ወሒድ የንጽጽር ማኅደር

Description
ወንድም ወሒድ በኢሥላም እና በክርስትና መካከል ያለውን ልዩነት እና አንድነት በንጽጽር የሚያስቀምጥ ወንድም ነው። ለዚህም የቋንቋ፣ የሰዋስው፣ የዐውድ፣ የተዛማች እና የሥነ አመክንዮ ሙግት በማቅረብ የሚታወቅ ተሟጋች እና ጦማሪ ነው። ለሙግቱ ነጥብ በዋነኝነት የሚጠቀምባቸው ቋንቋ ዐማርኛ፣ ግዕዝ፣ እንግሊዝኛ፣ ዐረቢኛ፣ ዕብራይስጥ እና ግሪክ ናቸው። መልካም የንባብ፣ የጥናት፣ የማነጻጸር ጊዜ ይሁንልዎ!
Advertising
We recommend to visit

ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ

Last updated 1 month, 3 weeks ago

ለማንኛውም አስተያየት እና ጥቆማ 👉 @Esat_tv_comment_bot

🇪🇹ኢሳት የኢትዮጵያ አይን እና ጆሮ🇪🇹

Last updated 4 days, 5 hours ago

በዚህ ቻናል ሀገራዊና አለምአቀፋዊ መረጃዎችን በፍጥነት ያገኛሉ❗
የውስጥ መስመር👉http://t.me/ayulaw

Last updated 3 weeks, 2 days ago

1 month, 3 weeks ago

ጉባኤው የማታ ማታ ኢየሱስ "ቴዎን ኤክ ቴዉ" Θεὸν ἐκ Θεοῦ ማለትም "ከአምላክ የተገኘ አምላክ ነው" በማለት አጸደቀ፥ "አምላክ አምላክን አህሎ እና መስሎ፣ ከባሕርይ ባሕርይ ወስዶ፣ ከአካል አካል ወስዶ ተወለደ" በማለት "ሆ ቴዎስ ሆ ሁዎስ" Ο Θεός ο γιος ማለትም "እግዚአብሔር ወልድ"God the Son" የሚል የአቋም መግለጫ ተሰጠ።

ከዚህ ጉባኤ ተነስተን ጥያቄ እናጭራለን፦
፨በኒቂያ ጉባኤ ድንጋጌ ላይ አምላክ አምላክን ከወለደ ሁለት አምላክ አይሆንም?
፨አምላክ አምላክን አስገኘ የሚለው ትምህርት ሕሊናስ ይቀበለዋልን?
፨ማስገኘት መንስኤ መገኘት ውጤት ከሆነ መቀዳደም ስላለ ጅማሮ እና መነሾ ያለው አምላክ ምን ዓይነት አምላክ ነው?

ይህ የነገረ ክርስቶስ"Christology" ውዝግብ ጠመዝማዛ መንገዱ የጀመረው ከዚህ ጉባኤ ጀምሮ ነው። አንብሮስ ዘሚለን "አብ የወልድ ኑባሬ ምንጭ እና ሥር ነው"ይለናል፦
"አብ የወልድ ኑባሬ ምንጭ እና ሥር ነው"
Exposition of the Christian Faith (Ambrose) > Book IV(4) Chapter 10 Number 133

አብ አስገኚ ወልድ ግኝት ከሆነ በመስኤ እና በውጤት በመካከላቸው መቀዳደም አለ፥ ዛሬ ላይ ዐበይት ክርስቲያኖች፦ "ወልድ ከአብ ባሕርይ ባሕርይን ወስዶ፣ ከአካሉ አካልን ወስዶ እና አብን አህሎና መስሎ ከእርሱ ወጣ፣ ተወለደ፣ ተገኘ" በማለት አሏህን ወላዲ መሢሑን ተወላዲ በማድረግ ለአሏህ ቁራጭን አደረጉለት፦
43፥15 ከባሮቹም ለእርሱ ቁራጭን ልጅ አደረጉለት፡፡ ሰው በእርግጥ ግልጽ ከሓዲ ነው፡፡ وَجَعَلُوا لَهُ مِنْ عِبَادِهِ جُزْءًا ۚ إِنَّ الْإِنسَانَ لَكَفُورٌ مُّبِينٌ

ከአንዱ አምላህ ባሕርይ ባሕርይን ወስዶ፣ ከአካሉ አካልን ወስዶ፣ እርሱን አህሎና መስሎ ከእርሱ ወጣ፣ ተወለደ፣ ተገኘ ማለት የአምላክን አንድነት ክፉኛ የሚያናጋ ትምህርት ነው። በዚህ ውዝግብ ጊዜ አምላካችን አሏህ እነዚያን «አሏህ ልጅን ወልዷል» ያሉትን ሊያስጠነቅቅበት ቁርኣንን አወረደው፦
18፥4 እነዚያንም «አሏህ ልጅን ወልዷል» ያሉትን ሊያስጠነቅቅበት አወረደው፡፡ وَيُنذِرَ الَّذِينَ قَالُوا اتَّخَذَ اللَّهُ وَلَدًا

አምላካችን አሏህ አንድ ነው፥ እርሱ የሁሉ መጠጊያ ነው። አምላክ ከወለደ ይባዛል፥ ከተወለደ በአጭር ቁመት በጠባብ ደረት ይወሰናል፣ ያድጋል፣ ይሞታል። አሏህ ግን አንድ ነውና አልወለደም አልተወለደምም፦
112፥1 በል «እርሱ አላህ አንድ ነው፡፡ قُلْ هُوَ اللَّهُ أَحَدٌ
112፥2 «አሏህ የሁሉ መጠጊያ ነው»፡፡ اللَّهُ الصَّمَدُ
112፥3 «አልወለደም አልተወለደምም»፡፡ لَمْ يَلِدْ وَلَمْ يُولَدْ

አሏህ መውለድ መወለድ የሚባል ባሕርይ ስለሌለው ብጤ፣ አምሳያ፣ ተፎካካሪ፣ እኩያ፣ ወደር፣ እኩያ አንድም የለውም፦
114፥4 «ለእርሱም አንድም ብጤ የለውም»። وَلَمْ يَكُن لَّهُ كُفُوًا أَحَدٌ

"ኩፉው" كُفُو ማለት "ወደር" "እኩያ" "አቻ" "ብጤ" "አምሳያ" "ተፎካካሪ" "ባላንጣ" ማለት ሲሆን እርሱ የሚተካከለው አቻ እና እኩያ እንዲሁ የሚመሳሰለው አምሳያ እና ቢጤ ከሌለው «አሏህ ወለደ» ያሉት እነርሱ በእርግጥ ውሸታሞች ናቸው፦
37፥152 «አሏህ ወለደ» አሉ፥ እነርሱም በእርግጥ ውሸታሞች ናቸው፡፡ وَلَدَ اللَّهُ وَإِنَّهُمْ لَكَاذِبُونَ

