Ethio Anti Corona

Description
?Ethio Anti Corona ?

#EAC

ወዳጅ ዘመድዎን ወደዚህ ቻነል እንዲቀላቀሉ ያድርጉ!

ስለ ኮሮና ቫይረስ ግንዛቤ ማስጨበጫ ፣ መከላከያ መንገዶች እና መረጃዎች የሚቀርቡበት ቻነል!

#COVID19
#Ethiopia

@EthioAntiCorona
Advertising
We recommend to visit

ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ

Last updated 3 weeks, 4 days ago

ለማንኛውም አስተያየት እና ጥቆማ ? @Esat_tv_comment_bot

??ኢሳት የኢትዮጵያ አይን እና ጆሮ??

Last updated 1 month, 1 week ago

Last updated 2 months, 1 week ago

4 years, 4 months ago

በኢትዮጵያ ተጨማሪ 150 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋግጧል!

ባለፉት 24 ሰዓት በተደረገው 5,141 የላብራቶሪ ምርመራ አንድ መቶ ሃምሳ (150) ሰዎች የኮሮና ቫይረስ ተገኝቶባቸዋል፡፡ በአጠቃላይ በሀገራችን ቫይረሱ በምርመራ የተገኘባቸው ሰዎች ቁጥር 1,636 ደርሷል፡፡

ቫይረሱ የተገኘባቸው 94 ወንድ እና 56 ሴት ሲሆኑ የዕድሜ ክልላቸው ከ3 እስከ 72 ዓመት ውስጥ ይገኛል። በዜግነት 147 ኢትዮጵያውያን ሲሆኑ ሶስቱ (3) የውጭ ዜጎች ናቸው።

ቫይረሱ የተገኘባቸው 123 ሰዎች ከአዲስ አበባ፣ 1 ሰው ከአፋር ክልል፣ 2 ሰዎች ከትግራይ ክልል፣ 3 ሰዎች ከደቡብ ክልል፣ 2 ሰዎች ከኦሮሚያ ክልል፣ 13 ሰዎች ከአማራ ክልል እና 6 ሰዎች ከሶማሌ ክልል ናቸው።

ተጨማሪ መረጃ ፦

በትላንትናው አራት (4) ሰዎች ከአዲስ አበባ ከበሽታው ያገገሙ ሲሆን በአጠቃላይ በሀገራችን ከበሽታው ያገገሙ ሰዎች 250 ደርሰዋል።

4 years, 4 months ago

በአዲስ አበባ ከተማ በኮሮና ቫይረስ (ኮቪድ-19) መያዛቸው የተረጋገጠ 458 ሰዎች ክፍለ ከተማ እንደሚከተለው ቀርቧል ፦

• ልደታ - 122 ሰዎች
• አዲስ ከተማ - 79 ሰዎች
• ቦሌ - 56 ሰዎች
• ጉለሌ - 40 ሰዎች
• ኮልፌ ቀራኒዮ - 40 ሰዎች
• ንፋስ ስልክ ላፍቶ - 27 ሰዎች
• የካ - 26 ሰዎች
• አራዳ - 21 ሰዎች
• ቂርቆስ - 16 ሰዎች
• አቃቂ ቃሊት - 10 ሰዎች
* አድራሻቸው በመጣራት ላይ ያለ - 21 ሰዎች

4 years, 5 months ago

በኢትዮጵያ 25 ተጨማሪ ሰዎች የኮሮና ቫይረስ ተገኘባቸው!

19የሚሆኑት ከበሽተኛ ሰው ጋር ምንም ንክኪ እና የውጪ ጉዞም ያልነበራቸው ናቸው!

የቁጥሩ መጨመር በጣም አስደንጋጭ እየሆነ ነው!

አላህ ይሁነን!!

4 years, 5 months ago

17ተጨማሪ ሰዎች የኮሮና ቫይረስ ተገኘባቸው!

