Why Pay for Entertainment? Access Thousands of Free Downloads Now!

ማኅበረ ቅዱሳን ( Mahibere Kidusan)

Description
The channel of mahibere kidusan
Advertising
We recommend to visit

ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ

Last updated hace 1 día, 17 horas

ለማንኛውም አስተያየት እና ጥቆማ 👉 @Esat_tv_comment_bot

🇪🇹ኢሳት የኢትዮጵያ አይን እና ጆሮ🇪🇹

Last updated hace 5 días, 6 horas

Last updated hace 5 días, 19 horas

6 days, 10 hours ago
ማኅበረ ቅዱሳን ( Mahibere Kidusan)
6 days, 10 hours ago
ማኅበረ ቅዱሳን ( Mahibere Kidusan)
6 days, 10 hours ago
ማኅበረ ቅዱሳን ( Mahibere Kidusan)
2 months, 1 week ago
ማኅበረ ቅዱሳን ( Mahibere Kidusan)
2 months, 1 week ago
ማኅበረ ቅዱሳን ( Mahibere Kidusan)
2 months, 1 week ago

ገዳሙ በተደጋጋሚ በታጠቁ ሰዎች ዐይነተ ብዙ ጥቃት እንደሚደርስበት ነገር ግን መፍትሔ እንዳላገኙ በመግለጽ የአሁኑ ጥቃት ግን በቃላት የማይገለጽ ነው ብለዋል።

"ገዳሙን እና እኛን ለማዳን እነሱ ተሰው፤ የእኛንም በደል እነሱ ከፈሉ፤ ጻድቁን አገልግዬ እዚሁ አርፋለሁ ሲሉ ደመ ከልብ ሆነው ዐፈራቸውንም ሳይቀምሱ ቀርተዋል" ሲሉም መረጃ የሰጡን አባቶች በከፍተኛ ሐዘን ገልጸዋል።

4 months, 1 week ago
ማኅበረ ቅዱሳን ( Mahibere Kidusan)
4 months, 2 weeks ago

መልካም አስተዳደር ማለት ምን ማለት ነው?

ዓለም በአሁኑ ጊዜ ትልቅ አጀንዳ ከሚያደርጋቸው ጉዳዮች ዋናው መልካም አስተዳደር ነው፡፡ መልካም አስተዳደር መገለጫው ብዙ ነው፤ እንደ የተቋማቱ ባሕርይ፣ የሥራ ሁኔታ በልዩ ልዩ ሁኔታ ሊገለጽ የሚችል ቢሆንም የጋራ ባሕርያት ይኖሩታል፡፡

ይሁን እንጂ መልካም አስተዳደር ውጤታማነት፣ ጥራት፣ የተገልጋዮችን ነጻነት የሚያከብር፣ አድልዎ የሌለባት፣ የሕግ የበላይነት፣ ተጠያቂነትና ግልጸኝነት፣ ያለው አገልግሎት መስጠትን፣ መልስ ሰጭነትን፣ ኃላፊነት መውሰድን፣ አሳታፊነት፣ ፍትሐዊነትና ስልታዊ የሆነ ርእይ መያዝን የሚያካትት እንደሆነ የዘርፉ ምሁራን ይገልጻሉ፡፡ መልካም አስተዳደር ካለ ሥልጣን ለያዙ ሰዎች ላይ ሕጋዊ ገደብ የሚያስቀጥ እና ሥልጣን በተወሰኑ በተጨማሪም መልካም አስተዳደር ግለሰቦች ሥር እንዳይሆን የሚያደርግ ነው፡፡

መልካም አስተዳደርን ከቤተ ክርስቲያን አኳያ ብፁዕ አቡነ አስጢፋኖስ በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ጽሕፈት ቤት ለሥራ ኃላፊዎች በሐምሌ ፳፻፭ ዓ.ም በተሰጠ ሥልጠና ላይ ተገኝተው እንዲህ ገልጸውት ነበር፡፡