ክርስቲያኖች ሆይ! ከዚህ ውስብስብ ትምህርት ወጥታችሁ በአንድነት ላይ ሁለትነት፣ መከፋፈል፣ መባዛት የሌለበትን አንዱን አምላክ አሏህን በብቸኝነት እንድታመልኩት ጥሪያችን ነው። አሏህ ሂዳያህ ይስጣችሁ! ለእኛም ጽናቱን ይስጠን! አሚን።

ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://t.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም

1 month, 3 weeks ago

የኒቂያ ጉባኤ

በአሏህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

112፥3 «አልወለደም አልተወለደምም»፡፡ لَمْ يَلِدْ وَلَمْ يُولَدْ

ጥንት ላይ የነበሩ ነቢያት እንዲሁ ኢየሱስ እና ሐዋርያት አሓዳዊያን"Unitarian" የነበሩ ሲሆን ከሐዋርያት ኅልፈት በኃላ የተነሱ የቤተክርስቲያን አበው ደግሞ በሂደት "ክልዔታውያን"Binitarian" ነበሩ። ከክልዔታውያን አበው መካከል ጠርጡሊያኖስ"Tertullian" ስለ ወልድ ሲናገር እንዲህ ይለናል፦
"አብ አጠቃላይ ባሕርይ ነው፥ ነገር ግን ወልድ የአጠቃላዩ መገኘት እና ክፍል ነው"
(Against Praxeas (Tertullian), Chapter 9).

አንድ ሰው ሰውነቱ ከራሱ ጋር ኖሮ ኖሮ ልክ ሲወልድ አባት እንደሚባለው አንድ አምላክ አምላክነቱ ከራሱ ጋር ኖሮ ኖሮ ልክ ሲወልድ አብ ተባለ የሚል ትምህርት ያስተማረው ጠርጡሊያኖስ ዘካርቴጅ ነው፦
"ምክንያቱም አምላክ እንዲሁ አብ ነው፥ እንዲሁ ደግሞ እርሱ ፈራጅ ነው። ሁልጊዜም አምላክ በሆነው መሠረት ላይ ብቻ እርሱ ግን ሁልጊዜ አብ እና ፈራጅ አልነበረም፥ ከወልድ በፊት አብ ሊሆን አይችልም፤ እንዲሁ ከኃጢአት በፊት ፈራጅ ሊሆን አይችልም። ነገር ግን በእርሱ ዘንድ ኃጢአት ባልነበረበት እና እንዲሁ ወልድ ባልነበረበት ወቅት ጊዜ ነበር፥ የመጀመሪያው ጌታ ፈራጅ ሆኖ እና የኃለኛ አብ ሆኖ መመሥረት ነበር። በዚህ መንገድ እርሱ ጌታ ሊሆን ከነበረባቸው ነገሮች በፊት ጌታ አልነበረም፥ ነገር ግን እርሱ ግን ወደፊት በሆነ ጊዜ ብቻ ጌታ ሊሆን ነበር። ልክ እንደዚሁ እርሱ በወልድ አብ እንደ ሆነ በኃጢአትም ፈራጅ ሆነ።
Against Hermogenes (Tertullian) chapter 3

ተመልከቱ! አብ ያለ አባትነት ከፍጥረት በፊት ወልድን እስከሚወልድበት ጊዜ ብቻውን በአምላክነት ነበር የሚለው እሳቤ የጠርጡሊያኖስ እሳቤ ነው፦
"ከፍጥረት በፊት እስከ ወልድ ውልደት ነበረ፥ ከሁሉ ነገር በፊት አምላክ ብቻውን ነበረ"።
Against Praxeas (Tertullian) Chapter 5.

በዚህ ወቅት የትርጓሜ ትምህርት ቤት"School of Thought" በእስክንድሪያ እና በአንጾኪያ ነበር፥ የእስክንድሪያን ትምህርት ቤት በአፍላጦን"Plato" ፍልስፍና ሰርጎገብ መሠረት ያረገ ሲሆን የአንጾኪያው ትምህርት ቤት ደግሞ በአሪስጣጣሊስ"Aristotle" ፍልስፍና መሠረት ያረገ ነው። በእስክንድሪያ ትምህርት ቤት ይማር የነበረው አትናቴዎስ ዘእስክንድሪያ "ከአምላክ አምላክ ተወለደ" የሚል አቋም ሲኖረው በአንጾኪያ ትምህርት ቤት ይማር የነበረው አርዮስ ዘሊቢያ "ከአምላክ አምላክ ተፈጠረ" የሚል አቋም ነበረው፥ አርዮስ ዘሊቢያ ስለ አቋሙ እንዲህ ይለናል፦
"አብ ወልድን ከወለደው የተወለደው መጀመሪያ ነበረው፥ ከዚህም ክስተት የተነሳ ልጁ ያልነበረበት ጊዜ እንደ ነበረ ግልጥ ነው። ስለዚህም እርሱ [ወልድ] ምንነቱ ካለመኖር እንደ ነበረው ነው"።
(Socrates of Constantinople, Church History, Book I, Ch. 5.)

በሁለቱ ውዝግብ የመጀመሪያው ዓለም ዓቀፍ ሲኖዶስ በኒቂያ ተካሄደ፥ "ሲኖዶስ" σύνοδος ማለት "ጉባኤ" "ስብሰባ"council" ማለት ነው። ኒቂያ፣ ቆስጠንጢኒያ፣ ኤፌሶን እና ኬልቄዶን በጥንት ጊዜ ቱርክ ውስጥ የሚገኙ ከተሞች ናቸው። በ325 ድኅረ ልደት በንጉሥ ቆስጠንጢኖስ ሊቀ መንበርነት የኒቂያ ጉባኤ ላይ 318 ኤጲጵ ቆጶሳት ከመላው ዓለም ተሰብስበው "ሆሙኡሲዮስ" እና "ሆሞኡሲዮስ" የሚባሉ ክርክሮችን ለመታደም መጡ፥ "ሆሙኡሲዮስ" ὅμοιοιούσιος የአርዮስ አቋም ሲሆን "ሆሞኡሲዮስ" ὁμόιοιούσιος ደግሞ የአትናቴዎስ አቋም ነው።
"ኡሲያ" οὐσία የሚለው ቃል "ኤይሚ" εἰμί ማለትም "ነኝ" ከሚል አያያዥ ግሥ የተገኘ ሲሆን "ህላዌ" "ሃልዎት" "ኑባሬ" የሚል ትርጉም አለው፥ "ሆሙስ" ὅμοιος ማለት "የተለያየ" ማለት ሲሆን "ሆሞስ" ὁμός ማለት ደግሞ "ተመሳሳይ" ማለት ነው።

