ናሁ ሰማን(Nahu seman)

Description
በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ
አምላክ አሜን

🚶‍♂️እንኳን ደህና መጡ👋

የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ አስተምህሮና ስርዓትን የጠበቁ የቅዱሳን ስንክሳር የድሮና አዳዲስ መዝሙራት ከነዜማቸው ለማግኘት ቻናላችንን like share subscribers በYouTube✅https://www.youtube.com/@nahu-seman-zema25
በማድረግ ይጎብኙ።
Advertising
We recommend to visit

ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ

Last updated 1 month, 3 weeks ago

ለማንኛውም አስተያየት እና ጥቆማ 👉 @Esat_tv_comment_bot

🇪🇹ኢሳት የኢትዮጵያ አይን እና ጆሮ🇪🇹

Last updated 4 days, 5 hours ago

በዚህ ቻናል ሀገራዊና አለምአቀፋዊ መረጃዎችን በፍጥነት ያገኛሉ❗
የውስጥ መስመር👉http://t.me/ayulaw

Last updated 3 weeks, 2 days ago

1 month, 1 week ago
1 month, 1 week ago
1 month, 1 week ago
1 month, 2 weeks ago
1 month, 2 weeks ago

✞ Gugee koo ✞

Gugee koo garraamii koo
Maariyaam ati qabeenyako
Nan furameem anoo ati qoricha deenyaan
Ulfatoo utaalee nagaa kee dhageenyaan

Kennaa kennaa caaluu naaf laatte haadha koo
Kanaaf daddabalee siwaama arrabni koo
Gugee koo siin jechuu garaa kootu hin obsu
Jecha koo isa kamiin an garaa siciibsu

Lafee keerra han hafe fudhatee dhiiga kee
Fayyisa ilmaan namaa baate cinaachi kee
Golgaa utubaa abiddaa museen arge sidha
Ibiddi waaqummaa sin gubnem dhugaadha

Sulaamaaxiis jennaan gammaddeem lubbuun koo
Biiftu barii baatu fakkaatti gugeen koo
Deebi'i in ga'aa Maariyaam Godaansi kee
Nagaa akka argannuuf nuuf kottu ijoolle keef

Kan museen dugdasaa argee naasuun kufe
Sinboo kee jaallatee garaa keetti hafe
Gad of qabummaan kee ol ol si taasisee
Ulfina hanga hin qabneen Mooticha kan deesse

✥•┈•●◉ ናሁ ሰማን-ዜማ ◉●•┈•✥
╭━─━─━─≪✠≫─━─━─━╮
    ✞ @Nahuseman256
    ✞ @Nahuseman256 ✞        
╰━─━─━─≪✠≫─━─━─━╯

1 month, 2 weeks ago
1 month, 3 weeks ago

በስመ አብ: ወወልድ: ወመንፈስ ቅዱስ: አሐዱ አምላክ

"" ግንቦት 27 ""

+"+ ቅዱስ አልዓዛር +"+

=>ቅዱስ አልዓዛር በሃገረ ቢታንያ ከእህቶቹ ማርያና ማርታ ጋር ይኖር ነበር:: ሦስቱም ድንግልናቸውን ጠብቅው ጌታችንን ያገለግሉት ነበርና አልዓዛርን ከ72ቱ አርድእት ማርያና ማርታን ደግሞ ከ36ቱ ቅዱሳት አንስት ቆጥሯቸዋል::

+በወንጌል ጌታችን ይወዳቸው እንደ ነበር ተገልጧል:: ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሲወድ የሚያበላልጥ ሆኖ አይደለም:: ይልቁኑ በምሥጢር እነርሱ ተወዳጅ የሚያደርጋቸውን ሥራ ይሠሩ እንደ ነበር ሲነግረን ነው እንጂ::

+ቅዱስ መጽሐፍ እንደ ነገረን ጌታችን በነ አልዓዛር ቤት በእንግድነት ይስተናገድ ነበር:: በመጨረሻዋ ምሴተ ሐሙስም ቅዱስ ሥጋውንና ክቡር ደሙን ለሐዋርያቱ ያቀበላቸው በእነዚህ ቅዱሳን ቤት ውስጥ ነው::

+ቅዱስ አልዓዛር በጽኑዕ ታሞ አርፏል:: ቅዱሳት እህቶቹ ማርያና ማርታ ከታላቅ ለቅሶ ጋር ዕለቱኑ ቀብረውታል:: (ዮሐ.11:1) ቸር ጌታችን ክርስቶስ ከ4 ቀናት በሁዋላ ሊያስነሳው ይመጣል::