‹‹መልካም አስተዳደር ማለት ከእግዚአብሔር በተሰጠን ሥልጣንና ኃላፊነት የተሟላ መንፈሳዊ አገልግሎት በመስጠት በሁሉም መስክ በጎ አርአያነት ያለው መልካም እረኛ መሆን ነው፡፡›› የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት በድረ ገጹ በለቀቀው አንድ ጽሑፍ ላይ ደግሞ ‹‹መልካም አስተዳደር ማለት በአገልጋይና በተገልጋይ መካከል በመተማመን ላይ የተመሠረተ ግንኙነት መፍጠር›› ማለት እንደሆነ ያትታል፡፡ ጠቅለል ብሎ ሲገለጽ መልካም አስተዳደር የሚባለው ሐሳብ ከውሳኔ አሰጣጥ ሂደትና የተወሰነውን ውሳኔ ከማስፈጸም ጋር የተያያዘ ነው፡፡ ስለሆነም ለተገልጋዮች ፍላጎት ተገቢ ምላሽ የሚሰጥ፣ መብታቸውን የሚያስጠብቅ፣ አገልግሎት የሚያቀርብ እና ሕጎችን ተግባራዊ የሚያደርግ የአስተዳደር ሥርዓት ሁሉ መልካም አስተዳደር ሊባል እንደሚችል መረዳት ይቻላል፡፡

የቤተ ክርስቲያን አስተዳደር የምንለው ምኑን ነው?

በዓለም ያሉ ተቋማት ቢያስተዳድሩ የተወሰነ ጉዳይን ነው፤ የቤተ ክርስቲያን አስተዳደር ግን ሥጋውንም፣ መንፈሳዊውንም ያቀፍ በመሆኑ ለየት ያደርገዋል፡፡ ይህም ከሰው ሀብት አስተዳደር፣ ከፋይናንስ አስተዳደር እና የንብረት አስተዳደር በተጨማሪ መንፈሳዊ አስተምህሮውም ያካተተ በመሆኑ ነው፡፡

ሀ. የሰው ሀብት አስተዳደር

የአንድ ተቋም ህልውናው የሚረጋገጠው ዋናውና የመጀመሪያው የሰው ሀብት አስተዳደሩ ነው፤ ተቋም ውጤታማ ለመሆን በጠንካራ፣ በብቁና በሥነ ምግባሩ ምስጉን የሆነ የሰው ኃይል መዋቀር አለበት፡፡ ቤተ ክርስቲያንም ልዩ ልዩ አገልግሎት የሚሰጡ መነኮሳት፣ ካህናት፣ ዲያቆናት፣ መዘምራንና ሌሎችም በልዩ ልዩ ሙያ የሚያገለግሎ ምእመናንን በርካታ የሰው ኃይል ታስተዳድራለች፡፡ እነዚህ አገልጋዮች ብዙኃኑ ጠንካሮችና በጥብቅ ሥነ ምግባር የሚመሩ፣ የሥጋዊና መንፈሳዊ ዕውቀት ባለቤቶች ስለ ነበሩ ቤተ ክርስቲያኗ በማዕበልና በወጀብ ውስጥ አልፋ ለእኛ ልትደርስ ችላለች፡፡

ለ. የንብረት አስተዳደር

ቤተ ክርስቲያን እጅግ ግዙፍ መንፈሳዊና ሥጋዊ ሀብት ባለቤት ናት፡፡ ቁጥራቸው ከአርባ ሺህ በላይ አድባራትና ገዳማትን፣ በርካታ የመሬት ይዞታዎችን፣ ትምህርት ቤቶችን፣ ኮሌጆችን፣ ልማት ተቋማትን፣ ሕንፃዎችን፣ የጸበል ቦታዎችን እና ተሽከሪካረዎችን የአገልግሎት መስጫዎችን፣ መኪኖችን ከመንበረ ፓትርያሪክ እስከ አጥቢያ ድረስ ታስተዳድራለች፡፡

ሐ. የፋይናንስ አስተዳደር

በገንዘብ አስተዳደር በኩልም በስእለት፣ በዐሥራት በኩራት፣ በልማት፣ በኪራይ፣ በርዳታ፣ በስጦታ፣ በጸበል እና በልዩ ልዩ አገልግሎት ምክንያት የሚሰበሰብ በቢሊዮን የሚቆጠር ገንዘብ ታስተዳድራለች፤ ታንቀሳቅሳለች፡፡

መ. የምእመናን አስተዳደር

መንግሥትም ሕዝብን ቢያስተዳድር በኃይል ታግዞ ነው፡፡ ቤተ ክርስቲያን ግን ከዚህ በተለየ መንገድ ምእመናንን ታስተዳድራለች፡፡ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን አንድ ተቋም እንደሚያደርገው በሥሯ የሚያገለግሉትን ብቻ ሳይሆን ምእመናንን በሥጋዊና በመንፈሳዊ ሕይወታቸው ትልቅ ኃላፊነት ወስዳ በኃይል ሳይሆን በሰላም በጠብ ያይደለ በፍቅር ታሰተዳድራለች፤ ትጠብቃለች፡፡