፨አርዮስ፦ "ወልድ ፍጡር ነው፥ አንዱ አምላክ አብ እና ኢየሱስ "ሆሙኡሲዮስ" ὅμοιοιούσιος ማለትም "የተለያየ ህላዌ" እንጂ ተመሳሳይ አይደለም" በማለት ኢየሱስ "ሆሙኡሲዮን ቶ ፓትሪ" ὅμοούσιον τῷ Πατρί ማለት "ከአብ ጋር የተለያየ ህላዌ ነው" የሚል አቋም ነበረው።
፨አትናቴዎስ፦ "ወልድ ፍጡር አይደለም፥ አንዱ አምላክ አብ እና ኢየሱስ "ሆሞኡሲዮስ" ὁμόιοιούσιος ማለትም "ተመሳሳይ ህላዌ" እንጂ የተለያየ አይደለም" በማለት ኢየሱስ "ሆሞኡሲዮን ቶ ፓትሪ" ὁμόούσιον τῷ Πατρί ማለት "ከአብ ጋር ተመሳሳይ ህላዌ ነው" የሚል አቋም ነበረው።

1 month, 3 weeks ago

የሃይማኖት ንጽጽር ኮርስ

በወሒድ ዕቅበተ ኢሥላም ማኅበር"Wahid islamic apologetics society" 13ኛ ዙር የሙቃረናህ ደርሥ!

"ሙቃረናህ" مُقَارَنَة የሚለው ቃል "ቃረነ" قَارَنَ ማለትም "አነጻጸረ" ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን "ንጽጽር" ማለት ነው፥ ሙቃረናህ የሃይማኖት ንጽጽር"Comparative Religion" ሲሆን በዱኑል ኢሥላም እና እና በክርስትና መካከል ያለው የሥነ መለኮት አንድነት እና ልዩነት እየተነጻጸረ የሚቀርብበት ጥናት ነው። ደርሡ (ትምህርቱ) የሚፈጀው 7 ወር ኢንሻሏህ ሲሆን ሁለት ተርም አለው።

፨ የመጀመሪያው ተርም ዐጽመ አሳብ በፈጣሪ እሳቦት ላይ የሚያውጠነጥነው፦
1.በነገረ ሥላሴ ጥናት"Triadogy"
2.በነገረ ክርስቶስ ጥናት"Christology"
3.በነገረ ማርያም ጥናት"Mariology"
4. በነገረ መላእክት ጥናት"angelology"
5. በነገረ ምስል ጥናት"Iconlogy" ላይ ነው።

፨ የሁለተኛው ተርም ዐጽመ-አሳብ በቅዱሳን መጽሐፍት ላይ የሚያውጠነጥነው፦
1.በአህሉል ኪታብ"People of the Book"
2.በመጽሐፍት"scriptures"
3. በመጽሐፍ አጠባበቅ"preservation"
4.በመጽሐፍት ልኬት"Standardization"
5. በባይብል ግጭት"Contradiction"
6. በኦሪት"Torah"
7. በወንጌል"Gospel" ላይ ነው።

አባሪ ኮርሶች፦
1. ዐቂዳህ"creed"
2. ሥነ ምግባር"ethics"
3. ሥነ አመክንዮ"logic"
4. ሥነ ልቦና"psychology"
5. ሥነ ቋንቋ"linguistics" ናቸው።

ለመመዝገብ ከታች የተዘረዘሩት አድሚናት በውስጥ ያናግሩ!
እኅት ጀሙቲ፦ http://t.me/myprophet34
ወንድም አቡ ኑዓይም፦https://t.me/arhmanu
እኅት ሰላም፦ http://t.me/SeuweSe
አኅት ዘሃራ፦ https://t.me/Zhara_mustefa
እኅት አበባ፦ http://t.me/selemtewa

ቦታ ሳይያዝ ይመዝገቡ! መልካም የትምህርት ጊዜ ይሁንልዎ!
ወጀዛኩሙላህ ኸይራ!

1 month, 3 weeks ago

ተአምረ ማርያም የዘወትር መቅድም ቁጥር 35-36 ገጽ 7
ግዕዙ፦
"ወቅድመ ስዕላ ስግዱ! ዘኢሰገደ ላቲ ይደምስስ እምቅዋሙ ወኢይትዐወቅ ዝግረ ስሙ። ወይበሉ መላእክተ ሰማይ ኲሎሙ አሜን"።

ትርጉም፦
"በስዕሏ ፊት ስገዱ! ለሥዕሏ ያልሰገደ ግን ከቆመበት ቦታ ይጥፋ! ስም አጠራሩ አይታወቅ። በሰማይ ያሉ መላእክትም ይደረግ ይሁን ይበሉ"።

"በስዕሏ ፊት ስገዱ! ለሥዕሏ ያልሰገደ ግን ከቆመበት ቦታ ይጥፋ" የሚል እያለ "እኛ ለስዕል አንሰግድም" ብሎ ማቄሉን እዛው የማያነቡትን ያቂል! በኦርቶዶክስ መምህራን "እኛ ለስዕል አንሰግድም" የሚል እንዲህ ዓይነት ለውጥ እንዴት ሊመጣ ቻለ? ሲባል መልሱ የሙሴ አምላክ ለሙሴ፦ "የተቀረጸም ምስል ወይም ሐውልት አታቁሙ፤ ትሰግዱለትም ዘንድ በምድራችሁ ላይ የተቀረጸ ድንጋይ አታኑሩ፣ የማናቸውንም ምሳሌ፥ የተቀረጸውንም ምስል ለአንተ አታድርግ፣ አትስገድላቸው፥ አታምልካቸውምም” ብሎ አዞልታ፤ እንደውም መዝሙረኛው፦ "ለተቀረጸ ምስል የሚሰግዱ ሁሉ ይፈሩ" ስለሚል ነው፦
ዘሌዋውያን 26፥1 እኔ ያህዌህ አምላካችሁ ነኝና ለእናንተ ”ጣዖት አታድርጉ፥ የተቀረጸም ምስል ወይም ሐውልት አታቁሙ”፤ ትሰግዱለትም ዘንድ በምድራችሁ ላይ የተቀረጸ ድንጋይ አታኑሩ።
ዘጸአት 20፥4 በላይ በሰማይ ካለው፥ በታችም በምድር ካለው፥ ከምድርም በታች በውኃ ካለው ነገር ”የማናቸውንም ምሳሌ፥ የተቀረጸውንም ምስል ለአንተ አታድርግ፤ አትስገድላቸው፥ አታምልካቸውምም”*፤
መዝሙር 97፥7 ”ለተቀረጸ ምስል የሚሰግዱ ሁሉ፥ በጣዖቶቻቸውም የሚመኩ ይፈሩ፤ መላእክቱ ሁሉ ስገዱለት።

