Ethio 251 Media

Description
ETHIO 251 is an independent media offering you News, Political Analysis and Information feeds. መረጃ ለማድረስ :- @Ethio251MediaInfo
Advertising
We recommend to visit

ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ

Last updated 1 month ago

ለማንኛውም አስተያየት እና ጥቆማ ? @Esat_tv_comment_bot

??ኢሳት የኢትዮጵያ አይን እና ጆሮ??

Last updated 1 month, 2 weeks ago

Last updated 2 months, 2 weeks ago

1 month ago
“ዘመቻ ሰማኝ አማረ” በወሎ

“ዘመቻ ሰማኝ አማረ” በወሎ

የአማራ ፋኖ በወሎ በትግል ወቅት በተሰዋው በእሸት ክፍለጦር ዋና አዛዥ ሻለቃ ሰማኝ አማረ ስም ዘመቻ አስጀመረ!

የአማራ ፋኖ በወሎ አሳመነዉ ኮር እሸት ክፍለ ጦር ዋና አዛዥ ሻለቃ  ሰማኝ አማረ  ከጠላት ጋር አንገት ላንገት ተናንቆ ብዙ ባንዳዎችን እስከወዲያኛው ሸኝቶ በጀግንነት መሰዋቱን ኮሩ አሳውቋል፡፡

ኮሩ የአዛዡን መሰዋት ተከትሎ ባወጣው መግለጫ “የአማራ ህዝብ የህልዉና ትግል አብሪ ኮከብ እና የትግላችን  ማርሽ ቀያሪዉ ወደ ኋላ ማለት አማይወደዉ  ሻለቃ  ሰማኝ አማረ  በሰሜን ወሎ ላስታ ወረዳ ግራኝ አምባ ዉስጥ  የጀግንነት ስራ ሰርቶ አርፏል፤ አደራውንም እንወጣለን” ብሏል፡፡

ሻለቃ ሰማኝ አማረን በማጣታችን መሪር ሀዘን ተሰምቶናል ሲልም ገልጿል:: ይህ  የኮራችን ኃይል ከዚህ በፊት በሻለቃ ሰማኝ አማረ አዛዥነት  የቆላዉን  ምድር ማለትም ገለሶት፣ እርፋ፣ ግራኝ አምባ፣ ዳቦ ከተማ፣ ድብኮን እና ሌሎች አካባቢወችን ሸፍኖ በማንቃት፣ በማደራጀት፣ በማስታጠቅና በመታገል ሲንቀሳቀስ የቆየ ኃይል ሲሆን ከክላሽ የነብስ ወከፍ መሳሪያ እስከ  ከባድ መሳሪያ በመታጠቅ እና በሰው ኃይል ብዛትም የተቀመጠውን መስፈርት አሟልቶ በመገኘቱ መስከረም 2 ቀን 2017  በጀግናዉ እና የትግሉ ማርሽ ቀያሪዉ ሻለቃ ሰማኝ አማረ አዛዥነት "እሸት  ክፍለጦር" ተብሎ በመሰየም ዕዉቅና እንደተሰጠው አስታውሷል።

ይሁን እንጂ ሻለቃ ሰማኝም  ክፍለጦርን መስርቶ መስከረም 11/2017 ዓ.ም  ከጠላት ጋር አንገት ላንገት ተናንቆ በጀግንነት መሰዋትነትን ተቀብሏል። በህልዉና ትግሉ ከ 17 በላይ አዉደ ወጊያወችን በመሪነት ያካሂደ ሲሆን በነዚህ አወደ ዉጊያወች ላይ  በጠላት ላይ ቁሳዊ እና አካላዊ ቀዉስ አድርሷል።

ታጋይ ይሰዋል ትግል ይቀጥላል ያለው ኮሩ በትግሉ ብዙ ጀግኖችን እየገበርን ብዙ ጀግኖች እየተተኩ በድል ዋዜማ ላይ እንገኛለን ብሏል፡፡

