ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።
@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna
#ኢትዮጵያ
Last updated 2 months, 3 weeks ago
Last updated 2 months, 2 weeks ago
ይህ ስለ Manchester United መረጃዎችን የሚያገኙበት የ Telegram ቻናል ነው 🇪🇹
--------------------------------------------------------------
☞︎| ስለ ማንቸስተር ዩናይትድ ትኩስ መረጃዎች
☞| ቀጥታ ስርጭቶች ከየስታድየሞቹ
☞| የዝውውር ዜናዎች
☞| ስለ ማንችስተር ዩናይትድ ታሪኮች
📩 ለማስታወቂያ ስራ DM :- @Marcoabdu
Last updated 1 month, 2 weeks ago
ጥቂት የመጽሐፍ ቅዱስ ሰዎች
ሁ?ከተሰኘው
✍አባታችን አብርሃም ኑሮውን ከእግዚአብሔር ጋር ማድረግ የጀመረው አገሩንና ቤተ ሰዎቹን በተወ ጊዜ ነበር፡፡ አባቶቻችን ሐዋርያት ተመሳሳይ ነገር ነው ያደረጉት፡፡ እነርሱ ሲጠሩ ዓሣ አጥማጆች ሆነው ሳሉ የተዉት መረቦቻቸውንና ታንኳዎቻቸውን ብቻ ሳይሆን ተከትለውትም ሄደዋል፤ማቴ 4፡20እና22፡፡ ቅዱስ ጴጥሮስ እንደ ተናገረው ከሆነማ ያላቸውን ነገር ሁሉ ትተው ነው የከተሉት፤ ማቴ 19፡27፡፡ እናንተስ? ስለ እግዚአብሔር ስትሉ የተዋችሁት ነገር ምንድር ነው? እናንተ ኃጢአተኛ ሕይወታችሁን በመተው ንስሐ ገብታችኋል?...
ያዕቆብመልእክት
ከተሰኘው
‹ብዙ ሰዎች እኔን በሀብታም ሰዎች ላይ ያለህ አቋም በጣም ጥብቅ ነው እያሉ ይናገሩኛል፡፡ በእርግጥም እንዲህ በማለታችሁ እውነት ብላችኋል፤ይሁን እንጂ እኔ በሀብታም ሰዎች ላይ ጥብቅ የሆንኩት ገንዘባቸውን ለመሳደቢያ አድርገው ለተጠቀሙበት ሀብታሞች ነው፡፡ እኔ እነርሱን የማጠቃቸው በግል አይደለም፤ነገር ግን የማጠቃው ስስታቸውን ነው፡፡ ........
✥••┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈••✥
...በተለይ በተለይ በትርጉም ስራ ረገድ ለኛ [ለኢትዮጵያውያን ] አባት ልጁን ለመመገብ እንደሚጨነቅ እና እንደሚፋጠን ኹሉ በልዩ እና በተረዳ እንዲሁም በማይጠገብ መልኩ የሚያዘጋጁልን ፦
#አያሌው ዘኢየሱስን ያቆይልን እያልን ፦
💥አሁንም እነዚህን ሁለት ግሩማን፤ ሐሳቦችን የተሞሉ ፤መጻሕፍት እነኾ ያሉን ሲሆን በግዮን መጻሕፍት ያገኟቸዋል ።
*👇ይህ የ fece book ገጻችን ነው ይቀላቀሉን !* https://www.facebook.com/share/15vnjyrzBv/
ለ Telegram በዚህ ይጎብኙን
http://t.me/GhionBookStore1623
ዜና ድጋሚ ኅትመት !