ሰው ለሠራው የእጅ ሥራ እንዴት ይሰገዳል? በኦርቶዶክስ፣ በካቶሊክ እና በአንግሊካን ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ለስዕል የጸጋ ስግደት ይሰገዳል፤ ልብ አድርግ የጸጋ ስግደት ስገዱ የሚል ትእዛዝ የለም። በተቃራኒው ለተቀረጸ ምስል "አትስገድላቸው" የሚል ትእዛዝ ቢኖር እንጂ። ይህንን አስፈሪ ወንጀል እያየ ወደ ክርስትና የሚገባ ሰው ቂል ካልሆነ ወይም በጥቅማ ጥቅም አሊያም በተቃራኒ ፆታ ፍቅር መነደፍ ካልሆነ በስተቀር አይሞክረውም። ይህንን ፍርድ እያወቀ ወደ ኢሥላም የማይመጣ በእሳት የሚጫወት ነው፦
41፥37 ሌሊትና ቀንም ፀሐይና ጨረቃም ከምልክቶቹ ናቸው፡፡ ለፀሐይና ለጨረቃ “አትስገዱ”፡፡ ለእዚያም ለፈጠራቸው ለአሏህ “ስገዱ” ፡፡ እርሱን ብቻ “የምታመልኩ” እንደ ኾናችሁ ”ለሌላ አትስገዱ”፡፡ وَمِنْ آيَاتِهِ اللَّيْلُ وَالنَّهَارُ وَالشَّمْسُ وَالْقَمَرُ ۚ لَا تَسْجُدُوا لِلشَّمْسِ وَلَا لِلْقَمَرِ وَاسْجُدُوا لِلَّهِ الَّذِي خَلَقَهُنَّ إِن كُنتُمْ إِيَّاهُ تَعْبُدُون

" እርሱን ብቻ የምታመልኩ እንደ ኾናችሁ ለሌላ አትስገዱ" የሚለው ኃይለ ቃል ይሰመርበት! በኢሥላም ፈጣሪ ከሆነው ከአንዱ አምላክ ከአሏህ ውጪ የሚሰገድለት ማንነት ሆነ ምንነት የለም። ስዕል የሰው እጅ ሥራ ነው፤ ለዚህ ግዑዝ ነገር የምትሰግዱ ካላችሁ ጊዜው ሳይረፍድ ወደ አሏህ በንስሓ ተመለሱ! ከአሏህ በቀር የምትጠሯቸው ሊረዷችሁ አይችሉም፤ እራሳቸውንም አይረዱምና፦
7፥197 እነዚያም ከእርሱ በቀር የምትጠሯቸው ሊረዷችሁ አይችሉም፤ እራሳቸውንም አይረዱም። وَٱلَّذِينَ تَدْعُونَ مِن دُونِهِۦ لَا يَسْتَطِيعُونَ نَصْرَكُمْ وَلَآ أَنفُسَهُمْ يَنصُرُونَ

ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://t.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም

1 month, 3 weeks ago

በወሒድ ዕቅበተ ኢሥላም ማኅበር ድረ ገጽ ላይ አዲስ የተለቀቁ 👇

1) የባሕርይ እናት
https://www.wahidislamicapologetics.org/የባሕርይ-እናት/

2)ታላቁ ገደል/

https://www.wahidislamicapologetics.org/ታላቁ-ገደል/

3) ተዋዱዕ

https://www.wahidislamicapologetics.org/ተዋዱዕ/

🌐 ወደ ድረ ገጹ ለመግባት
http://www.wahidislamicapologetics.org

1 month, 3 weeks ago

ባወቀ ኖሮ

በአሏህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

8፥23 በውስጣቸውም ደግ መኖሩን አሏህ ባወቀ ኖሮ ባሰማቸው ነበር፡፡ ባሰማቸውም ኖሮ እነርሱ እውነትን የተው ኾነው በሸሹ ነበር፡፡ وَلَوْ عَلِمَ اللَّهُ فِيهِمْ خَيْرًا لَّأَسْمَعَهُمْ ۖ وَلَوْ أَسْمَعَهُمْ لَتَوَلَّوا وَّهُم مُّعْرِضُونَ

ኢሥላም እንደ ትቢያ በኖ እንደ ጢስ ተኖ እንዲጠፋላቸው የሚፈልጉ ሚሽነሪዎች እውነትን የመሸጥ እና የመሸቀጥ አባዜ የተጠናወታቸው ሰዎች እንጂ መስማት እና መስማማት ሞታቸው ነው። እነዚህ ባተሎ እና ዘባተሎ ሙግት የሚሟገቱ ተላላ እና ጽሉል ሰዎች "አሏህ ሁሉን ዐዋቂ አይደለም" ብለው ይህንን ጥቅስ ይጠቅሳሉ፦
8፥23 በውስጣቸውም ደግ መኖሩን አሏህ ባወቀ ኖሮ ባሰማቸው ነበር፡፡ ባሰማቸውም ኖሮ እነርሱ እውነትን የተው ኾነው በሸሹ ነበር፡፡ وَلَوْ عَلِمَ اللَّهُ فِيهِمْ خَيْرًا لَّأَسْمَعَهُمْ ۖ وَلَوْ أَسْمَعَهُمْ لَتَوَلَّوا وَّهُم مُّعْرِضُونَ

"በውስጣቸውም ደግ መኖሩን አሏህ ባወቀ ኖሮ" ማለት "አሏህ የሚያውቀው በውስጣቸው ክፉ መኖሩን ነው" ወይም "አሏህ የሚያውቀው በውስጣቸው ደግ አለመኖሩን ነው" ማለት ነው፥ ሙፈሢሮች ያስቀመጡልን "አሏህ ያላሰማቸው በውስጣቸውም ደግ አለመኖሩን ስለሚያውቅ ነው" በማለት ነው። "ለው" لَوْ የሚለው ሐርፉሽ ሸርጥ የመጣው በውስጣቸው ደግ አለመኖሩን ለማሳየት የገባ አጽንዖታዊ እና አንክሮታዊ ቃል ነው። ለምሳሌ፦ አንድ ነገርን አለመኖሩን ለማሳየት አጽንዖታዊ እና አንክሮታዊ ቃል መግባት በባይብልም የተለመደ ነው፦
ኢሳይያስ 44፥8 ከእኔ ሌላ አምላክ አለን? አምባ የለም፥ ማንንም አላውቅም። הֲיֵ֤שׁ אֱלֹ֙והַּ֙ מִבַּלְעָדַ֔י וְאֵ֥ין צ֖וּר בַּל־יָדָֽעְתִּי׃

