Why Pay for Entertainment? Access Thousands of Free Downloads Now!

ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

Description
Official ERA Telegram Channal
በዚህ የቴሌግራም ቻናል
የመንገድ ዜናዎችን
የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን
የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።
Advertising
We recommend to visit

ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ

Last updated hace 1 día, 17 horas

ለማንኛውም አስተያየት እና ጥቆማ 👉 @Esat_tv_comment_bot

🇪🇹ኢሳት የኢትዮጵያ አይን እና ጆሮ🇪🇹

Last updated hace 5 días, 6 horas

Last updated hace 5 días, 19 horas

1 day, 7 hours ago
ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር
1 day, 7 hours ago
ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር
1 day, 7 hours ago

ሦስት ዞኖችን የሚያገናኘው የሞርካ - ጊርጫ ጨንቻ መንገድ ግንባታ ፕሮጀክት 72 በመቶ ደረሰ

አዲስ አበባ ፣ ሚያዚያ 24 ቀን 2016 ዓ / ም ( ኢ.መ.አ ) ፡ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የጋሞ፣ ጎፋ እና ወላይታ ዞኖችን የሚያገናኘው የሞርካ - ጊርጫ- ጨንቻ መንገድ ስራ ፕሮጀክት አፈጻጸም 72 በመቶ ደርሷል።

ይህ መንገድ 72.663 ኪ.ሜ የሚሸፍን ሲሆን የመንገዱ ስፋት በወረዳ ከተማዎች 21.5 ሜ.፤በቀበሌ ከተማዎቸ 12 ሜ. በገጠር 8 ሜ ስፋት አለው ።

በአሁኑ ወቅት በመንገድ ግንባታው የ39 ነጥብ 45 ኪ.ሜ. የአስፋልት ንጣፍ ሥራ የተከናወነ ሲኾን፣ የሦስት ድልድዮች ግንባታ ሥራም ሙሉ በሙሉ ተጠናቋል። በመኾኑም ከአጠቃላይ የመንገዱ ክፍል 52 ኪሎሜትሩ ወይም 72 በመቶው ተጠናቋል።

የፕሮጀክቱን ቀሪ የግንባታ ሥራ በቀጣይ በጀት ዓመት ለማጠናቀቅ ዕቅድ ተቀምጦ እየተሠራ ይገኛል።
በዲታ እና ደረማሎ ወረዳዎች መካከል ያለው ተራራ ሁለቱን ወረዳዎች ለሁለት ለያይቶ የነበረ ሲሆን ፕሮጀክቱ ችግሩን በመቅረፍ ሁለቱን አርስ በእርስ በቀላሉ ከማገናኘት አኳያ ትልቅ ሚና ይጫወታል፡፡

ከኪ.ሜ 39+000 እስክ ኪ.ሜ 45+000 ያለው ለዚህ ተራራማ የመንገዱን ክፍል አስፈላጊውን የዲዛይን መፍትሄ በጥናት የመስጠት ሥራ እየተከናወነ ቢሆንም ወሰን ማስከበር ጋር በተያያዘ በአፈጻጸሙ ላይ ተጽዕኖ አሳድሯል፡፡
የሶዶ አካባቢ የግንባታ ፕሮጀክቶች ማኔጀመንት ጽ/ቤት ከአከባቢው መስተዳድር አካላት እና ከአከባቢው ነዋሪዎች ውይይቶች በማድረግ የወሰን ማስከበር ችግሩ ለመፍታት ጥረት እያደረጉ ይገኛሉ፡፡

ለመንገዱ የሚውለው ብር 1,967,496,759.60 (አንድ በሊዮን ዘጠኝ መቶ ስልሳ ሰባ ሚሊዮን አራት መቶ ዘጠና ስድስት ሺህ ሰባት መቶ ሃምሳ ዘጠኝ ብር ከ ስልሳ ሳንቲም) በኢትዮጵያ መንግስት የሚሸፈን ነው፡፡

ግንባታውን እያካሄደ ያለው ቤጂንግ አርባን ኮንስትራክሽን ግሩፕ /ቢዩሲጂ/ ሲሆን የማማከሩን ሥራ ደግሞ ኮር ኮንሰልቲንግ ኢንጂነርስ ኃላ/የተ/የግ/ማ እያከናወነ ይገኛል።
ሞርካ፣ዋጫ፣ወይዛ፣ሁሉ ቆዴ፣ዛዳ፣ዶኮና ጨንቻ መንገዱ በዋናነት የሚያገናኛቸው ከተሞች ናቸው። መንገዱ ከዚህ ቀደም በጥርጊያ ደረጃ የነበረ ሲሆን በአሁኑ ወቅት በአስፓልት ኮንክሪት ደረጃ እየተገነባ ይገኛል።

የዚህ መንገድ መገንባት የ127 ዓመት ዕድሜ ያላት ጨንቻ ከተማን ሐብቷንና ልምላሜዋን እንድትጠቀም ፡፡ አካባቢው ከፍተኛ የአፕል ፣ድንች ፣የስንዴ ምርት የሚገኝበት በመሆኑ ህብረተሰቡን ተጠቃሚ ከማድረግም በላይ ለክልላዊና ሀገራዊ ኢኮኖሚያዊ ፋይዳው ከፍተኛ ነው።

በተጨማሪ
› አጭር መልዕክት 8561
› ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770
› ድህረገጽ www.era.gov.et
› ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et
› ቴሌግራም https://t.me/ethioroads
› ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd
› ኢሜል communication@era.gov.et
› ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

Facebook

Log in or sign up to view

See posts, photos and more on Facebook.