ሳይንስ እና ሃይማኖት
..✍ሳይንስ የሰው ልጅ ከእግዚአብሔር የተሰጠውን አዕምሮ ተጠቅሞ ያስገኘውና በዚህ ዓለም ያለውን የኑሮ ድካም ማቅለያው የዕውቀት ዘርፍ ሲሆን ሃይማኖት ደግሞ ከአምላኩ ከእግዚአብሔር ጋር የሚያገናኘው መንገድ ነው። ነገር ግን የሳይንስን ውሱንነት ያልተረዱ ሰዎች ሃይማኖትን በሳይንሳዊ ዕውቀት ለመተንተን ሲሞክሩና ወደ ተሳሳተ ግንዛቤ ሲያመሩ ይስተዋላል። በሌላ መልኩ ደግሞ ሳይንስ ለመንፈሳዊ ሰዎች እርባና የሌለው ነው ብለው የሚያምኑም አሉ።
ይህንን በተመለከተ ለሚነሱ ጥያቄዎችና ፍልስፍናዊ አስተያየቶች፣ ጸሐፊው መምህር ያረጋል አበጋዝ፣ በዚህ መጽሐፉ ከሳይንስና ከሃይማኖት ጋር በተገናኙ ፍልስፍናዊ አስተሳሰቦች ዙሪያ ሰፊ ጥናት በማድረግ ከጥልቅ ትንታኔ ጋር አቅርቦልናል። ስለሆነም መጽሐፉን አንብበን የተሻለ ግንዛቤ እንድናገኝና እንድንጠቀምበት እየጠየቅኩ፣ ለመምህር ያረጋል ዕድሜና ጤናን ለእናንተ ለአንባብያን ደግሞ መልካም ንባብ እንዲሆንላችሁ እመኛለሁ።
ቀሲስ ሰሙ ምትኩ (ፕሮፌሰር)
ቦትስዋና የሳይንስና ቴክኖሎጂ ኢንተርናሽናል ዩኒቨርሲቲ
ይህ መንፈሳዊ እና ሳይንሳዊ እሳቤዎችን የተነተነ በግሩማን ሐሳቦች የታጨቀው [የተሞላው] በመምህረ ቤተክርስትያን ዲያቆን ያረጋል አበጋዝ የቀረበ ጥዑም ማዕድ[መጽሐፍ ] ለ ሁለተኛ ጊዜ የታተመ ሲሆን በግዮን መጻሕፍት ዘወትር በልዩ ቅናሽ ያገኙታል።
# ግዮን መጻሕፍት ለመላው ከሀገር ውጪ እና ሀገር ውስጥ ለምትገኙ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲሁም የ Delivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን።
ይደውሉልን !📞፦0913083816
፦0912198891
https://t.me/GhionBookStore1623
በዚህ መጽሐፍ የተካተቱት ዓሥር ድርሳናት፥ ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ በ386 እና በ387 ዓ.ም. በአንጾኪያ ያስተማራቸው ሲኾኑ፥
👉 ኃጥአንም ጻድቃንም ንስሓ እንደሚያሻቸው እግዚአብሔር ለሰው ልጆች ካለው ወደር የለሽ ፍቅሩ የተነሣ አንድ ዓይነት የንስሓ መንገድ እንዳልሰጠ፣
👉 በዚህ የቅድስት ቤተ ክርስቲያን ዓምድ ትምህርት በኾነው በንስሓ አማካኝነት ኃጥአን ያሳደፉትን ልጅነታቸውን የሚያድሱበትና ሕይወት ወደ ኾነው ወደ ቅዱስ ቁርባን የሚመልሳቸው መንገድ መኾኑን፣
👉 ወደ ቅዱስ ቁርባን መድረሻ መንገድ ብቻ ሳይኾን ከላይ እንደ ተገለጠው በተለያየ መንገድ ማለትም በጸጸት፥ በምጽዋት፣ በጸሎት፣ በፆም፥ በትሕትና፥ ቅዳሴውንና አጠቃላይ የቤተ ክርስቲያን ሥርዓተ አምልኮን በመሳተፍ፥ በአጠቃላይ ምግባር ትሩፋትን በመሥራት ያሸበረቀ ቤተ ክርስቲያናዊ ሕይወትን በመኖር የሚገለጥ ምሥጢር መኾኑን፣
👉 የአምላክን መጠን አለፍ ቸርነት ስጦታ መኾኑን ከብዙ ማሳያዎች ጋር ያስተማረባቸው ናቸው፡፡
መጽሐፉ በ200 ገጾች፣ በሚማርክ ኅትመትና በ300 ብር የሽፋን ዋጋ ለሦስተኛ ጊዜ ታትሞ ለአንባቢያን ቀርቧል።
____
በግዮን መጻሕፍት መደብር ዘወትር በልዩ ቅናሽ ያገኙታል።