“በመሆኑም ሻለቃ ሰማኝ አማረ  ለከፈለው ዉድ ዋጋ የአማራ ፋኖ በወሎ በሚንቀሳቀስበት በሁሉም  ቀጠና ከትናንት መስከረም 12/2017 አ.ም ጀምሮ "ዘመቻ ሻለቃ ሰማኝ አማረ" አውጀናል” ሲል አሳውቋል::

“መላው ሰራዊታችን ብሎም ህዝባችን በጀግናው መሪያችን የተሰየመው ዘመቻ በድል የታጀበ እንዲሆን የተለመደዉ ተጋድሎ ተጠናክሮ እንዲቀጥል” ሲል ጥሪ አስተላልፏል፡፡

ኢትዮ 251 ሚዲያ
የነጻነት አንደበት!

https://t.me/ethio251media

1 month ago
Ethio 251 Media
1 month ago

የላስታው ያልተጠበቀ ጥቃት

በላስታ ቀጠና በፋኖ በተፈጸመ የደፈጣ ጥቃት በርካታ የአገዛዙ ወታደሮች ተገደሉ
በወሎ ላስታ ቀጠና ልዩ ስሙ ድብኮ አከባቢ በተፈፀመ የደፈጣ ጥቃት አንድ የሻለቃ እና ሦስት የሻምበል አዛዦችን ጨምሮ በርካታ የገዢው ቡድን ወታደሮች መገደላቸው ታውቋል፡፡

የደፈጣ ጥቃት የተፈፀመበት ይህ የአገዛዙ ኃይል ከሰሞኑ ወደ አማራ ክልል የገባ መሆኑም ነው የተነገረው።
ከሌሎች የሃገሪቱ ክፍል ተወጣጥቶ ወደ አማራ ክልል ላስታ ላሊበላ ቀጠና እየገባ የነበረው አዲስ የገዢው ቡድን ወታደር ላይ ትናንት መስከረም 11/2017 ዓ/ም አመሻሹን በተፈፀመ የደፈጣ ጥቃት አንድ የሻለቃ እና ሦስት የሻምበል አዛዦችን ጨምሮ በርካታ ወታደሮች መገደላቸውን መረብ ሚዲያ ጥቃቱ በተፈፀመበት አከባቢ የነበሩ የአይን እማኞችንና የፋኖ አባላቱን አነጋግሬ አረጋግጫለሁ ብሏል፡፡

የደፈጣ ጥቃቱ የተፈፀመው በጋሼና እና በላሊበላ ከተማ መካከል በሚገኙ ልዩ ስማቸው ድብኮ እና ግራኝ አምባ በተባሉ አከባቢዎች ላይ ሲሆን፡ በዚህም በገዢው ቡድን ኃይል ላይ ከባድ የሆነ የሰብአዊና ቁሳዊ ውድመት መድረሱን አማራ ፋኖ በወሎ የአሳምነው ኮር ቃል አቀባይ ፋኖ ሞገስ አባራው ገልጿል፡፡

በዚህ ጥቃት አንድ የሻለቃ አዛዥ እና ሦስት የሻምበል አዛዦችን ጨምሮ ቁጥራቸው በውል ያልታወቀ በርካታ ወታደሮች ሙትና ቁስለኛ ሲሆኑ፡ 12 የነፍስ ወከፍ ክላሽንኮቭ መሣሪያና ሦስት መገናኛ ራዲዮን በፋኖ እጅ መግባቱን ነው የኮሩ ቃል አቀባይ የገለፀው።

"የደፈጣ ጥቃቱ የተፈፀመባቸው የአገዛዙ ወታደሮች ከሰሞኑ ነው ወደ አማራ ክልል የገቡት፡ የመጀመሪያውን ጥቃት አድርሰንባቸዋል" ያለው የኮሩ ቃል አቀባይ ፋኖ ሞገስ አባራው፡ "ገዢው ቡድን እያስገባው ያለው ኃይል ካለን የተዋጊ ኃይል ብዛት አንፃር ያሉብንን አንዳንድ የትጥቅ ጉድለቶችን ያሟላልናል" ሲል ተናግሯል።

ዘገባው የመረብ ሚዲያ ነው!

3 months, 3 weeks ago

ልዩ መረጃ!