+ለስም አጠራሩ ስግደት: ክብር: ጌትነት ይድረሰውና አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ አልዓዛር ባረፈ በአራተኛው ቀን ወደ ቢታንያ ደረሰ:: ማርታ ቀድማ ወጥታ ከእንባ ጋር ተቀበለችው:: "አዳም ወዴት ነህ" ያለ (ዘፍ. 3) የአዳም ፈጣሪ "አልዓዛርን ወዴት ቀበራችሁት" አለ:: ቸርነቱ: ባሕርዩ ያራራዋልና ማርያም ስታለቅስ ባያት ጊዜ አብሮ አለቀሰ::

+ከዚያም በባሕርይ ስልጣኑ "አልዓዛር አልዓዛር!" ብሎ አልዓዛርን አስነሳው:: ይሕች ተአምርም በአይሁድ ዘንድ ግርምት ሆነች:: ለጌታም የሞት ምክንያት አደረጉዋት:: ቅድስት ቤተ ክርስቲያን መጽሐፍ ቅዱስን መሠረት አድርጋ እንዲህ ታስተምራለች:: (ዮሐ. 11:1-ፍጻሜው)

+ቅዱስ አልዓዛር ጌታችን ካስነሳው በሁዋላ በበዓለ ሃምሳ መንፈስ ቅዱስን ተቀብሎ (ቁጥሩ ከ72ቱ አርድእት ነውና): ለ40 ዓመታት ወንጌልን አስተምሮ: በ74 ዓ/ም አካባቢ ቆዽሮስ ውስጥ አርፏል::

=>የጌታችን ቸርነቱ: የአልዓዛር በረከቱ ይድረሰን::

=>ግንቦት 27 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት=
1.ቅዱስ አልዓዛር ጻድቅ ሐዋርያ
2.ቅዱሳት ደናግል ማርያ ወማርታ
3.አባ ዮሐንስ ሊቀ ዻዻሳት

=>ወርኀዊ በዓላት
1.የጌታችንና አምላካችን መድኃኔ ዓለም ክርስቶስ በዓለ ስቅለት
2.አቡነ መብዐ ፅዮን ጻድቅ
3.ቅዱስ መቃርስ (የመነኮሳት ሁሉ አለቃ)
4.ቅዱስ ያዕቆብ ዘግሙድ
5.ቅዱስ ገላውዴዎስ ሰማዕት (ንጉሠ ኢትዮዽያ)
6.ቅዱስ ቢፋሞን ጻድቅና ሰማዕት
7.ማር ቅዱስ ፊቅጦር ሰማዕት

=>+"+ ጌታ ኢየሱስም "ብታምኚስ የእግዚአብሔርን ክብር እንድታዪ አልነገርሁሽምን?" አላት . . . ይሕንም ብሎ በታላቅ ድምጽ "አልዓዛር ሆይ! ወደ ውጭ ና" ብሎ ጮኸ:: የሞተውም እጆቹና እግሮቹ በመግነዝ እንደ ተገነዙ ወጣ:: ፊቱም በጨርቅ እንደ ተጠመጠመ ነበረ:: ጌታ ኢየሱስም "ፍቱትና ይሂድ ተውት" አላቸው:: +"+ (ዮሐ. 11:40-44)

<<< ወስብሐት ለእግዚአብሔር >>>

Telegram

ናሁ ሰማን(Nahu seman)

በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን ***🚶‍♂️***እንኳን ደህና መጡ***👋*** የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ አስተምህሮና ስርዓትን የጠበቁ የቅዱሳን ስንክሳር የድሮና አዳዲስ መዝሙራት ከነዜማቸው ለማግኘት ቻናላችንን like share subscribers በYouTube***✅***https://www.youtube.com/@nahu-seman-zema25 በማድረግ ይጎብኙ።

***✝***✞***✝*** በስመ አብ: ወወልድ: ወመንፈስ ቅዱስ: አሐዱ አምላክ ***✝***✞***✝***
1 month, 3 weeks ago

በስመ አብ : ወወልድ : ወመንፈስ ቅዱስ : አሐዱ አምላክ . . . አሜን ::

+" አቡነ ሃብተ ማርያም ጻድቅ "+

=>እኒህ ጻድቅ የሃገራችን ኮከበ ገዳም ናቸው:: "ጽድቅና ትሩፋት እንደ ሃብተ ማርያም" እንዲሉ አበው:: ባሕር ከሆነ ጣዕመ ሕይወታቸው ጥቂቱን ለበረከት እንካፈል::

+ጻድቁ መካነ ሙላዳቸው ሽዋ (የራውዕይ) ውስጥ ሲሆን አባታቸው ፍሬ ቡሩክ : እናታቸው ደግሞ ቅድስት ዮስቴና ትባላለች:: በተለይ ቅድስት ዮስቴና እጅግ ደመ ግቡ : ምጽዋትን ወዳጅ : ቡርክት ሴት ነበረች:: እንዲያውም ከጻድቁ መወለድ በፊት መንና ጭው ካለ በርሃ ገብታ ነበር::