"ማንንም አላውቅም" የሚለው ኃይለ ቃል ይሰመርበት! "ያዳአቲ" יָדָֽעְתִּי የሚለው ቃል "ያዳ" יָדַע ማለትም "አወቀ" ከሚል ሥርወ ቃል የመጣ ሲሆን "አውቃለው" ማለት ነው፥ "በል" בַּל־ የሚለው አፍራሽ ቃል ሲሆን "በል ያዳአቲ" בַּל־ יָדָֽעְתִּי ማለት "አላውቅም" ማለት ነው። "ማንንም አላውቅም" ሲል "ሁሉን ዐዋቂ" ከሚል ማንነቱ ጋር ይጋጫል? ወይስ "ማንንም አላውቅም" ሲል "አምልኮ የሚገባው አምላክ ከእኔ ውጪ የለም" ለማለት ፈልጎ ነው? አዎ! "አላውቅም" ሲል "የለም" ለማለት ከሆነ እንግዲያውስ አሏህ የሚያውቀው በውስጣቸው ክፉ መኖሩን ስለሆነ "ደግ በውስጣቸው የለም" ማለት ነው። ሌላ ምሳሌ፦
ሆሴዕ 8፥4 ለራሳቸው ነገሥታትን አነገሡ፥ ከእኔም ዘንድ አይደለም። አለቆችንም አደረጉ፥ እኔም አላወቅሁም። ለጥፋታቸውም ከብራቸውና ከወርቃቸው፤ ጣዖታትን ለራሳቸው አደረጉ። הֵ֤ם הִמְלִיכוּ֙ וְלֹ֣א מִמֶּ֔נִּי הֵשִׂ֖ירוּ וְלֹ֣א יָדָ֑עְתִּי כַּסְפָּ֣ם וּזְהָבָ֗ם עָשׂ֤וּ לָהֶם֙ עֲצַבִּ֔ים לְמַ֖עַן יִכָּרֵֽת׃

እስራኤላውያን ለራሳቸው አለቆች ሲያደርጉ ያህዌህ ስለማያውቅ "እኔም አላወቅሁም" ብሏል። "አላወቅሁም" ለሚለው የገባው ቃል "ቨሎ ያዳአቲ" וְלֹ֣א יָדָֽעְתִּי ሲሆን እርሱ ሳያውቅ እንዴት አንድ ድርጊት ይከናወናል? ሰካራም ሰው በስካር ውስጥ እያለ ሲጎስሙት ስለማይታወቀው የገባው ቃል በተመሳሳይ "በል ያዳአቲ" בַּל־ יָדָֽעְתִּי ነው፦
ምሳሌ 23፥35 መቱኝ፥ ያውም አልተሰማኝም፤
ጐሰሙኝ፥ "አላወቅሁምም"። መቼ እነሣለሁ? ደግሞ ጨምሬ እሻታለሁ ትላለህ። הִכּ֥וּנִי בַל־חָלִיתִי֮ הֲלָמ֗וּנִי בַּל־יָ֫דָ֥עְתִּי מָתַ֥י אָקִ֑יץ אֹ֝וסִ֗יף אֲבַקְשֶׁ֥נּוּ עֹֽוד׃

እንዲህ ዓይን ያስፈጠጠ እና ጥርስ ያገጠጠ ሐቅ ሲመጣ ሞንሟና እና ሸሞንሟና ከመሆን ይልቅ ተረጋግቶ የራስን መጽሐፍ መፈተሽ ይገባል! አየክ ጥቂት ኩርማ መረዳት በጥሪኝ እና በእፍኝ ቀድቶ እና ዘግኖ ማቅረብ ዕቅበተ ኢሥላም ላይ ለሚሠራ ሰው ኢምነት ነው። አምላካችን አሏህ ሂዳያህ ይስጣችሁ! ለእኛም ጽናቱን ይስጠን! አሚን።

ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://t.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም

3 months, 3 weeks ago

ዘካህ ለሠለምቴዎች

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ፥ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው።

2፥219 ”ምንን እንደሚመጸውቱም መጠኑን ይጠይቁሃል፡፡ «ትርፍን መጽውቱ» በላቸው”፡፡ እንደዚሁ ታስተነትኑ ዘንድ አላህ ለእናንተ አንቀጾችን ይገልጽላችኋል፡፡ وَيَسْأَلُونَكَ مَاذَا يُنفِقُونَ قُلِ الْعَفْوَ ۗ كَذَٰلِكَ يُبَيِّنُ اللَّهُ لَكُمُ الْآيَاتِ لَعَلَّكُمْ تَتَفَكَّرُونَ

“ዘካህ” زَكَاة ጥቅላዊ የግዴታ ምፅዋት ማለት ሲሆን የዘካህ ብዙ ቁጥር “ዘካት” زَكَوَات ሲሆን በተናጥል ዘካት በሁለት ይከፈላል፥ እነርሱም “ዘካቱል ማል” زَكَاة المَال እና “ዘካቱል ፊጥር” زَكَاة الفِطْر ናቸው።
“ማል” مَال ማለት “ሀብት” ማለት ሲሆን የማል ብዙ ቁጥር ደግሞ “አምዋል” أَمْوَال ነው፥ ከተቀማጭ ሀብት ላይ ወይም ከትርፍ ላይ የሚሰጠው ዘካህ “ዘካቱል ማል” زَكَاة المَال ይባላል። በነቢያችን”ﷺ” ሸሪዓህ ግን ዘካቱል ማል ከካፒታል ላይ ከመቶ 2.5 % የሚሰጥ ነው፥ ነቢያችን”ﷺ” ከሁለት መቶ ዲርሀም 5% ዘካህ እንደሚወጣ ተናግረዋል። ያ ማለት የዘካህ ሒሳብ በመቶ ዲርሀም 5፥2=2.5 ይሆናል፦
2፥219 ”ምንን እንደሚመጸውቱም መጠኑን ይጠይቁሃል፡፡ «ትርፍን መጽውቱ» በላቸው”፡፡ እንደዚሁ ታስተነትኑ ዘንድ አላህ ለእናንተ አንቀጾችን ይገልጽላችኋል፡፡ وَيَسْأَلُونَكَ مَاذَا يُنفِقُونَ قُلِ الْعَفْوَ ۗ كَذَٰلِكَ يُبَيِّنُ اللَّهُ لَكُمُ الْآيَاتِ لَعَلَّكُمْ تَتَفَكَّرُونَ
ሡነን አቢ ዳውድ መጽሐፍ 9, ሐዲስ 18 ዐሊይ”ረ.ዐ” እንደተረከው፦ “ነቢዩም”ﷺ” እንዲህ አሉ፦ ”ሁለት መቶ ዲርሀም ለአንተ በሆነች ጊዜና ዓመት ከሞላች አምስት ደራሂም ይወጣል፥ በአንተ ምንም ነገር አይሆንም ሃያ ዲናር እስኪሆን ድረስ”። عَنْ عَلِيٍّ، – رضى الله عنه – عَنِ النَّبِيِّ صلى الله عليه وسلم بِبَعْضِ أَوَّلِ هَذَا الْحَدِيثِ قَالَ ‏”‏ فَإِذَا كَانَتْ لَكَ مِائَتَا دِرْهَمٍ وَحَالَ عَلَيْهَا الْحَوْلُ فَفِيهَا خَمْسَةُ دَرَاهِمَ وَلَيْسَ عَلَيْكَ شَىْءٌ – يَعْنِي فِي الذَّهَبِ – حَتَّى يَكُونَ لَكَ عِشْرُونَ دِينَارًا

