አንኳር መረጃ- ETH

Description
ለጥቆማ እና ማስታወቂያ ለማሰራት
👇👇👇👇
@Melkka_promo

አንኳር መረጃ
በዚህ ቻናል ለኢትዮጵያ ፍቅር ሰላም አንድነት ስለ ፍትህ የምናወራበት ድምፅ ላጡ ድምፅ የምንሆንበት ቻናል ነው።

''We testify about the Truth ''
We recommend to visit

ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ

Last updated 2 months, 3 weeks ago

Last updated 2 months, 2 weeks ago

ይህ ስለ Manchester United መረጃዎችን የሚያገኙበት የ Telegram ቻናል ነው 🇪🇹
--------------------------------------------------------------
☞︎| ስለ ማንቸስተር ዩናይትድ ትኩስ መረጃዎች
☞| ቀጥታ ስርጭቶች ከየስታድየሞቹ
☞| የዝውውር ዜናዎች
☞| ስለ ማንችስተር ዩናይትድ ታሪኮች

📩 ለማስታወቂያ ስራ DM :- @Marcoabdu

Last updated 1 month, 1 week ago

2 weeks, 5 days ago
መረጃ***‼️***

መረጃ‼️

አስገዳጅ የባንኮች ውህደት እንደሚኖር ብሄራዊ ባንክ ገለፀ

አስገዳጅ የባንኮች ውህደት እንደሚኖር የኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክ ገዥ ማሞ እስመለአለም ምህረቱ ገልፀዋል ፡፡

እንደ ገዥው ገለፃ የውህደቱ ዋነኛ አላማ ችግር ያለባቸውን ባንኮች ለማዳን ነው ብለዋል።

በቅርቡ የፀደቀው የባንክ ስራ አዋጅ የባንኮችን ውህደት በተመለከተ የገለፀ ሲሆን ዝርዝር የአፈፃፀም መመሪያ እየተጠበቀ ነው።

ብሄርን መሰረት አድርገው ስለተመሰረቱ ባንኮች በውህደት ወቅት ስለ ሚያጋጥም ተግዳሮት የተጠየቁት አቶ ማሞ ውህደትን ጨምሮ አጠቃላይ የባንክ ስራ በህግ እንደሚመራ አስታውሰው፣ "ከዚህ አኳያ ከብሄር ጋር ተያይዞ የሚነሳው ጉዳይ በተለይ በአስገዳጅነት የሚፈፀም ውህደት ላይ የሚኖረው ተፅእኖ አናሳ ነው፣" ብለዋል።
@Ankuar_mereja
@Ankuar_mereja

2 weeks, 6 days ago
የዓለማችን የበረዶ ግግር በከፍተኛ ፍጥነት እየቀለጠ …

የዓለማችን የበረዶ ግግር በከፍተኛ ፍጥነት እየቀለጠ ነው ዓለም ላይ ያለው የበረዶ ግግር እጅግ በከፍተኛ ፍጥነት እየቀለጠ መሆኑን ተመራማሪዎች አስታወቁ።

በሰው ልጆች በሚፈጠረው የዓየር ንብረት ለውጥ ምክንያት በተለይም በተራሮችእና በሁለቱ ንፍቀ ክበቦች ያለው የበረዶ ግግር እና የበረዶ ንጣፍ አስደንጋጭ በሚባል ፍጥነት እየቀነሰ እና የውሃማ አካላት ከፍታ
እየጨመረ መሆኑን ነው ዓለም አቀፉ የበረዶ ግግር ክትትል አገልግሎት ያወጣው የጥናት ሪፖርት ያመላከተው።

ባለፉት 20 ዓመታት በከፍተኛ መጠን እየቀለጠ ሲሆን፥ ይህም እስከዛሬ ከታዩትአስደንጋጩና ከፍተኛው ነው ተብሏል። @Ankuar_mereja @Ankuar_mereja

2 weeks, 6 days ago
መረጃ ***‼️***

መረጃ ‼️

ታዋቂው የኦሮሞ ባለሃብት ድንቁ ደያስ ከሃገር እንዳይወጡ መከልከላቸዉ ተሰማ

ባለሃብቱ ከሃገር ለመዉጣት ቦሌ ኤርፖርት ቢደርሱም በደህንነቶች ከሃገር  መዉጣት እንደማይችሉ ተነግሮቸዉ ወደ ቤት መመለሳቸዉ ተሰምቷል