1 week, 3 days ago
ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር
1 week, 3 days ago
ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር
1 week, 3 days ago

በቡልቡላ-አላጌ-ባራ-ሚቶ መንገድ ሥራ ፕሮጀክት አስፋልት ማንጠፍ ተጀመረ

አዲስ አበባ ፣ ሚያዚያ 15 ቀን 2016 ዓ.ም (ኢ መ አ) የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልልን ከኦሮሚያ ጋር በቅርበት በሚያገናኘው የቡልቡላ - አላጌ መንገድ ሥራ ፕሮጀክት አስፋልት ማንጠፍ ተጀምሯል፡፡

38 ኪሎ ሜትር ርዝመትን የሚሸፍነው ይኸው የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት በአስፋልት ኮንክሪት ደረጃ በመገንባት ላይ ይገኛል፡፡ ግንባታውን እያካሄደ የሚገኘው ሀገር በቀሉ የስራ ተቋራጭ ኪቢሽ ኮንስትራክሽን ሲሆን ፣ ዩናይትድ አማካሪ ማሀንዲሶች (ዩኒኮን) ደግሞ የፕሮጀክቱን የማማከርና የቁጥጥር ስራ እያከናወነ ይገኛል ።

መንገዱ ከፌደራል መንግስት በተመደበ 878,514,732 (ስምንት መቶ ሰባ ስምንት ሚሊዮን አምስት መቶ አሥራ አራት ሺህ ሰባት መቶ ሰላሳ ሁለት ) ብር ወጪ ነው እየተገነባ የሚገኘው፡፡

በፕሮጀክቱ አሁን ላይ አስፋልት የማንጠፍ ሥራ የተጀመረ ሲሆን ፣ ከአጠቃላይ የመንገዱ ክፍል 8 ኪሎሜትሩን አስፋልት የማልበስ ሥራ ተሠርቷል፡፡  

በተጨማሪም የ 33 ኪሎ ሜትር አፈር ሙሌት ፣ የ30 ኪሎ ሜትር ሰብቤዝ ፣ የ15 ኪሎ ሜትር ቤዝኮርስ እንዲሁም የ 72 በመቶ የስትራክቸር ሥራዎች ተሠርተዋል፡፡ ከዚህም ባሻገር የአነስተኛ እና ከፍተኛ ከልቨርቶች ግንባታ ሥራም የፕሮጀክቱ አካል ነው፡፡ ይህም የፕሮጀክቱን አጠቃላይ አፈጻጸም 62 ነጥብ 24 በመቶ ያደርሰዋል፡፡ አሁን ላይ ግንባታውን በቀጣይ ዓመት ለማጠናቀቅም ትኩረት ተሰጥቶ እየተሠራ ነው፡፡  

በመንገዱ ወሰን ውስጥ ያልተነሱ ንብረቶች ፣ የውኃ እና የመብራት መሥመሮች በፕሮጀክቱ ሂደት ላይ ተፅዕኖ እያሳደሩ ሲሆን ፣ የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ቡታጅራ አካባቢ ኮንስትራክሽን ፕሮጀክቶች ጽ/ቤት ከወረዳ ፣ ከዞን እና ክልል አመራሮች ጋር በመቀናጀት ችግሩን ለመቅረፍ ጥረት እያደረገ ይገኛል፡፡   

ከባቱ -ሐዋሳ በመሰራት ላይ ካለዉን ፈጣን መንገድ ተገንጥሎ እየተካሄደ ያለው ይኸው ፕሮጀክት መነሻውን ቡልቡላ በማድረግ በመስመሩ የሚገኙትን ጂዶ ፣ አላጌ ግብርና ኮሌጅ እና ሚቶ ከተሞችን ደረጃውን በጠበቀ መንገድ ያስተሳስራል፡፡ የመንገድ ግንባታው ሲጠናቀቅ ከዚህ ቀደም ለመጓዝ ይወስድ የነበረውን የሁለት ሠዓታት የጉዞ ጊዜ ወደ ግማሽ ሠዓት ያሳጥረዋል፡፡

በተጨማሪም በአካባቢው የሚመረቱ  የበቆሎ ፣ የቦሎቄ  እና የበርበሬ ምርቶችን ወደ ገበያ  ለማውጣት ብሎም የተሻለ የጤና እና የትምህርት ተቋማት ተደራሽነትን ለማስፋት ጉልህ አስተዋፅኦ እንደሚያበረክት ይታመናል፡፡

በተጨማሪ
› አጭር መልዕክት 8561
› ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770
› ድህረገጽ www.era.gov.et
› ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et
› ቴሌግራም https://t.me/ethioroads
› ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd
› ኢሜል communication@era.gov.et
› ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

Facebook

Log in or sign up to view

See posts, photos and more on Facebook.