ፋሽስቱ ዐቢይ አሕመድ በነገው ዕለት የአሻንጉሊቶች ስብስብ በሆነው ፓርላማ ቀርቦ ሲዘጋጅበት የከረመውን ሴራ፣ ከፋፋይና መርዛማ ንግግሩን ያሰማል።

የኢትዮ 251 ሚዲያ ምንጮች ያደረሱን መረጃ ጋዜጠኛ ሙሉጌታ አንበርብር እንደሚከተለው ያቀርበዋል፦

©ኢትዮ 251 ሚዲያ
   የነጻነት አንደበት! 

Merja tv : Eutelsat 8 West B Freq: 11.636 Vertical. SR: 27.500 FEC: 5/6
Telegram: https://t.me/ethio251media
Twitter : https://x.com/251media?s=21
Rumble : https://rumble.com/user/ETHIO251MEDIA
Facebook: https://www.facebook.com/ETHIO251?mibextid=LQQJ4d
Website: https://www.ethio251media.org
Gofund.me : https://gofund.me/a2d99937

3 months, 3 weeks ago
አማራን ተቋም አልባ የማስቀረት ግዙፍ ሴራዎች …

አማራን ተቋም አልባ የማስቀረት ግዙፍ ሴራዎች በነ ዐቢይ አሕመድ…

በሕክምና ትምህርት ዘርፍ ከ65 ዓመት በላይ ልምድ ያለው 'የጎንደር ዩንቨርስቲ'ን የማፍረስ እና ልምድ ያላቸውን መምህራንን እና ዶክተሮች ወደ ጅማ የማዘዋወር የነ ዐቢይ አሕመድ ድብቅ ፕሮጀክት በሰፊው እየተሰራበት ነው።

የጎንደር ዩኒቨርሲቲ በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዘመነ መንግሥት የተመሰረተና በህክምናው ዘርፍ ከአዲስ አበባው (ጥቁር አንበሳ) ዩኒቨርሲቲ በመቀጠል በምስራቅ አፍሪካ ደረጃ አንጋፋው የህክምና ተቋም ነው።

በህክምናው ዘርፍ ብቻ በመቶ ሺህዎች የሚቆጠሩ ባለሙያዎችንም አፍርቷል።
ይህን አንጋፋ የአፍሪካ ሀብት የሆነ ተቋም በግብዓትና በሰው ኃይል ለማፍረስ ጅማ ዩኒቨርሲቲን ለማንገሥ በጥናት ላይ የተመሠረተ ሴራ እየተሰራበት ነው።

(መረጃው ከጎንደር ዩንቨርስቲ ሰዎች የተላከልን ነው)

በኦሕዴድ በኩል፦ "ጅማን የ ሜዲካል ቱሪዝም ማዕከል እናደርጋለን" በሚል የጎንደር ዩንቨርስቲን ማፍረስ እንደ ግብ ማስፈፀሚያ መሳሪያ ሆኗል።

ይህ አማራን የተቋማት መዃን የማድረግ የኦህዴድ ፕሮጀክት፣ ከጥልቅ ጥላቻ እና አማራ ጠልነት የሚመነጭ ነው።

የጎንደር ዩንቨርስቲ በወልቃይት ጉዳይ በሰራቸው ወገን ተኮር (አማራዊ) ተግባራት በሁለቱም ኃይሎች ማለትም በወያኔም፣ በኦሕዴድም ጥርስ ውስጥ የገባ ተቋም ነው።

ለዚህ አንጋፋ የትምህርት ተቋም ካለፉት ሦስት ዓመታት ወዲህ ምንም ዓይነት አዳዲስ የሕክምና ግብዓት አልተሰጠውም፤ ተቋሙም በበጀት እየታሸ ይገኛል።

በአንፃሩ ጅማ ዩንቨርስቲ ራሱን እንዲያደራጅ የማድረግ እንቅስቃሴ በከፍተኛ ሁኔታ ኢንቨስት እየተደረገበት ነው።

የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ውስጥ ሚሰሩ ከፍተኛ ልምድና ዕውቀት ያላቸው የሕክምና ሳይንስ መምህራንና ተመራማሪዎችን በከፍተኛ ጥቅማ ጥቅም በማማለል እንዲፈልሱ የማድረግ ሥራው በትልቅ በጀት እየተሰራበት ነው።

