ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።
@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna
#ኢትዮጵያ
Last updated 2 months, 3 weeks ago
Last updated 2 months, 2 weeks ago
ይህ ስለ Manchester United መረጃዎችን የሚያገኙበት የ Telegram ቻናል ነው 🇪🇹
--------------------------------------------------------------
☞︎| ስለ ማንቸስተር ዩናይትድ ትኩስ መረጃዎች
☞| ቀጥታ ስርጭቶች ከየስታድየሞቹ
☞| የዝውውር ዜናዎች
☞| ስለ ማንችስተር ዩናይትድ ታሪኮች
📩 ለማስታወቂያ ስራ DM :- @Marcoabdu
Last updated 1 month, 1 week ago
የዲላ - ቡሌ - ሐሮ - ዋጮ መንገድ ፕሮጀክት አፈጻጸም በሚሻሻልበት ሁኔታ ላይ ውይይት ተካሄደ
ዲላ፣ የካቲት 13፣ 2017 (ኢ መ አ):- የኦሮሚያ እና የደቡብ ኢትዮጵያ ክልሎችን የሚያገናኘው የዲላ - ቡሌ - ሐሮ - ዋጮ 68 ኪሎሜትር መንገድ ፕሮጀክት ያጋጠሙ ችግሮችን በመቅረፍ አፈጻጸሙ በሚሻሻልበት ሁኔታ ላይ በዲላ ከተማ ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት ተካሂዷል።
በውይይቱ ላይ በከተማ እና መሠረተ-ልማት ሚንስቴር ሚንስትር ዴኤታ ክቡር አቶ የትምጌታ አሥራት የተመራ ድጋፋዊ ሱፐርቪዥን እንዲሁም የጌዲዮ ዞን ከፍተኛ አመራር አካላት ተሳትፈዋል።
በወቅቱ የመንገድ ፕሮጀክቱ ከአንድ ዓመት ከስድስት ወር በፊት ቢጀመርም አሁንም ድረስ እልባት ያላገኙ የወሰን ማስከበር ሥራዎች እንዲሁም የጠጠር መፍጫ ማሽን (ክሬሸር) መትከያ ቦታ በዞን አስተዳደሩ አለመፈቀዱ ጋር ተያይዞ ፕሮጀክቱ ለከፍተኛ ወጪ እና መጓተት መዳረጉ ተመልክቷል።
ለዚህም የባለድርሻ አካላት ትብብር እና ቅንጅት ማነስ ችግሩን በቀላሉ ላለመፈታቱ በመንስኤነት ተነስቷል።
በመኾኑም በአጭር ጊዜ ውስጥ የመንገድ ወሰኑን ከንብረት ነጻ ለማድረግ እና የጠጠር መፍጫ ማሽን (ክሬሸር) መትከያ ቦታ ችግሩን በመቅረፍ የመንገድ ግንባታውን ለማፋጠን እንደሚሠራ መድረኩ ከጋራ መግባባት ላይ ደርሷል።
በዚህ ረገድ የመንገድ ግንባታው በታለመለት ጊዜ ተጠናቅቆ ተገቢውን አገልግሎት መስጠት እንዲችል የአካባቢው ማኅበረሰብ እና በየደረጃው የሚገኙ የመስተዳድር አካላት አስፈላጊውን ድጋፍ እና ትብብር እንዲያደርጉ ተጠይቋል።
የመንገድ ፕሮጀክቱ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በጌዲኦ ዞን እና በኦሮሚያ የጉጂ ዞኖችን ያገናኛል። ለግንባታው 2 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር የተመደበ ሲኾን፥ ወጪው በአረብ ልማት ባንክ፣ በነዳጅ ላኪ ሀገራት (ኦፔክ) እና በፌደራል መንግስት ይሸፈናል።
ዓለም-አቀፉ ቻይና ሲቪል ኢንጅነሪንግ ኮንስትራክሽን ኮርፖሬሽን ግንባታውን ያከናውናል። ኮር ኮንሰልቲንግ ኢንጅነርስ የማማከር እና የቁጥጥር ሥራውን ያከናውናል።
በተጨማሪ
› አጭር መልዕክት 8561
› ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770
› ድህረገጽ www.era.gov.et
› ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et
› ቴሌግራም https://t.me/ethioroads
› ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd
› ኢሜል [email protected]
› ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads
የያቤሎ ከተማ ተለዋጭ መንገድ ፕሮጀክትን በተያዘው ዓመት ለማጠናቀቅ እየተሠራ ነው
ያቤሎ፣ ታኅሣሥ 03፣ 2017 ዓ.ም (ኢ መ አ):- በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ቦረና ዞን በ304 ሚሊዮን ብር ወጪ እየተገነባ የሚገኘውን የያቤሎ ከተማ ተለዋጭ መንገድ ፕሮጀክት በተያዘው ዓመት ለማጠናቀቅ እየተሠራ ነው።
የመንገድ ፕሮጀክቱ 7 ነጥብ 44 ኪሎሜትር የሚሸፍን ሲኾን፥ የዞኑ መቀመጫ ለኾነችው ያቤሎ ከተማ ተጨማሪ አማራጭ ኾኖ የሚያገለግል ነው። በተለይም በያቤሎ -ኬላ ነባር መንገድ ላይ የሚስተዋለውን የትራፊክ ጭንቅንቅ ያስቀራል፡፡
ከዚህም ባለፈ በአቅራቢያ ከሚገኙ የጎሮቤት ሀገራት ጋር ያለውን የወጪ እና የገቢ ንግድን በማቀላጠፍ በኩልም አዎንታዊ ሚና ይጫወታል፡፡
አሁን ላይ የፕሮጀክቱ አጠቃላይ አፈጻጸም 91 ነጥብ 43 በመቶ ደርሷል። እየተከናወኑ ከሚገኙ የግንባታ ሥራዎች መካከል የ87 በመቶ የፍሳሽ ማስወገጃ፣ የ99 በመቶ የአፈር ቆረጣ እና ሙሌት፣ የ7 ኪሎሜትር ሰብቤዝ፣ የ6 ኪሎሜትር ቤዝኮርስ እና የ5 ኪሎሜትር አስፋልት ሥራዎች ተከናውነዋል። በተጨማሪም የአንድ ድልድይ ግንባታ ሙሉ በሙሉ ተጠናቅቋል።
ግንባታው በታቀደለት ጊዜ እንዲጠናቀቅም በኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር በኩል አስፈላጊው ድጋፍ እና ጥብቅ ክትትል እየተደረገ ይገኛል።
መንግስታዊው የልማት ድርጅት የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ሥራዎች ኮርፖሬሽን ግንባታውን ያከናውናል። ቤስት ኮንሰልቲንግ ኢንጅነርስ ፕሮጀክቱን የመቆጣጠር እና የማማከር ሥራ ይሠራል። የግንባታው ወጪ ሙሉ በሙሉ በፌደራል መንግስት ይሸፈናል።
በተጨማሪ
› አጭር መልዕክት 8561
› ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770
› ድህረገጽ www.era.gov.et
› ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et
› ቴሌግራም https://t.me/ethioroads
› ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd
› ኢሜል [email protected]
› ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።
@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna
#ኢትዮጵያ
Last updated 2 months, 3 weeks ago
Last updated 2 months, 2 weeks ago
ይህ ስለ Manchester United መረጃዎችን የሚያገኙበት የ Telegram ቻናል ነው 🇪🇹
--------------------------------------------------------------
☞︎| ስለ ማንቸስተር ዩናይትድ ትኩስ መረጃዎች
☞| ቀጥታ ስርጭቶች ከየስታድየሞቹ
☞| የዝውውር ዜናዎች
☞| ስለ ማንችስተር ዩናይትድ ታሪኮች
📩 ለማስታወቂያ ስራ DM :- @Marcoabdu
Last updated 1 month, 1 week ago