ሠ. የመንፈሳዊ ሀብት አሰተዳደር

ቤተ ክርስቲያን ሌላም ድርብ አስተዳደራዊ ኃላፊነት አለባት፡፡ እርሱም የማይዳሰሰውንና በቁሳዊ ዋጋ የማይተመነውን መንፈሳዊ ሀብት ማስተዳደር ነው፡፡ ይህም ዜማውን፣ ቅኔውን፣ ሥነ ጥበባዊ ዕውቀቱን፣ ሥነ ጽሑፋዊ ሀብቱ፣ ሥነ ሥዕሉን ሁሉ መንፈሳዊ ዋጋ ያለውን፣ መለያዋ የሆነውን ትጠብቃለች፤ ታስተዳድራለች፡፡ ከምንም በላይ ኦርቶዶክሳዊ አስተምህሮውን፣ ትውፊቱን፣ ዶግማውን ከቀኖና አስተባብራ ትጠብቃለች፤ እንዳይቀሰጥና እንዳይሸራረፍ ታሰተዳድራለች፡፡

የተወዳጆችሁ የእግዚአብሔር ቤተ ሰቦች! ለዛሬ በዚህ አበቃን! ‹‹የመልካም አስተዳደር እጦት በቤተ ክርስቲያን›› በሚል ርእስ ሁለተኛውን ክፍል ይዘንላችሁ እስክንቀርብ ቸር እንሰንብት! አሜን!

4 months, 2 weeks ago

በአጠቃላይ ለድጋፉ ከ 1,500,000 (አንድ ሚሊዮን አምስት መቶ ሺህ) ብር በላይ ወጭ ተደርጓል። በድጋፉም ርክክቡ ወቅትም የማኅበረ ቅዱሳን ዋናው ማእከል ልዑካን፣ የደባርቅ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሰለሞን ጌትነት፣ የጎንደርና ደባርቅ ማእከላት ተወካዮች ታኅሣሥ 6 ቀን 2016 ዓ.ም በቦታው ተገኝተው ድጋፉን ለተጎጅዎች እጅ በእጅ አስረክበዋል።  

ድጋፉ የሜሪላንድ ኆኅተ ምሥራቅ ቅድስት ኪዳነ ምሕረት ቤተ ክርስቲያን፣ ማኅበረ ቅዱሳን ካናዳ ማእከልና ሌሎች በጎ አድራጊ ምእመናንና ተቋማት ባደረጉት የገንዘብ ድጋፍ የተከናወነ ነው። በተመሳሳይ መረጃ በቅርብ ጊዜያት ብቻ በዋግሕምራ የተለያዩ አካባቢዎች ለሚገኙ ተፈናቃዮች፣ በደቡብ ኦሞ በናጸማይ ወረዳ በድርቅ ለተጎዱ ወገኖች፣ ከቅበት ተፈናቅለው ቡታጅራ ይገኙ ለነበሩ ተጎጅዎች ተመሳሳይ ድጋፎች ተደርገዋል።

ማኅበረ ቅዱሳን በቀጣይ ጊዜያትም በድርቅና ልዩ ልዩ ማኅበራዊ ቀውሶች ለተጎዱ አካባቢዎች ተጨማሪ ድጋፎችን ለማድረስ የሚያከናውናቸው የአስቸኳይ ድጋፍና መልሶ ማቋቋም ሥራዎችን አጠናክሮ ለማስቀጠል በሚደረገው የሰብአዊነት ሥራ ምእመናን፣ ማኅበራት፣ ልዩ ልዩ ተቋማትና በጎ አድራጊ ድርጅቶች የተለመደ ድጋፍ እንድታደርጉልን ሲል ጥሪውን ያቀርባል።