“ፊጥር” فِطْر ማለት “ፆም መግደፊያ” ማለት ሲሆን የፊጥር ብዙ ቁጥር ደግሞ “ፉጡር” فُطُور ነው፥ የረመዷን ፆም ማብቂያ በዓል እራሱ “ዒዱል ፊጥር” عِيدُ ٱلْفِطْر ይባላል። “ዘካቱል ፊጥር” زَكَاة الفِطْر ደግሞ ለመሣኪን በዒዱል ፊጥር ቀን ለማስፈጠሪያነት የሚውል ገንዘብ ነው፥ “መሣኪን” مَسَاكِين ማለት የዕለት ጉርስ የዓመት ልብስ የሌላቸው “ነዳያን” ማለት ነው። “ለግው” لَّغْو ማለት “ውድቅ ንግግር” ማለት ሲሆን “ረፈስ” رَّفَث ማለት ደግሞ “ስሜት ቀስቃሽ ንግግር” ማለት ነው፥ ዘካቱል ፊጥር ለፆመኛ ውድቅ ንግግር እና ስሜት ቀስቃሽ ንግግር ማፅጃ እንዲሁ ለመሣኪን መብል ነው፦
ሡነን ኢብኑ ማጃህ መጽሐፍ 8, ሐዲስ 45
ኢብኑ ዐባሥ እንደተረከው፦ “የአሏህ መልእክተኛ”ﷺ” ዘካቱል ፊጥርን ለፆመኛ ለግው እና ረፈስ ማፅጃ እንዲሁ ለመሣኪን መብል እንዲሆን ግዴታ አድርገዋል”። عَنِ ابْنِ عَبَّاسٍ، قَالَ فَرَضَ رَسُولُ اللَّهِ ـ صلى الله عليه وسلم ـ زَكَاةَ الْفِطْرِ طُهْرَةً لِلصَّائِمِ مِنَ اللَّغْوِ وَالرَّفَثِ وَطُعْمَةً لِلْمَسَاكِينِ .‏

“ግዴታ አድርገዋል” ለሚለው የገባው የግስ መደብ “ፈረዶ” فَرَضَ መሆኑ በራሱ ዘካቱል ፊጥር ፈርድ መሆኑ ቁልጭ አድርጎ ያሳያል፥ “ፈርድ” فَرْض የሚለው ቃል እራሱ “ፈረዶ” فَرَضَ ማለትም “ግዴታ አደረገ” ከሚለው ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን “ግዴታ” ማለት ነው።

ዘካቱል ማል ከቤት ለተባረሩ ሠለምቴዎች መቋቋሚያ መስጠት ከፈለጋችሁ እና ዘካቱል ፊጥር ለመሣኪን ሠለምቴዎች ማስፈጠሪያ መስጠት ከፈለጋችሁ ከዚህ በታች ያሉትን አድሚናት አናግሩ፦
ወንድም አቡ ኑዓይም፦https://t.me/arhmanu
እኅት ሰላም፦ http://t.me/SeuweSe
አኅት ዘሃራ፦ https://t.me/Zhara_mustefa

ወጀዛኩሙላህ ኸይራ!

ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://t.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም

3 months, 3 weeks ago

ወደ ዲኑል ኢሥላም ስንመጣ "ዐቅመ ጋብቻ" ማለት አንድ ተባእት ለዐቅመ አደም ሲደርስ እና አንዲት እንስት ለዐቅመ ሐዋህ ስትደርስ ማለት ነው። ለምሳሌ፦ የቲሞች እራሳቸው ይችሉ ወይም አይችሉ እንደሆነ ይፈተናሉ፥ ይህም ፈተና ለጋብቻ እስከሚደርሱበት ድረስ ነው፦
4፥6 የቲሞችንም ጋብቻን እስከደረሱ ጊዜ ድረስ ፈትኑዋቸው፡፡ وَابْتَلُوا الْيَتَامَىٰ حَتَّىٰ إِذَا بَلَغُوا النِّكَاحَ

"ኢዛ"  إِذَا ማለት "ጊዜ" ማለት ሲሆን የጊዜ ተውሳከ ግሥ ሲሆን ጋብቻ የራሱ የሆነ ጊዜ እንዳለው አመላካች ነው፥ ይህም ጊዜ ለማመልከት "ጋብቻን እስከደረሱ" ድረስ በማለት ይናገራል። እዚህ አንቀጽ ላይ  "ጋብቻን እስከደረሱ" ለሚለው የገባው ቃል "በለጉ" بَلَغُوا ሲሆን "ለጋብቻ በሰሉ" ማለት ነው፥ "በለገ" بَلَغَ ማለት እራሱ "ለጋብቻ በሰለ" ማለት ሲሆን "በለገት" بَلَغَت ማለት ደግሞ "ለጋብቻ በሰለች" ማለት ነው። "ባሊግ" بَٰلِغ ማለት እራሱ "ዐቅመ ጋብቻ"Puberty" ማለት ነው፦
ተፍሢሩል ኢብኑ ከሲር 4፥6 "ጋብቻን እስከደረሱ ጊዜ" የሚለውን ሙጃሂድ፦ "ለዐቅመ ጋብቻ ነው" ብሏል፥ ዐበይት ምሁራን፦ "ለዐቅመ ጋብቻ" ለጋዎች "ኢሕቲላም" ሲኖራቸው ነው" ብለዋል። አቢ ዳውድ በሡናው እንደዘገበው፥ ዐሊይ ኢብኑ አቢ ጧሊብ"ረ.ዐ." እንደተረከው፦ "የአላህ መልእክተኛ”ﷺ” እንዲህ አሉ፦ "ከዐቅመ ጋብቻ በኃላ የቲምነት የለም"።
( حتى إذا بلغوا النكاح ) قال مجاهد : يعني : الحلم . قال الجمهور من العلماء : البلوغ في الغلام تارة يكون بالحلم ، وهو أن يرى في منامه ما ينزل به الماء الدافق الذي يكون منه الولد . وقد روى أبو داود في سننه عن أمير المؤمنين علي بن أبي طالب ، رضي الله عنه ، قال : حفظت من رسول الله صلى الله عليه وسلم : " لا يتم بعد احتلام
ሡነን አቢ ዳውድ መጽሐፍ 18, ሐዲስ 12
ዐሊይ ኢብኑ አቢ ጧሊብ እንደተረከው፦ "የአሏህ መልእክተኛ”ﷺ” እንዲህ አሉ፦ "ከዐቅመ ጋብቻ በኃላ የቲምነት የለም"።  قَالَ عَلِيُّ بْنُ أَبِي طَالِبٍ حَفِظْتُ عَنْ رَسُولِ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم ‏ "‏ لاَ يُتْمَ بَعْدَ احْتِلاَمٍ