+ግን የበቃ ግኁስ አግኝቷት "ከማሕጸንሽ ደግ የሥላሴ ባርያ አለና ተመለሽ" ብሏት እንደ ገና ተመልሳለች:: ጻድቁን ወልዳ አሳድጋም እንደ ገና መንና በተጋድሎ ኑራ 7 አክሊላትን ተቀብላ ዐርፋለች::

+ወደ ጻድቁ ዜና ሕይወት ስንመለስ አቡነ ሃብተ ማርያም ገና ሕጻን እያሉ ከእናታቸው ጋር ቆመው ሲያስቀድሱ "እግዚኦ መሐረነ ክርስቶስ" ሲባል ይሰማሉ:: ይሕችን ጸሎት በሕጻን አንደበታቸው ይዘው ሌሊት ሌሊት እየተነሱ "ማረን እባክህን?" እያሉ ይሰግዱ ነበር::

+የ5 ዓመት ሕጻን እንዲህ ሲያደርግ ማየቱ በእውነት ይደንቃል:: ትንሽ ከፍ ብለው በእረኝነት ሳሉም ፍጹም ተሐራሚና ጸዋሚ ነበሩ:: ጸጋው ስለ በዛላቸውም ልጅ ሆነው ብዙ ተአምራትን ሰርተዋል:: የፈጣሪውን ስም ያቃለውን አንድ እረኛም በዓየር ላይ ሰቅለው አውለውታል::

+ከዚያ ግን ለአካለ መጠን ሲደርሱ ወደ ት/ቤት ገብተው : መጻሕፍትንም አጥንተው መንነዋል:: በአባ መልከ ጼዴቅ እጅ ከመነኮሱ በሁዋላ የሠሩትን ትሩፋትና የነበራቸውን ተጋድሎ ግን የኔ ብጤ ደካማ ሰው ሊዘረዝረው አይችልም::

*ባሕር ውስጥ ሰጥመው 500 ጊዜ ይሰግዳሉ::

*በየቀኑ 4ቱን ወንጌልና 150 መዝሙረ ዳዊትን ይጸልያሉ:: (መጽሐፍ ቅዱስን ማንበብ ታላቅ ጸሎት ነው)

*በ40 ቀናት : ቀጥሎም በ80 ቀን አንዴ ብቻ ይመገባሉ::

*ምግባቸው ደግሞ ሣርና ቅጠል ብቻ ነው::

*በየዕለቱ ያለ ማስታጐል ማዕጠንት ያሳርጋሉ:: (ካህን ናቸውና)

*ዘወትር በንጽሕና ቅዱስ ሥጋውን ይበላሉ : ክቡር ደሙን ይጠጣሉ::

*በፍጹም በልባቸው ውስጥ ቂምን : መከፋትን አላሳደሩም::

+በእነዚህና በሌሎች ትሩፋቶቻቸው ደስ የተሰኘ ጌታም ለጻድቁ የእሳትና የብርሃን ሠረገላን ሰጥቷቸው በዚያ እየበረሩ ኢየሩሳሌም ይሔዱ ነበር:: ከብዙ የተጋድሎ ዘመናት በሁዋላም የክብር ባለቤት መድኃኒታችን ክርስቶስ አዕላፍ መላእክትን አስከተትሎ መጥቶ አላቸው::

"1.ስለ እኔ ረሃብና ጥምን ስለ ታገስክ:
2.ስለ ምናኔሕ:
3.ስለ ተባረከ ምንኩስናህ:
4.ስለ ንጹሕ ድንግልናህ:
5.ቂምና በቀልን ስላለመያዝህ:
6.ስለ ንጹሕ ክህነትህና ማዕጠንትህ:
7.ቅዱስ ወንጌልን በፍቅር ስለ ማንበብህ 7 አክሊላትን እሰጥሃለሁ::"

+"በሰማይም ከመጥምቁ ዮሐንስ ጐን : 500 የእንቁ ምሰሶዎች ያሉበትን አዳራሽ ሰጥቼሃለሁ:: በስምህ የሚለምኑ : በቃል ኪዳንህ የሚማጸኑትንም ሁሉ እንድምርልህ 'አማንየ! በርእስየ!' ብዬሃለሁ" አላቸው::

+ቅዱሳን መላእክትም "ሃብተ ማርያም ወንድማችን" ሲሉ አቀፏቸው:: ጌታ ግን በዚያች ሰዓት አንድም ሦስትም ሆኖ ታያቸውና አቅፎ 3 ጊዜ ሳማቸው:: ከፍቅሩ ጽናትም የተነሳ ነፍሳቸው ከሥጋቸው ተለየች:: በዝማሬም ወሰዷት:: {ይህች ቀን (ግንቦት 26) ለጻድቁ ዕለተ ልደታቸው ናት::}