ለእነዚህ መሰል ሰብአዊ ፕሮጀክቶች ድጋፍ ለማድረግም፡- በማኅበረ ቅዱሳን የማኅበራዊ ድጋፍና መልሶ ማቋቋም ሒሳብ ቁጥሮች፡-

በማኅበረ ቅዱሳን የማኅበራዊ ድጋፍና መልሶ ማቋቋም ሒሳብ ቁጥሮች፡-
1. በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ - 1000309803648
2. በአሐዱ ባንክ - 0025393810901
4. በወጋገን ባንክ - 0837331610101
5. በአቢሲንያ ባንክ - 37235458
6. በአዋሽ ባንክ 01329817420400                                                                                                   7. በወገን ፈንድ፡- https://www.wegenfund.com/causes/nu-badereqe-yatagodu-waganocaacenene-hheyete-eneta/  መጠቀም የምትሉ መሆኑን እንገልጻለን።                                                        
ለበለጠ መረጃ
•  09 43 00 04 03
•  09 84 18 15 44 
ማኅበረ ቅዱሳን ሕንጻ 1ኛ ወለል
የማኅበረ ቅዱሳን ሙያና ማኅበራዊ አገልግሎት ማስተባበሪያ

6 months ago

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ ፡፡ አሜን ፡፡

እንኩዋን ለታላቁ ቅዱስ አባ ዮሐንስ ሐጺር እና ለቅዱስ ኤልሳዕ ነቢይ ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ

ቅዱስ አባ ዮሐንስ ሐጺር

በቤተ ክርስቲያን ያሉ አበው ሊቃውንት እንደሚሉት ከቅዱሳን በቁመቱ የአባ አርሳኒን ያክል ረዥም አልነበረም:: እርሱ እንደ ዝግባ ቀጥ ያለ ነበር:: በዚያው ልክ ደግሞ የቅዱስ ዮሐንስን (ዛሬ የምናከብረውን) ያህል አጭር አልነበረም:: በዚህ ምክንያት ይሔው ለዘለዓለም "ዮሐንስ ሐጺር - አጭሩ አባ ዮሐንስ" ሲባል ይኖራል::

ሊቃውንትም ቁመቱንና ቅድስናውን በንጽጽር ሲገልጡ:-
"ሰላም ሰላም ዕብሎ በሕቁ:
ለዮሐንስ ሐጺር ዘነዊኅ ሒሩተ ጽድቁ
" ይላሉ:: "ቁመቱ እጅግ ያጠረ: ጽድቁ ግን ከሰማይ የደረሰ ቅዱስ ዮሐንስን ሰላም ሰላም እንለዋለን" እንደ ማለት ነው::

ቅዱሱ የተወለደው በ4ኛው መቶ ክ/ዘመን በምድረ ግብጽ ነው:: ወላጆቹ ምንም ከሥጋዊ ሃብት ድሆች ቢሆኑም ባለ መልካም ክርስትና ነበሩና በጐውን ሕይወት አስተምረውታል:: ወደ ምናኔ የገባው ገና በ18 ዓመቱ ሲሆን የታላቁ አባ ባይሞይ ደቀ መዝሙር ሆኖ ተጋድሎንና ትሕርምትን ተምሯል::

ቅዱስ ዮሐንስ ሐጺር በወቅቱ ከነበሩ ቅዱሳን ከቁመቱ ባሻገር በትሕትናው: በትእግስቱና በመታዘዙ ይታወቅ ነበር:: አባ ባይሞይ ይጠራውና ያለ ምንም ምክንያት ደብድቦ ያባርረው ነበር:: እርሱ ግን "ምን አጠፋሁ?" ብሎ እንኩዋ ሳይጠይቅ "አባቴ ሆይ! ማረኝ?" እያለ ከእግሩ ሥር ይወድቅ ነበር::

ለብዙ ጊዜ በተመሳሳይ ሲደበድበው: እርሱም እርሱው ተደብድቦ: እርሱው ይቅርታን ሲጠይቅ ኖረ:: አንድ ቀን ግን እንደ ልማዱ ሊገርፈው ሲሔድ 7ቱ ሊቃነ መላእክት ከበውት አይቶ ደንግጦ ተመልሷል::

አባ ባይሞይ ይሕንን ሁሉ የሚያደርገው ጠልቶት ወይ ክፉ ሆኖ አይደለም:: አንድ ሰው የሌላኛውን ግፍ መቀበል ካልቻለ ሰይጣንን ድል አይነሳም የሚል ትምሕርት ስለ ነበረ ነው እንጂ::