"ዐቅመ ጋብቻ" አካል ተራክቦ ለማድረግ ሲበስል ነው፥ ከዐቅመ ጋብቻ በኃላ የቲምነት ስለሌለ የቲሞች እራሳቸው እንዲችሉ ይፈተናሉ። "ኢሕቲላም" احْتِلاَم ማለት አንድ ልጅ ወይም አንዲት ልጂት ተራክቦ ለማድረግ የሚኖራቸው ፈሳሽ ነው። አንድ ለጋ ሕጻን ለዐቅመ አደም ከደረሰ የሰው ቤት ዘው ብሎ አይገባም፥ ከዚያ ይልቅ አንኳክቶ ያስፈቅዳል፦
24፥59 ከእናንተም ሕፃናቶቹ "ዐቅመ አዳምን" በደረሱ ጊዜ እነዚያ ከእነርሱ በፊት የነበሩት እንዳስፈቀዱ ያስፈቅዱ፡፡ وَإِذَا بَلَغَ الْأَطْفَالُ مِنكُمُ الْحُلُمَ فَلْيَسْتَأْذِنُوا كَمَا اسْتَأْذَنَ الَّذِينَ مِن قَبْلِهِمْ

አሁን እዚህ አንቀጽ ላይ "ኢዛ"  إِذَا የሚለው የጊዜ ተውሳከ ግሥ የዐቅመ ጋብቻ ጊዜ አመላካች ነው፥ ይህንን ዐቅመ ጋብቻ ለማመልከት "ዐቅመ አዳም" ለሚለው ቃል "በለገ" بَلَغَ  የሚል የግሥ መደብ ይጠቀማል። አንዲት እንስት ለዐቅመ ሐዋህ ደረሰች የሚባለው አካሏ ለተራክቦ ዝግጁ ሲሆን የመድረሷ የመጀመሪያው እና ዐቢይ ምልክት ደግሞ ጡቷ ሲያጎጠጉጥ እና ብብቷና ብልቷ አካባቢ ጸጉር መብቀል ሲጀምር ነው። ይህ የምታመነጨው ፈሳሽ "ኢሕቲላም" احْتِلاَم ሲባል ትርጉሙ "ከረቤዛዊ ፈሳሽ"Vaginal lubrication" ነው፥ ይህ ፈሳሽ ከጨቅላነት ወደ ዐቅመ ሐዋህ የምትሸጋገርበት አካላዊ ሽግግር"physical transition" ምልክት ነው።
ይህንን ታሳቢ እና ዋቢ በማድረግ እናታችን ዓኢሻህ"ረ.ዐ." ለነቢያችን"ﷺ" የተዳረችው በስድስት ዓመቷ ሲሆን ለዐቅመ ሐዋህ እስክትደርስ ድረስ ለሦስት ዓመት ከተጠበቀ በኃላ በዘጠኝ ዓመቷ ወደ ነቢያችን"ﷺ" ቤት ገብታለች፦
ኢማም ሙሥሊም መጽሐፍ 16, ሐዲስ 82
ዓኢሻህ እንደተረከችው፦ "ነቢዩ"ﷺ" ሲያገቡኝ የስድስት ዓመት እንስት ነበርኩኝ፥ የዘጠኝ ዓመት እንስት ስሆን ወደ ቤቱ ገባሁኝ"። عَنْ عَائِشَةَ، قَالَتْ تَزَوَّجَنِي النَّبِيُّ صلى الله عليه وسلم وَأَنَا بِنْتُ سِتِّ سِنِينَ وَبَنَى بِي وَأَنَا بِنْتُ تِسْعِ سِنِينَ
ኢማም ቡኻርይ መጽሐፍ 67, ሐዲስ 69
ዓኢሻህ"ረ.ዐ." እንደተረከችው፦ "ነቢዩ"ﷺ" ሲያገቧ የስድስት ዓመት ነበረች፥ የዘጠኝ ዓመት እንስት ሲሆናት ደረሱባት"። عَنْ عَائِشَةَ ـ رضى الله عنها ـ أَنَّ النَّبِيَّ صلى الله عليه وسلم تَزَوَّجَهَا وَهْىَ بِنْتُ سِتِّ سِنِينَ

በስድስት ዓመቷ ተድራ ሦስት ዓመት የመቆየቷ ጉዳይ ለዐቅመ ሐዋህ እስክትደርስ ድረስ ነው፥ "በስድስት ዓመቷ ተድራ በዘጠኝ ዓመቷ ለምን ተራከበች" ብለህ እርር እና ምርር የምትል ከሆነ እንግዲያውስ ይስሐቅ ርብቃን በሦስት ዓመቷ ማግባቱን እና በስድስት ዓመቷ ተራክቦ ማድረጉን ስትሰማ ልትንጨረጨር እና ልትንተከተክ ይገባክ ነበር። የምጣዱ እያለ የዕንቅቡ ተንጣጣ ይሉካል እንደዚህ ነው፥ ወይም ቅቤ አንጣሪዋ እያለች ጎመን ቀንጣሿ ምች መታት ይሉካል እንደዚህ ነው። በነገራችን ላይ ጥንታዊ ዘመን"classical age" ላይ የነበሩትን ባህል፣ ወግ፣ ልማድ፣ ትውፊት በድኅረ ዘመናዊ ዘመን"postmodern age" ባህል፣ ወግ፣ ልማድ፣ ትውፊት መመዘን ከሥነ አመክንዮ አንጻር ታሪካዊ ሕፀፅ"historical fallacy" ነው። አምላካችን አሏህ ሂዳያህ ይስጣችሁ! ለእኛም ጽናቱን ይስጠን! አሚን።

ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://t.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም

3 months, 3 weeks ago

የርብቃ ጋብቻ

በአሏህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው።

4፥6 የቲሞችንም ጋብቻን እስከደረሱ ጊዜ ድረስ ፈትኑዋቸው፡፡ وَابْتَلُوا الْيَتَامَىٰ حَتَّىٰ إِذَا بَلَغُوا النِّكَاحَ

እንደ ዘፍጥረት ዘገባ አብርሃም ልጁ ይስሐቅን ሊሠዋ እንደነበር ተዘግቧል። በዚያን ይስሐቅ የሠላሳ ስድስት ዓመት ልጅ እንደነበር በታርገም ዮናታን ተዘግቧል፦
ታርገም ዮናታን ዘፍጥረት 22፥1 ይስሐቅም እንዲህ ሲል መለሰ፦ "እነሆ፥ ዛሬ የሠላሳ ስድስት ዓመት ልጅ ነኝ"። ויען יצחק: "הנה אני בן שלושים ושש שנה היום".