=>አምላከ አበው ወሰማዕት ጣዕመ ፍቅራቸውን: ክብራቸውን: ጸጋ በረከታቸውንም ይክፈለን::

=>+"+ እግዚአብሔር ፍርድን ይወድዳልና::
ቅዱሳኑንም አይጥላቸውምና::
ለዘለዓለምም ይጠብቃቸዋል . . .
ጻድቃን ምድርን ይወርሳሉ::
በእርስዋም ለዘላለም ይኖራሉ::
የጻድቅ አፍ ጥበብን ያስተምራል::
አንደበቱም ፍርድን ይናገራል::
የአምላኩ ሕግ በልቡ ውስጥ ነው::
በእርምጃውም አይሰናከልም:: +"+ (መዝ. 36:28-31)

<<< ወስብሐት ለእግዚአብሔር >>>

1 month, 3 weeks ago

መርቆሬዎስ

መርቆሬዎስ ሰማዕት ገባሬ ተዐምር ወኃይል
ምርሐኒ ለወልድከ ፍና ጽድቅ ወሣህል/2/
       አዝ-----
የወንጌልን ቃል የፈጸምክ
በመንፈስ ቅዱስ የታተምክ
የአብ ወዳጁ ፒሉፓዴር
ሰማዕቱ ልብሰ ሠንፔር
   መኑ መኑ ዘይትማስለከ መኑ
   እንበለ ጊዮርጊስ ሰማዕት ዘአዳም ሥኑ
       አዝ-----
ምሉዓ ጥበብ ወሞገስ
ገብረ ኢየሱስ ክርስቶስ
በምግባር የኖርክ በእምነት
ዓለምን የናቅህ ለእውነት
   መኑ መኑ ዘይትማስለከ መኑ
   እንበለ ጊዮርጊስ ሰማዕት ዘአዳም ሥኑ
       አዝ-----
ዕጉሰ ሕማም ወምንዳቤ
እናመስግንህ በይባቤ
ገድልን የፈጸምክ በክብር
መርቆሬዎስ ገባሬ ተአምር
   መኑ መኑ ዘይትማስለከ መኑ
   እንበለ ጊዮርጊስ ሰማዕት ዘአዳም ሥኑ
       አዝ-----
ልቡሰ ዓቢይ ወግርማ
ዝናህ በዓለም ተሰማ
ዳኬዎስ ንጉስ አፈረ
በሰማዕትነት ስምህ ከበረ
   መኑ መኑ ዘይትማስለከ መኑ
   እንበለ ጊዮርጊስ ሰማዕት ዘአዳም ሥኑ

🙏🙏አዲስ ዝማሬ በዘማሪት ሲስተር ሕይወት ተፈሪ 🙏🙏

✥•┈•●◉ ናሁ ሰማን-ዜማ ◉●•┈•✥
╭━─━─━─≪✠≫─━─━─━╮
    ✞ @Nahuseman256
    ✞ @Nahuseman256 ✞        
╰━─━─━─≪✠≫─━─━─━╯

2 months ago

++"+ በተኩላና በእባብ ላይ ትጫማለህ::
አንበሳውንና ዘንዶውን ትረግጣለህ::
በእኔ ተማምኗልና አስጥለዋለሁ::
ስሜንም አውቁዋልና እጋርደዋለሁ::
ይጠራኛል እመልስለትማለሁ::
በመከራውም ጊዜ ከእርሱ ጋር እሆናለሁ::
አድነዋለሁ: አከብረውማለሁ::
ረጅም እድሜን አጠግበዋለሁ::
ማዳኔንም አሳየዋለሁ:: +"+ (መዝ. 90:13-16)

<<< ወስብሐት ለእግዚአብሔር >>>

Telegram

ናሁ ሰማን(Nahu seman)

በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን ***🚶‍♂️***እንኳን ደህና መጡ***👋*** የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ አስተምህሮና ስርዓትን የጠበቁ የቅዱሳን ስንክሳር የድሮና አዳዲስ መዝሙራት ከነዜማቸው ለማግኘት ቻናላችንን like share subscribers በYouTube***✅***https://www.youtube.com/@nahu-seman-zema25 በማድረግ ይጎብኙ።

++"+ በተኩላና በእባብ ላይ ትጫማለህ::
We recommend to visit

ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ

Last updated 1 month, 3 weeks ago

ለማንኛውም አስተያየት እና ጥቆማ 👉 @Esat_tv_comment_bot

🇪🇹ኢሳት የኢትዮጵያ አይን እና ጆሮ🇪🇹

Last updated 4 days, 5 hours ago

በዚህ ቻናል ሀገራዊና አለምአቀፋዊ መረጃዎችን በፍጥነት ያገኛሉ❗
የውስጥ መስመር👉http://t.me/ayulaw

Last updated 3 weeks, 2 days ago