አንድ ቀን ቅዱስ ዮሐንስ ወደ መምሕሩ ቀርቦ "አባቴ ጅብ ካገኘሁ ምን ላድርግ?" ሲል ጠየቀው:: (የአካባቢው ጅብ መናጢ ነበር) አባ ባይሞይ ግን "ይዘህልኝ አምጣው" አለው:: ትዕዛዝ ነውና ቅዱሱ ወደ በርሃ ወርዶ: ጅብ አልምዶ ይዞለት መጥቷል::

ሌላ ቀን ደግሞ አባ ባይሞይ ቅዱስ ዮሐንስን ጠራውና ተፈልጦ የወደቀ ደረቅ እንጨት ሠጠው:: "ምን ላድርገው አባ?" አለው:: "ትከለውና እንዲያፈራ አድርገው:: ከዚያ አምጥተህ አብላኝ" ሲል መለሰለት:: ይህ ነገር ከተፈጥሮ ሥርዓት ውጪ መሆኑን እያወቀ ቅዱስ ዮሐንስ "እሺ" ብሎ ወስዶ ተከለው::

ከዚያም ለ2 ዓመታት ሳይታክት ውሃ አጠጣው:: ውሃውን የሚያመጣበት ቦታ ደግሞ 10 ኪሎ ሜትር ያህል ከገዳሙ ይርቅ ነበር:: ቅዱሱ ላቡን እያፈሰሰ አሁንም ማጠጣቱን ቀጠለ::

በ3ኛው ዓመት ግን ለምልሞ አበበ: ደግሞም አፈራ:: ካፈራው በኩረ ሎሚም ወስዶ ለመምሕሩ "አባቴ! እንካ ብላ" ብሎ ሰጠው:: አባ ባይሞይ ግን ማመን አልቻለም:: እጅግ አደነቀ: አለቀሰም::

ወዲያው ያን ፍሬ ታቅፎ ወስዶ ለገዳሙ መነኮሳት አላቸው- "ንሱ ብሉ: በረከትንም አግኙ:: ይህ የዛፍ ሳይሆን የመታዘዝ ፍሬ ነው:: ቅዱስ ዮሐንስ አባ ባይሞይ ቢታመም ለ12 ዓመት አስታሞታል::

መምሕሩ ከማረፉ በፊትም መነኮሳቱን ሰብስቦ የቅዱስ ዮሐንስን እጅ አስጨበጣቸው:: "ይህ የያዛችሁት እጅ የሰው ሳይሆን የመልአክ እጅ ነው" ብሏቸው ዐርፏል:: ቅዱስ ዮሐንስም ከዓመታት ቆይታ በሁዋላ የገዳሙ አበ ምኔት ሆኖ አገልግሏል:: ብዙ ነፍሳትንም ለቅድስና ማርኩዋል::

መላእክት ንጽሕናው ደስ ስለሚያሰኛቸው አብረውት ይውሉ ነበር:: ሲተኛም በተራ በተራ ክንፋቸውን ያለብሱት ነበር:: ምጽዋትን በጣም ስለሚወድ ሰፌድ እየሰፋ ይሸጥና ገንዘቡን ለነዳያን ያን ያካፍል ነበር::

አንድ ቀን እንደ ልማዱ ወደ ገበያ ወጥቶ ሳለ ተደሞ (ተመስጦ) መጣበት:: ሰማያት ተከፍተው: ቅዱሳን ሊቃነ መላእክት ሚካኤልና ገብርኤል በግርማ በጌታ ፊት ቆመው ተመለከተ::

"እጹብ: እጹብ" እያለ ሲያደንቅ አንድ ገዢ መጥቶ "ባለ እንቅብ ዋጋው ስንት ነው?" ቢለው "እኁየ ሚካኤልኑ የዓቢ ወሚመ ገብርኤል - ከሚካኤልና ከገብርኤል ማን ይበልጣል?" ብሎታል:: ገዢውም ደንግጦ "እብድ መነኩሴ" ብሎት ሔዷል::

ቅዱስ ዮሐንስ ሐጺር ወደ ባቢሎን (የአሁኗ ኢራቅ) ሒዶ ከተመለሰ በሁዋላ በበርበሮች ምክንያት ከአስቄጥስ ወደ ቁልዝም ተሰዷል:: በዚያም በአባ እንጦንስ በዓት ውስጥ ዐርፏል:: ለ400 ዓመታት በዚያው ቆይቷል::