ደህንነቶቹም ለባለሀብቱ ኤርፖር መመለስ ያቀረቡት ምክንያት የኦሮሚያ ክልል ፕሬዝዳንት ሺመልስ አብዲሳ ትእዛዝ መሆኑ ተነስቷል ፡፡

ከዚህ በፊት ባለሃብቱ ድንቁ ደያስ ሶደሬን ጨምሮ በኦሮሚያ እና በአዲስ አበባ ያሎቸዉ ህንፃዎች በመንግስት እንደተወረሱባቸዉ ይታወሳል ፡፡

@Ankuar_mereja
@Ankuar_mereja

2 months, 4 weeks ago
**ጋዛ የቀሩት የመጨረሻው ፍልስጤማዊ የአጥንት ቀዶ …

ጋዛ የቀሩት የመጨረሻው ፍልስጤማዊ የአጥንት ቀዶ ጥገና ሐኪም ተገደሉ

በሰሜን ጋዛ የቀሩት የመጨረሻው ፍልስጤማዊ የአጥንት ቀዶ ጥገና ሐኪም በእስራኤል ታንክ ጥቃት መገደላቸውን የፍልስጤም ባለስልጣናት ገለጹ።

ዶክተር ሰይድ ጁዴህ ሕይወታቸው የተቀጠፈው ሐሙስ፣ ታህሳስ 3/ 2017 ዓ.ም. ወደ ስራ እየሄዱ በነበረበት ወቅት በተፈጸመባቸው ጥቃት ነው።

ዶክተሩ በሰሜን ጋዛ ውስጥ በሚገኙት ካማል አድዋን እና አል አውዳ ሆስፒታሎች በአጥንት ቀዶ ጥገና ሐኪምነት ያገለግሉ ነበር። የእስራኤል ጦር ስለ ግድያው አላውቅም የሚል ምላሽ ሰጥቶ ነገር ግን እየመረመርኩ ነው ብሏል።

@Ankuar_mereja
@Ankuar_mereja

2 months, 4 weeks ago
አስገራሚ ***‼️***

አስገራሚ ‼️

የባስ አታምጣ! "እዚህ ጋር ደግሞ ሌላ ትኩሳት" አለ ድምፃዊ ቴዲ አፍሮ "ብቻ ጌታ ዓለማችንን ሰላም ያድርግልን እንጂ ነገሩ ሁሉ ከባድ ነው።

ጋናዊ ፓስተር ራሱን መልዓክ ነኝ ብሎ ሰይሟል ። እኔን አዝላችሁ እንድትወስዱ ጌታ አዟል በማለት ምዕመናኖቹን ጀርባ ላይ እንደ ህጻን ታዝሎ ወደ አምልኮ ስፍራው ይሄዳል።

ምዕመናኑም በረከት ለማግኘት በሚል ተሽቀዳድመው በነቢያቸው ይጋለባሉ ነቢያቸውን አዝለው ወደ ቸርች የሚገቡ ምዕመናንም በልዩ ሁኔታ በጭብጨባ አቀባበል ይደረግላቸዋል።
ማሕበራዊ ሚዲያ የማያሳየን የለም።"

Via Befekadu Abay

@Ankuar_mereja
@Ankuar_mereja

2 months, 4 weeks ago

ሐርጌሳ****

አዲሱ የሶማሌላንድ ፕሬዝዳንት አብዲራህማን ሞሐመድ አብዱላሂ ስድስተኛው የራስ ገዟ ፕሬዝዳንት ኾነው ዛሬ በይፋ ሥልጣናቸውን ተረክበዋል።

ኢትዮጵያ እና ሱማሊያ የባሕር በር ዙሪያ ከስምምነት በደረሱ ማግስት ሥልጣናቸውን የተረከቡት ፕሬዝዳንት አብዱላሂ፣ ሶማሌላንድ የአገርነት እውቅና እንድታገኝ ጥረት ማድረጋቸውን እንደሚቀጥሉ አረጋግጠዋል።

ሶማሌላንድ ከኢትዮጵያ ጋር ባለፈው ዓመት የተፈራረመችው የባሕር በር የመግባቢያ ስምምነት ዕጣ ፋንታው ምን እንደሚኾን ለጊዜው አልታወቀም።