2 weeks, 4 days ago
ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር
2 weeks, 4 days ago
ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር
2 weeks, 4 days ago

በዘጠኝ ወራት ከ10.35 ቢሊዮን ብር በላይ የመንገድ ፈንድ ገቢ ተሰበሰበ

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 7 ቀን 2016 ዓ.ም (ኢመአ)፡ በዘጠኝ ወራት ውስጥ ከተለያዩ የገቢ ምንጮች ለመንገዶች ጥገና እና የመንገድ ደህንነት ማስፈጸሚያ የሚሆን ብር 10,356,019,307.40 የመንገድ ፈንድ ገቢ ተሰብስቧል፡፡ በተሰበሰበው ገቢ የወቅታዊና መደበኛ የመንገድ ጥገናዎች ሥራዎችም ተከናውነዋል፡፡

ገቢው የተገኘው በነዳጅ ላይ ከተጣለ ታሪፍ ብር ፣ ከተሸከርካሪ ዘይትና ቅባት፣ ከመንገድ ጠቀሜታ ክፍያ ብር እና በክብደት ላይ የተመሰረተ ዓመታዊ የተሸከርካሪ ፈቃድ ማደሻ ነው፡፡

የተሰበሰበውን ገቢ ለመንገድ ጥገና ከማዋል አንፃር በዘጠኝ ወራት ጊዜ ውስጥ ባቀረቡት የክፍያ ሰርቲፊኬት መሰረት የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር(ኢመአ) ብር 4,163,410,907.23 ፣ የክልል ገጠር መንገድ ኤጀንሲዎች ብር 1,726,478,976.99 እና የከተማ መንገድ ኤጀንሲዎች ብር 916,865,104.27 እንዲሁም ለድጋፍ ሰጪ (የአማካሪ ክፍያ) ብር 17,471,811.59፣ ለመንገድ ደህንነት እና መድን ፈንድ አገልግሎት ብር 26,519,109.14 እና የባንክ ፤ለፖስታ ቤት ኮሚሽን ክፍያ ብር 12,770,080.33 በአጠቃለይ በመንገድ ጥገና ጥቅም ላይ እንዲያውሉ ብር 6,863,515,989.55 ተከፍሏቸዋል፡፡

የተመደበው በጀት ለተገቢው አገልግሎት መዋሉን ከማረጋገጥ አኳያ በኢመአ፣ በክልል እና በከተማ የመንገድ ኤጀንሲዎች በሚያስተዳድሯቸው ፕሮጀክቶች ላይ የመስክ ቅኝት የማድረግና የምህንድስና (ቴክኒካል) ኦዲት ሥራ ተከናውኗል፡፡

በተደረገው የመስክ ምልከታና የተለያዩ መደበኛ፣ ወቅታዊና ድንገተኛ የመንገድ ጥገና ሥራዎች መከናወናቸውን ማረጋገጥ ተችሏል፡፡ የመንገድ ፈንዱ መንገዶችን ከመጠበቅና ከመንከባከብ አንጻር ጉልህ አስተዋጽኦ እያበረከተ ይገኛል፡፡ ውድ የሀገር መዋለ ነዋይ የፈሰሰባቸው መንገዶች እንዳይጎዱ ተገቢውን ጥንገና እንዲያገኙ የማድረጉ ሥራ ተጠናክሮ ይቀጥላል ።

መንገዶች ተገቢውን ጥገና በወቅቱ እንዲያገኙ እና ለመንገድና ትራፊክ ደህንነት ሥራዎች ማስፈፀሚያ በቂና የማያቋርጥ የገንዘብ ፈሰስ በማስፈለጉ ከተለያዩ የገቢ ምንጮች ገቢን ለማሰበሰብ፣ ለመመደብና ለማስተዳደር የመንገድ ፈንድ በአዋጅ ቁጥር 66/89 መቋቋሙ ይታወቃል።

በተጨማሪ
› አጭር መልዕክት 8561
› ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770
› ድህረገጽ www.era.gov.et
› ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et
› ቴሌግራም https://t.me/ethioroads
› ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd
› ኢሜል communication@era.gov.et
› ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

Facebook

Log in or sign up to view

See posts, photos and more on Facebook.

2 months, 1 week ago

Specific Procurement Notice
Invitation for Initial Selection
Works (Design and Build)

We recommend to visit

ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ

Last updated hace 1 día, 17 horas

ለማንኛውም አስተያየት እና ጥቆማ 👉 @Esat_tv_comment_bot

🇪🇹ኢሳት የኢትዮጵያ አይን እና ጆሮ🇪🇹

Last updated hace 5 días, 6 horas

Last updated hace 5 días, 19 horas