ምሁራን ይስሐቅ በሞርያ ተራራ ሠላሳ ስድስት ዓመት ከመንፈቅ ስላለፈ ሠላሳ ሰባት ዓመቱ እንደነበር ይዘግባሉ፦
ራሺ ዘፍጥረት 25፥20 "አብርሃም ከሞሪያ ተራራ በመጣ ጊዜ ርብቃ መወለዱን ሰምቷልና፥ በዚያ ጊዜ ይስሐቅ የሠላሳ ሰባት ዓመት ልጅ ነበር። ምክንያቱም በዚያን ጊዜ ሣራ ስለሞተች። שֶׁהֲרֵי כְּשֶׁבָּא אַבְרָהָם מֵהַר הַמּוֹרִיָּה נִתְבַּשֵּׂר שֶׁנּוֹלְדָה רִבְקָה, וְיִצְחָק הָיָה בֶּן ל"ז שָׁנָה, שֶׁהֲרֵי בּוֹ בַּפֶּרֶק מֵתָה שָׂרָה, וּמִשֶּׁנּוֹלַד יִצְחָק עַד הָעֲקֵדָה שֶׁמֵּתָה שָׂרָה, ל"ז שָׁנָה הָיוּ

"ይህም ከሆነ በኋላ" ማለትም "ይስሐቅ ሊሠዋ ከሆነ በኃላ" ለአብርሃም ሚልካ ለወንድሙ ለናኮር ልጆችን ወለደች፦
ዘፍጥረት 22፥20 ይህም ከሆነ በኋላ ለአብርሃም እንዲህ ተብሎ ተነገረ፦ “እነሆ፥ ሚልካ ደግሞ ለወንድምህ ለናኮር ልጆችን ወለደች።

ሚልካ የናኮር ሚስት ስትሆን የአብርሃም ወንድም ናኮር ዑፅ፣ ቡዝ፣ ቀሙኤል፣ ኮዛት፥ ሐዞ፣ ፊልዳሥ፣ የድላፍ፣ እና ባቱኤል የሚባሉ ስምንት ልጆችን ወለደች፦
ዘፍጥረት 22፥21-22 እነርሱም በኵሩ ዑፅ፥ ወንድሙ ቡዝ፥ የአራም አባት ቀሙኤል፥ ኮዛት፥ ሐዞ፥ ፊልዳሥ፥ የድላፍ፥ ባቱኤል ናቸው።

ባቱኤል የናኮር የመጨረሻ ልጅ ሲሆን ባቱኤል ደግሞ ርብቃን ወለደ፦
ዘፍጥረት 22፥23 ባቱኤልም ርብቃን ወለደ።

በትንሹ ይስሐቅ ርብቃን በሠላሳ ሰባት ዓመት ይበልጣታል፥ ይስሐቅ አርባ ዓመት ሲሆነው ርብቃን አገባ፦
ዘፍጥረት 25፥20 ይስሐቅም አርባ ዓመት ሲሆነው ርብቃን አገባ።

ይስሐቅ ርብቃን ሲያገባት የሦስትት ዓመት ልጅ ነበረች፥ ምክንያቱም 40-37=3 ይሆናልና። ከጋብቻ በኃላ ይስሐቅ ከርብቃ ጋር በተራክቦ ለመራከብ የነበረው የጊዜ ክፍተት ሦስት ዓመት እንደነበር በራሺ ዘፍጥረት ላይ እንዲህ ተዘግቧል፦
ራሺ ዘፍጥረት 25፥20 "ለጋብቻ ብቁ እስክትሆን ድረስ ሦስት ዓመት ጠበቀ፥ ከዚያም ደረሰባት። הִמְתִּין לָהּ עַד שֶׁתְּהֵא רְאוּיָה לְבִיאָה ג' שָׁנִים וּנְשָׂאָהּ:

ስለዚህ የሦስት ዓመት ልጅ ለአርባ ዓመት ሰው መዳር በጥንት ጊዜ የተለመደ ጉዳይ መሆኑ ይህ ታሪክ ጉልኅ ማሳያ ነው። እንደ ታሪኩማ ይስሐቅ በተራክቦ ሲራከባት ርብቃ መካን ነበረችና ይስሐቅም ስለሚስቱ ወደ አምላክ ጸለየ፥ አምላክም ስለተለመነው ርብቃም ሚስቱ ፀነሰች፦
ዘፍጥረት 25፥21 ይስሐቅም ስለሚስቱ ወደ ያህዌህ ጸለየ፥ መካን ነበረችና ያህዌህም ተለመነው፥ ርብቃም ሚስቱ ፀነሰች።

5 months, 3 weeks ago

"ኤሎሂም" በሚል ትምህርት ተለቋል። "ኤሎሂም" ማለት ትርጉሙ "አማልክት" ማለት ሲሆን ፈጣሪ “ኤሎሂም” ሲባል ምን ማለት ነው? "አማልክት" የተባሉት ሥላሴ ከሆኑ ሥላሴ አማልክት ናቸው? እነዚህ የመሳሰሉ እሳቦት ዳሰሳ አድርገናልና ትምህርቱን በጥሞና እና በቅጡ ያድምጡና ያስደምጡ፦ https://youtu.be/DYDqQqemDFk?si=qYY0t9HgIv-F0cvi

ሌሎቻችሁ ሼር አርጉት!

We recommend to visit

ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ

Last updated 1 month, 3 weeks ago

ለማንኛውም አስተያየት እና ጥቆማ 👉 @Esat_tv_comment_bot

🇪🇹ኢሳት የኢትዮጵያ አይን እና ጆሮ🇪🇹

Last updated 4 days, 5 hours ago

በዚህ ቻናል ሀገራዊና አለምአቀፋዊ መረጃዎችን በፍጥነት ያገኛሉ❗
የውስጥ መስመር👉http://t.me/ayulaw

Last updated 3 weeks, 2 days ago