በአንፃሩ የጎንደር ዩኒቨርሲቲ በግብዓትና በበጀት እጦት እንዲሽመደመድ በመደረግ ላይ ነው።
ይህም አማራን በሰው ኃይልና በተቋማት የማራቆት ኦነጋዊ ፕሮጀክት ነው።
በሌላ ተመሳሳይ የሕክምና ነክ መረጃ ፦

በአሁኑ ወቅት በአማራ ክልል እና በአዲስ አበባ አዲስ ፋርማሲ መክፈት አይቻልም። ፍቃድ ተከልክሏል።

በአማራ ክልል ከመካከለኛ ክሊኒክ ጀምሮ መክፈት አይቻልም። ምክንያት ያሉት ደሞ አዲስ ስታንዳርድ እያወጣን ስለሆነ የሚል 'ታገሱን' የሚል ምላሽ ተሰጥቷል።

በሌላ በኩል በኦሮሞ ክልል የፋርማሲ ፍቃድ ያወጡ ሰዎች አዲስ አበባ ላይ መስራት የሚችሉበት ያልተፃፈ ሕግ ተግባራዊ በመሆን ላይ ነው።

በሌላ መረጃ ደብረ ማርቆስ ዩንቨርሲቲ ሕክምና ክፍሉን የመዝጋት እንቅስቃሴ በሚቀጥለው በጀት ዓመት ይኖራል። ለዚህም እንዲረዳ አቅጣጫ እንዲያስቀምጡ የኦህዴድ ፖለቲካ አስፈፃሚ ሆዳም አማሮች በምሁር ሥም ተሰብስበዋል።

እነዚህን መረጃዎች በሙሉ ደምረን ስንመለከታቸው አማራን በሰው ኃይልና በተቋማት የማዳከም፤ የማራቆት ብሎም የተቋም መኻን የማድረግ ኦነጋዊ ፕሮጀክቶች ናቸው።

ይህ ደግሞ ከጥልቅ ጥላቻና አማራ-ጠልነት የሚመነጭ ነው።
~
ለውስጥ መረጃ ምንጮቻችን በኢትዮ 251 አድማጭ ተመልካቾች ሥም ከልብ እናመሰግናለን!!

ኢትዮ 251 ሚዲያ
የነጻነት አንደበት!

Merja tv : Eutelsat 8 West B Freq: 11.636 Vertical. SR: 27.500 FEC: 5/6
Telegram: https://t.me/ethio251media
Twitter : https://x.com/251media?s=21
Rumble : https://rumble.com/user/ETHIO251MEDIA
Facebook: https://facebook.com/ETHIO251?mibextid=LQQJ4d
Website: https://ethio251media.org
http://Gofund.me : https://gofund.me/a2d99937

3 months, 3 weeks ago
ታንኩንም ባንኩንም የጠቀለለው ኦሕዴድ፣ ከሚውጠው በላይ …

ታንኩንም ባንኩንም የጠቀለለው ኦሕዴድ፣ ከሚውጠው በላይ ማላመጡን ቀጥሏል…

ፋሽስቱ ዐቢይ አሕመድ በዛሬው ዕለት ሦስት አገልጋዮቹን በሚኒስትር ደረጃ ሹመት ሰጥቷል። ከሦስቱ ሁለቱ የኦሮሞ ተወላጆች ሲሆኑ፤ አንደኛዋ ተሿሚ ከደቡብ ኢትዮጵያ ነች። የኦነጉ ሰው ቀጀላ መርዳሳ የሹመት ሽግሽግ ተደርጎለት ዐቢይ አሕመድ አማካሪ ብሎ ወስዶታል። ኦነግ ኦነግን ሲያማክር ማለት ነው።