825 ዓ/ም ግን በአባ ዮሐንስ ፓትርያርክ ዘመን ክቡር ሥጋው ወደ ገዳመ አስቄጥስ ተመልሷል:: ቅዱሱ ያረፈው ጥቅምት 20 ቀን ሲሆን ዛሬ ሥጋው የፈለሠበት ነው:: በዚህ ዕለትም የቅዱስ ዮሐንስ ሐጺርና የታላቁ ቅዱስ መቃርስ ሥጋ በተገናኙ ጊዜ ግሩም ተአምር ተደርጉዋል:: ወደ ቤተ ክርስቲያኑ ሲገባም ታላቅ የብርሃን ጐርፍ ሲፈስ ታይቷል::

ሰማያዊ መዓዛም አካባቢውን ሞልቶታል:: ከዻዻሳቱ አንዱ እባረካለሁ ብሎ የቅዱስ ዮሐንስን ሥጋ ቢገልጠው አካባቢው ተናወጠ:: መባርቅትም (መብረቆች) ተብለጨለጩ:: ደንግጠው ቶሎ ቢያለብሱት ጸጥታ ሆኗል:: በዚህ ሁሉ ደስ ያላቸው አበው ቅዱሱን በዝማሬ ሲያወድሱት ውለዋል::

ቅዱስ ኤልሳዕ ነቢይ

- ከነቢያተ እሥራኤል አንዱ
- ከእርሻ ሥራ ቅዱስ ኤልያስን የተከተለ
- መናኔ ጥሪት የተባለ
- በድንግልና ሕይወት የኖረ
- የታላቁ ነቢይ ኤልያስ መንፈስ እጥፍ የሆነለት
- እጅግ ብዙ ተአምራትን ያደረገ
- አንዴ በሕይወቱ: አንዴ በአጽሙ ሙታንን - - ያስነሳ ታላቅ ነቢይና አባት ነው::

ቅዱስ ኤልሳዕ በጣም ረዥም: ራሱ ገባ ያለ (ራሰ በራ): ቀጠን ያለ: ፊቱ ቅጭም ያለ (የማይስቅ) ሽማግሌ ነበር::

አምላከ ቅዱሳን የሐጺር ቅዱስ ዮሐንስን መታዘዙን: ትሕትናውን: ትእግስቱንና ቅንነቱን ያድለን:: በበረከቱም ይባርከን::

#ጥቅምት_20 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ
የቅዱሳን በዓላት
1.ቅዱስ አባ ዮሐንስ ሐጺር
2.ቅዱስ ኤልሳዕ ነቢይ
3.አባ ባይሞይ

ወርኀዊ በዓላት
1..ቅዱስ ዮሐንስ ሐፂር
2.ቅዱስ አክሎግ ቀሲስ
3.ቅዱስ አፄ ካሌብ ጻድቅ (ንጉሠ ኢትዮዽያ)
4.አባ አሞንዮስ ዘሃገረ ቶና
5.ቅድስት ሳድዥ የዋሒት
6.ቅዱስ ወክቡር ማር ቴዎድሮስ ሰማዕት

" እናንተ ደግሞ የታዘዛችሁትን ሁሉ ባደረጋችሁ ጊዜ 'የማንጠቅም ባሪያዎች ነን: ልናደርገው የሚገባንን አድርገናል' በሉ``:: " (ሉቃ. 17:10)

ወስብሐት ለእግዚአብሔር

"ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እንግር ዜናሆሙ ለቅዱሳን":: የቅዱሳንን ዜና(ታሪክ) እንድመሰክር ፍቅር ያስገድደኛል:: 

የቴሌግራም ገፃችን - https://t.me/betel_et
የፌስቡክ ገጻችን - https://www.facebook.com/profile.php?id=61552723809417

Telegram

| ቤተል |

"ቤተክርስቲያን ወደ እግዚአብሔር እንድንቀርብ የምታደርገን የልዑል እግዚአብሔር ደጅ ናት፡፡" https://www.facebook.com/profile.php?id=61552723809417

**በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ ፡፡ አሜን ፡፡**
We recommend to visit

ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ

Last updated hace 1 día, 17 horas

ለማንኛውም አስተያየት እና ጥቆማ 👉 @Esat_tv_comment_bot

🇪🇹ኢሳት የኢትዮጵያ አይን እና ጆሮ🇪🇹

Last updated hace 5 días, 6 horas

Last updated hace 5 días, 19 horas