7ቱ ከጅቡቲ የተመለሱ፣6ቱ ከሶማሊያ የተመለሱ እና 4ቱ ደግሞ ከአዲስ አበባ ናቸው::

ከበሽታው ያገገሙ ሰዎች ቁጥር 93 ደርሷል::

4 years, 5 months ago
Ethio Anti Corona
4 years, 5 months ago
Report #46

Report #46
የኢትዮጵያ የኮሮና ቫይረስ ሁኔታ መግለጫ
Status update on
# COVID19Ethiopia

እርማት:- ከታች በተገለጸው መግለጫ ላይ 4 አመት እድሜ ተብሎ የተገለጸው 42 አመት በሚል ማስተከከያ እንዲደረግበት ከይቅርታ ጋር እንጠይቃለን።

4 years, 6 months ago
Ministry Of Health,Ethiopia\

Ministry Of Health,Ethiopia\
የኢትዮጲያ ጤና ሚኒስቴር

Report #38

የኮሮና ቫይረስ ( # ኮቪድ -19) ወቅታዊ ሁኔታ

4 years, 6 months ago

ብረት ነክ እቃዎችን ከነኩ እጆትን ይታጠቡ !
ማንኛውም ብረት ነክ ዕቃዎችን ከነካን ቢያንስ ለ 40 ሰከንድ እጃችንን በሳሙና እና በውሃ መታጠብ ያስፈልጋል።

የጤና ጥበቃ ሚኒስትር

4 years, 6 months ago
ቻይና የህክምና ባሉሙያዎችን ወደ ኢትዮጵያ ልትልክ …

ቻይና የህክምና ባሉሙያዎችን ወደ ኢትዮጵያ ልትልክ ነው

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 7፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ኢትዮጵያ የኮሮና ቫይረስ ለመከላከል የምታደርገው ጥረት የሚደግፉ የህክምና ባለሙያዎችን ቻይና ወደ ኢትዮጵያ ልትልክ ነው።

ቻይና ከኢትዮጵያ በተጨማሪም የህክምና ባለሙያዎችን ወደ ቡርኪና ፋሶ እንደምትልክ ነው የተገለፀው።

እነዚህ የህክምና ባለሙያዎች ልምዳቸውን ያጋራሉ እንዲሁም የኮሮና ቫይረስን ለመቆጣጠርና ለመከላከል የሚያስችሉ መመሪያዎችን እና ቴክኒካል ምክሮችን ለጤና ባለሙያዎች እና ለህክምና ተቋማት ያካፍላሉ ተብሏል።

ቻይና ከአፍሪካ ጋር ጠንካራ ግንኙነት እንዳላት የገለፁት የሀገሪቱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ዝሆ ሊጂዓን በአፍሪካ ቫይረሱን ለመከላከል እና ለመቆጣጠር እየተከናወነ ያለውን ስራ ሀገራቸው እንደምትደግፍ ገልፀዋል።

በአፍሪካ ሀገራት ያለውን ሁኔታ በትኩረት እየተከታተለች መሆኑን ያስታወቀችው ቻይና ቫይረሱን ለመቆጣጠርና ለመከላከል የሚያስችሉ መሳሪያዎችን ማቅረቧን ሲ ጂ ቲ ኤን ዘግቧል።

4 years, 6 months ago
ሙቀት ሲለኩ ተገቢውን ርቀት ይጠብቁ!

ሙቀት ሲለኩ ተገቢውን ርቀት ይጠብቁ!

ከ 3 እስከ 5 ሴንቲ ሜትር ይራቁ!

We recommend to visit

ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ

Last updated 3 weeks, 4 days ago

ለማንኛውም አስተያየት እና ጥቆማ ? @Esat_tv_comment_bot

??ኢሳት የኢትዮጵያ አይን እና ጆሮ??

Last updated 1 month, 1 week ago

Last updated 2 months, 1 week ago