ቀጀላ መርዳሳን የተካችው የደቡብ ተወላጇ ወ/ሮ ሽዊት ሻንካ የባህልና ስፖርት ሚኒስትር ሆና ተሹማለች።

የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚንስትር ሆኖ ሲሰራ የነበረው የወላይታ ተወላጁ አቶ ገብረመስቀል ተነስቶ በምትኩ የኦሕዴዱ ሰው ካሳሁን ጎንፌ ተሹሞበታል።

ካሳሁን ጎንፌ በንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር ውስጥ በሚኒስትር ዴኤታነት የነበረ የኦሕዴድ ሰው ሲሆን፤ አሁን ተቋሙን በሙሉ ኃላፊነት ጠቅልሎታል። ይህ መስርያ ቤት የኢትዮጵያ ኢምፖርት ኤክስፖርት ፍቃድ መስጠትና መንጠቅ የሚከናወንበት በአንድ ጀንበር ቢሊየነር የመሆኛ ቁልፍ ተቋም ነው።

30 ሺህ የኦሮሞ ተወላጅ ቢሊየነሮችን ለመፍጠር ኦሕዴድ ብልጽግና ግብ አስቀምጦ በመስራት ላይ እንዳለ ይታወቃል።

የኦሕዴድ ብልጽግናው ካሳሁን ጎንፌ የንግድና ቀጠናዊ ትስስር መስርያ ቤት በሚኒስቴር ደረጃ እንዲመራ የተሾመው ይህን የኦሕዴድ ግብ ለማሳካት በማሰብ እንደሆነ የደረሱን መረጃዎች ያሳያሉ።

በንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር መስርያቤት የቡና፣ ጫት፣ ቅባት እህሎች ኤክስፖርት ፈቃድ በመስጠት፤ ብድርና የውጭ ምንዛሬ እንዲሰጥ ከፖሊሲ ባንኮች ጋር ቢሮክራሲውን በማቅለል ደረጃ ቁልፍ ሚና ያለው ተቋም ነው።

ኦሕዴድ ብልጽግና የኢትዮጵያ ቁልፍ የኢኮኖሚ፣ ወታደራዊና የደህንነት ተቋማትን በበላይነት ተቆጣጥሮ እንደያዘ ይታወቃል።

የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ኃላፊው ዶ/ር ዩሃንስ አያሌው፣ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ኃላፊ አቤ ሳኖ ሲሆን፤ አሁን ደግም የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስትሩ ካሳሁን ጎንፌ ሆኖ ተሹሟል።

በአጠቃላይ የፖሊሲና የንግድ ባንኮች፣ እንዲሁም የአገሪቱን አጠቃላይ ንግድ የሚመለከተው ግዙፍ መስርያቤት በሙሉ በኦሕዴድ ብልጽግና እጅ ውስጥ ገብቷል።

በነገራችን ላይ የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ግዙፍ የኢትዮጵያን ሀብት የሚንቀሳቅስ የፖሊሲ ባንክ ነው። በውስጡ ትልቅ ሀብት ይዟል።

የተቋሙ የውስጥ ምንጮቻችን ባደረሱን መረጃ መሠረት፦
• የባንኩ አጠቃላይ ሃብት 179 ቢሊዮን ብር
• የባንኩ ካፒታል 39.7 ቢሊዮን ብር ነው።

የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ባለፉት አራት ዓመታት በትልልቅ ፕሮጀክቶች (ፋይናንስ የተደረጉ ፕሮጀክቶች) ብድር የወሰዱ 5,540 ሲሆኑ፤ (ይህ ቁጥር በግዙፍ ፕሮጀክቶች ላይ የተሰጠውን ብድር ብቻ የሚያሳይ ነው) ከእነዚህ 5,540 ሰዎች ውስጥ 87% ከመቶ የኦሮሞ ባለሃብቶች ናቸው ብድር የወሰዱት። በስድስት አመት ውስጥ በዚህን ያህል መጠን ተቋማዊ ምዝበራ የተፈፀመው።