ፕሬዝዳንቱ፣ በምሥራቃዊ ሶማሌላንድ የፑንትላንድ ራስ ገዝ አዋሳኝ በኾነው ሱል አውራጃ ለተከሰተው ግጭት ያለ ምንም ቅድመ ኹኔታ ሰላማዊና ዲፕሎማሲያዊ መፍትሄ እንደሚፈልጉም ቃል ገብተዋል።

በሶማሌላንድ ወታደሮችና ባካባቢው የጎሳ ታጣቂዎች መካከል ለወራት የዘለቀ ውጊያ ከተካሄደ በኋላ፣ የአካባቢው የጎሳ መሪውዎች ራሱን የቻለ የፌደራል ግዛት በመመስረት ከሱማሊያ ጋር ለመቀላቀል መወሰናቸው አይዘነጋም።

በፕሬዝዳንቱ በዓለ ሲመት ላይ፣ የሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ሙስጠፌ ሞሐመድ የኢትዮጵያ መንግሥትን ወክለው ተገኝተዋል።

@Ankuar_mereja

3 months ago

የታጠቁ የባሕር ላይ ወንበዴዎች በሱማሊያ የባሕር ጠረፍ አካባቢ አንዲት የቻይና አሳ አጥማጅ መርከብ ከሐሙስ ጀምሮ እንዳገቱ መኾኑን ዓለማቀፍ የዜና ምንጮች ዘግበዋል።

የባሕር ላይ ወንበዴዎቹ መርከቧን ያገቱት፣ በፑንትላንድ ግዛት የባሕር ጠረፍ አቅራቢያ እንደኾነ ዘገባዎቹ አመልክተዋል።

በመርከቧ ውስጥ ኹለት ጠባቂዎችን ጨምሮ 18 ሠራተኞች እንዳሉ መረጋገጡንና እስካኹን በመርከቧ ሠራተኞች ላይ የደረሰ ጉዳት እንደሌለ ዘገባዎቹ ጠቅሰዋል።

መርከቧን ለማስለቀቅ እየተደረገ ያለ ጥረት ስለመኖሩ ግን የተሰማ ነገር የለም።

@Ankuar_mereja
@Ankuar_mereja

3 months ago

24 አካባቢ የተነሳዉን የእሳት አደጋ ለመቆጣጠር የእሳት አደጋ ሰራተኞች እየተረባረቡ ይገኛል ፡፡

እሳቱ አሁን እየቀነሰ ነዉ

#አንኳር_መረጃ  

@Ankuar_mereja
@Ankuar_mereja

3 months ago

አዲስአበባ አሁን ከመሸ ከባድ የእሳት አደጋ ተከስቶል ??

#አንኳር_መረጃ  

@Ankuar_mereja
@Ankuar_mereja

3 months, 1 week ago
መረጃ ***‼️***

መረጃ ‼️

ከ2004 በሆላ  የተገነቡ መንግሥት ህገወጥ ያላቸው ቤቶች ሊወረሱ መሆኑ ተሰምቶል፡፡

የከተማ መሬትን በሊዝ መያዝ በሚል በቀረበ ረቂቅ አዋጅ ላይ ምክርቤቱ እየተዋያየ ባለበት ሰአት የከተማ እና መሰረተ ልማት ሚኒስቴር የመሬት ማኔጅመንት  ዴስክ ሃላፊ ገብሩ ባየብኝ ናቸዉ ከ2004 በሆላ  ጀምሮ የተገነቡ  ህገወጥ ያሎቸውን ቤቶች መንግስት ሊወረስ መሆኑን የተናገሩት ፡፡

#አንኳር_መረጃ  

@Ankuar_mereja
@Ankuar_mereja

We recommend to visit

ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ

Last updated 2 months, 3 weeks ago

Last updated 2 months, 2 weeks ago

ይህ ስለ Manchester United መረጃዎችን የሚያገኙበት የ Telegram ቻናል ነው 🇪🇹
--------------------------------------------------------------
☞︎| ስለ ማንቸስተር ዩናይትድ ትኩስ መረጃዎች
☞| ቀጥታ ስርጭቶች ከየስታድየሞቹ
☞| የዝውውር ዜናዎች
☞| ስለ ማንችስተር ዩናይትድ ታሪኮች

📩 ለማስታወቂያ ስራ DM :- @Marcoabdu

Last updated 1 month, 1 week ago