.me/AddisEka1 (Join)

ሊንኩን በመጫን ይቀላቀሉ! በቅናሽ ይሸምቱ!
?ተአማኒነት እና ጥራት መገለጫችን ነው!

?‍➡️?‍♂‍➡️?‍♂‍➡️?‍♀‍➡️?‍♂‍➡️?‍♂‍➡️?‍♀‍➡️?‍♀‍➡️.... Join us

4 months ago
ETHIO-MEREJA®
4 months ago
**በሸገር ከተማ በዛሬው እለት በደረሰ የእሳት …

በሸገር ከተማ በዛሬው እለት በደረሰ የእሳት አደጋ እናት ከስድስት ወር ልጇ ጋር ህይወታቸው አለፈ

ጥቅምት 26 ቀን 2017 ዓ.ም በሸገር ከተማ ፉሪ ክፍለ-ከተማ በመስሪያና መሸጫ ሼድ ላይ በተነሳ የእሳት አደጋ እናት ከስድስት ወር ልጇ ጋር ህይወቷ  ማለፋን የእሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አስታውቋል።

በእሳት አደጋዉ በሼድ ዉስጥ ካሉ  ሱቆች መካከል ስድስት የንግድ ሱቆች ተቃጥለዋል። የእሳት አደጋዉን ለመቆጣጠር ሶስት የአደጋ መቆጣጠር ተሽከርካሪና ሁለት አምቡላንሶች ከሰላሳ የአደጋ ጊዜ ሰራተኞች ጋር የተሰማራ ሲሆን የእሳት አደጋዉ ወደሌሎች ንግድ ሱቆች ተዛምቶ ተጨማሪ ጉዳት ሳያደርስ መቆጣጠር መቻሉን የኮሚሽኑ የህዝብ ግንኙነት ባለሙያ አቶ ንጋቱ ማሞ ለብስራት ሬዲዮ እና ቴሌቪዥን ተናግረዋል ።

ከንግድ ሱቆቹ መካከል በአንደኛዉ ነዳጅ በፕላስቲክ ጠርሙስ በችርቻሮ የሚሸጥበት ሱቅ በመሆኑ ለሽያጭ የተዘጋጀዉ ነዳጅ ለቃጠሎው መከሰትና መባባስ ምክንያት ሆኗል።

ከስድስት ወር ልጇ ጋር ህይወቷ ያለፈችዉ እናት በእሳት አደጋዉ ከተቃጠሉት የንግድ ሱቆች ዉስጥ በአንደኛዉ ሱቅ የንግድ ስራ ላይ የነበረች መሆኗን አቶ ንጋቱ ጨምረው ለብስራት ተናግረዋል።

ነዳጅ ማከማቸትም ሆነ መሸጥ ያለበት በተፈቀደለትና የአደጋ ደህንነት መስፈርትን ባሟሉ የነዳጅ መሸጫ ጣቢያዎች ዉስጥ ብቻ መከናወን ያለበት በመሆኑ በተለያዩ የንግድ ሱቆች ዉስጥ ነዳጅ ማከማቸትም ሆነ መሸጥ መሰል አደጋዎችን የሚያስከትል በመሆኑ የንግድ ፈቃድ የሚሰጡ አካላት ተገቢዉን ቁጥጥር ማድረግ ይኖርባቸዋልም ሲሉ አክለዋል።

T.me/ethio_mereja ኢትዮ-መረጃ

4 months ago
ETHIO-MEREJA®
4 months, 1 week ago
**ትራምፕ ያልተረጋጋ፣ የበቀል አባዜ የተጠናወተው እና …

ትራምፕ ያልተረጋጋ፣ የበቀል አባዜ የተጠናወተው እና በቁጭት የተጨማለቀ ሰው ነው ሲሉ ካማላ ሀሪስ ተናገሩ!

ዴሞክራቷ ካማላ ሃሪስ በዋሽንግተን በተካሄደ ታላቅ የድጋፍ ሰልፍ ላይ ለተሰበሰቡ በሺዎች ለሚቆጠሩ ሰዎች እንደተናገሩት የሪፐብሊካኑ ተቀናቃኛቸው ዶናልድ ትራምፕ ያልተረጋገጠ ስልጣን ይፈልጋሉ ሲሉ አስጠንቅቀዋል። ሃሪስ በጃንዋሪ 6፣ 2021 ትራምፕ ደጋፊዎቻቸውን በዩናይትድ ስቴትስ ካፒቶል እንዲነሳ ያደረጉትን አመፅ በማስታወስ ተናግረዋል። የካማላ ሀሪስ የድጋፍ ሰልፍ በዋይት ሀውስ አቅራቢያ ባለው ቦታ ከ75,000 በላይ ሰዎች ማክሰኞ ምሽት ላይ ታድመዋል።

ዶናልድ ትራምፕ ማን እንደሆኑ እናውቃለን ያሉት ሃሪስ የቀድሞ ፕሬዝዳንት በ2020 ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ የደረሰባቸውን ሽንፈት ለመቀልበስ ወደ ዩናይትድ ስቴትስ ካፒቶል ታጣቂ ኃይልን ልከው ነበር። "ይህ ሰው ያልተረጋጋ፣ የበቀል አባዜ የተጠናወተው፣ በቁጭት የተጨማለቀ እና ላልተረጋገጠ ስልጣን የሚሻ ሰው ነው" ሲሉ ሃሪስ ከቀጣዩ ማክሰኞ ምርጫ በፊት ተናግረዋል። በፍሎሪዳ ዩኒቨርሲቲ የምርጫ ማዕከል እንደዘገበው በምርጫው ከ53 ሚሊዮን በላይ አሜሪካውያን የአለማችን ባለጸጋ እና ኃያል ሀገርን ማን ለቀጣዮቹ ለአራት አመታት እንደሚመራ ለመወሰን የሚደረገው ፍልሚያ ትንቅንቁ እንዳየለ አስነብቧል።

ሃሪስ በመድረኩ ላይ በአሜሪካ ባንዲራዎች ታጅበው በሰማያዊ እና ነጭ ባነሮች "ነጻነት" የሚል ፅሁፍ ቡስፋት ታይተዋል። በዕድሜ የገፉ እና የኮሌጅ ተማሪዎች፣ ከኒውዮርክ እና ከቨርጂኒያ አቅራቢያ የመጡ ሰዎች ታድመዋል። በርካታ ሴቶች በቡድን ተገኝተዋል። ከአሌክሳንድሪያ ቨርጂኒያ የፌደራል የቀድሞ ሰራተኛ ሳውል ሽዋርትዝ “በፕሬዝዳንት ትራምፕ ወደነበሩት አስከፊ ፖሊሲዎች እንዳንመለስ ይህ ድጋፍ አስፈላጊ ነው” ብለዋል።

T.me/ethio_mereja

We recommend to visit

ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ

Last updated 2 months, 3 weeks ago

Last updated 2 months, 2 weeks ago

ይህ ስለ Manchester United መረጃዎችን የሚያገኙበት የ Telegram ቻናል ነው 🇪🇹
--------------------------------------------------------------
☞︎| ስለ ማንቸስተር ዩናይትድ ትኩስ መረጃዎች
☞| ቀጥታ ስርጭቶች ከየስታድየሞቹ
☞| የዝውውር ዜናዎች
☞| ስለ ማንችስተር ዩናይትድ ታሪኮች

📩 ለማስታወቂያ ስራ DM :- @Marcoabdu

Last updated 1 month, 1 week ago