ይህን የሚያስፈፅመው የፖሊሲ ባንኩን እንዲመራ የተመደበው ኦሮሞው ዶ/ር ዩሃንስ ነው።

በአጠቃላይ የፖሊሲና የንግድ ባንኮች፣ እንዲሁም የአገሪቱን አጠቃላይ ንግድ የሚመለከተው ግዙፍ መስርያቤት በሙሉ በኦሕዴድ ብልጽግና እጅ ውስጥ ገብቷል። ታንኩንም ባንኩንም የጠቀለለው ኦሕዴድ ይህ አማራንና ሌላውን የኢትዮጵያ ክፍል በኢኮኖሚ ተንበርካኪ ማኀበረሰብ ለማድረግ ትልቅ አቅም ፈጥሮለት ይታያል።

በአንድ በኩል ጦሩንና ደህንነቱን፤ በሌላ በኩል ደግሞ ንግድና ኢንቨስትመንቱን በበላይነት ተቆጣጥረው በጦርነትም በኢኮኖሚም ማዳከሙን ተያይዞታል።

"የግብርና ዘርፍ ምርታማነት የኢኮኖሚያዊ እድገት መሰረት ነው"
በሚል የሚመፃደቁት እነዚህ ኦነጋዊ ኃይሎች፤ በኢትዮጵያ አቅም የኦሮሞ ኢምፓየር ግንባታ ላይ ናቸው። እናም በመላ ኢትዮጵያዊያን የሕዝብ ትግል መውደቅ አይቀሬ ዕጣ ፈንታቸው ነው።

ለዚህም ትግሉን አጠናክሮ መቀጠል ይገባል!!

©ኢትዮ 251 ሚዲያ
የነጻነት አንደበት!

Merja tv : Eutelsat 8 West B Freq: 11.636 Vertical. SR: 27.500 FEC: 5/6
Telegram: https://t.me/ethio251media
Twitter : https://x.com/251media?s=21
Rumble : https://rumble.com/user/ETHIO251MEDIA
Facebook: https://facebook.com/ETHIO251?mibextid=LQQJ4d
Website: https://ethio251media.org
http://Gofund.me : https://gofund.me/a2d99937

4 months ago
ሰበር ዜና!

ሰበር ዜና!

የአማራ ፋኖ በወሎ የላስታ አሳምነው ክፍለጦር “ዘመቻ አሳምነው ፅጌ” አውጇል፣ ሌሎቹም የፋኖ ዕዞችና ክፍለጦሮች ይሄን ዘመቻውን እንዲቀላቀሉት ጥሪ አቅርቧል።

ድል ለአማራ ፋኖ!

t.me/ethio251media

4 months ago

https://www.youtube.com/live/JWWA6eppVrk?si=zjziliiS0CWvg9gt

YouTube

"የዘመቻ አሳምነው" ጥሪና የአገዛዙ ቅጥፈት | 251 ZARE | 251 AGENDA | ETHIO 251 MEDIA | JUNE 26 2024

Ethio 251 Media
4 months ago

የአማራ ሕዝብ ምን ያክል በአሸናፊነት እየመጣ እንደሆነ አንደኛው ማሳያ በየአደራሹ የታየው ውጤት ነው፤ ብልፅግና ጨርቁን ጥሎ አብዷል።

አብይ አሕመድ የግል ጄኔራሎቹ በየአደራሹ የካድሬ ስራ እንዲሰሩ አሰማርቷቸዋል። ይህን አስመልክቶ ጋዜጠኛ ይርጋ አበበ የሚተነትነውን ዝርዝር አዳምጡት፤

https://t.me/ethio251media

4 months, 1 week ago

https://www.youtube.com/live/y6C7nspemmY?si=s2cVQuVEq3gR-M5F

YouTube

ለኢትዮ 251 የደረሰው ወታደራዊ ሚስጥር እና የፋኖ ተጋድሎ | Ethio 251 Media | 251 Zare | 251 Agenda |

Ethio 251 Media
We recommend to visit

ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ

Last updated 1 month ago

ለማንኛውም አስተያየት እና ጥቆማ ? @Esat_tv_comment_bot

??ኢሳት የኢትዮጵያ አይን እና ጆሮ??

Last updated 1 month, 2 weeks ago

Last updated 2 months, 2 weeks ago