ለበለጠ መረጃ በ0913083816 ይደውሉ።
"የክርስቶስ ቤዛነት ይህ ነው፦ እርሱ ስለተሸከማቸው ዘግናኝ ሕማሞች እና ኃጢኣቶች እስካሁን ድረስ ያለማቋረጥ ይናገራል። ኃጢኣት የማያውቀውን እርሱን እግዚአብሔር አብ ስለእኛ ሲል 'ኃጢኣት እንዲሆን' አደረገው። አመንዝራው፣ ስድ ሆኖ የሚበድለው፣ ቆሻሻ በሆኑ ተግባራት አረንቋ ውስጥ የሚዛቅጠው እና ኃፍረት አልባ በሆኑ ተግባራት የሚበላሸው ሁሉ ከክርስቶስ ሲሸሽ ድምጹ በኋላው ይከተለዋል። ይኸውም 'የተወደድህ ልጅ ሆይ፥ ና! ኃጢኣቶችህ ከእኔ ጋር ናቸው፤' እያለ የሚጣራ የእግዚአብሔር ልጅ ደም ነው! ገና የሠራሃቸው ዕለት ነው በምልዓት የተሸከምኳቸው። ካሣውን ከፍያለሁ፦ ሐፍረት ተጭኖብኛል፤ ተገርፌያለሁ፤ ደቅቄያለሁ፤ ተሰቅያለሁ፤ እንዲሁም መርገምን ተሸክሜያለሁ። ለአንተ የይቅርታ እና የንጽሕና ተግባራትን እንዲሁም ይገባኛል የምትልበትን ጸጋ አዘጋጅቼልሃለሁ። ና! ለአንተ መከራ የተቀበልኩትን ያህል በአንተ ደስ ይለኝ ዘንድ ና! የመዳንን ዘውድ እደፋልህ ዘንድ፣ ፍቅሬን እና መንፈስ ቅዱስን በአንተ ላይ አፈስስ ዘንድ፣ እንዲህ አድርጌ ወደ አባቴ አቀርብህ ዘንድ ና! አንተ ከበጎቼ ሁሉ እጅግ ውዱ ነህ፤ እኔ ደሜን እስከመክፈል ደርሼ ከፍ ያለ ዋጋ ሰጥቼሃለሁና።"
የክርስቶስ ስሞች፣ ገጽ 135-36።
ይህን ምሥጢር የሆነ መሐፍ እንድታነቡት ግብዣችን ነው።
በግዮን መጻሕፍት መደብር ታገኙታላችሁ።
“ኃጢአቷን የቀበረችው ማርያም” መጽሐፍ በድጋሚ ታተመ
-በመ/ር ሥሙር አላምረው የተዘጋጀው “ኃጢአቷን የቀበረችው ማርያም” የተሰኘ መጽሐፍ ጌታን ሽቶ ስለቀቡት ማርያም ኀጥእት ብዙ ኃጢአቷን ቀብራ ብዙ ጸጋ ስላገኘችውና ማርያም እኀተ አልዓዛር ልዩነት ያስረዳል፡፡ መምህሩ “ከዚኽ በኋላ ጌታችንን ሽቱ የቀቡት ሴቶች እንዴት ሥስት ናቸው ተባለ የጋራ የቤት ሥራ ይኾነናል እንጅ አንዲት ሴት ብቻ ቀባችው ብለን የጨለማ ገልማጭ አንኾንም” ይሉናል፡፡
የመጽሐፉ አላማዎች
1) በእኅተ አልአዛር ማርያም ስም ማርያም ኃጥእት ተሠውራ እንዳትቀር ማድረግ
2)ስለ ባለሽቱ ሴቶች የግብጽ ቤ/ንና ሌሎች ተቋማት ምን አይነት ትምህርት እንዳላቸው ማሳየት
3)የተለያዩ የሊቃውንት ትርጓሜ ስለ ኃጢአተኛዋ ማርያም ምን እንደሚሉ ማስረዳት
4) የማርያም ኀጥእትን ገድል መሠረት በማድረግ የንስሐ ለቅሶዋን፣ ያጋጠማትን ፈተና እንዲሁም ገድሉ ያሉበትን የስምና የታሪክ ቅደም ተከተል ዝንፈትን መጠቆም፡፡
5)መጽሐፈ ስንክሳር የካቲት 6 የእኅተ አልዓዛር መታሰቢያ እንዳልሆነና የማርያም ዘሀገረ ናይን መታሰቢያ እንደሆነ ማስረዳት
-የደራሲያን መጻሕፍት በመግዛትና በማንበብ እናበረታታ እንደግፍ፡፡
መጽሐፉን ቅዳሜ በግዮን መጻሕፍት መደብር ታገኙታላችሁ።
“ቃልኪዳን በነገረ ድኅነት” (በዲ/ን ያረጋል አበጋዝ)
ቆየት ካሉ ነገር ግን እንደ መጽሐፉ ብስለት ብዙዎች እጅ ካልገቡ፣ በጥልቅ ትንታኔ ከተዘጋጁ መጻሕፍት አንዱ የዲ/ን ያረጋል አበጋዝ “ቃል ኪዳን በነገረ ድኅነት” በሚል ርእስ የተዘጋጀው መጽሐፍ ነው፡፡ ይህን መጽሐፍ ያነበቡ አንባቢያን ትልቅ መንፈሳዊ መረዳትን ስለሚጠይቀው ስለ ቃል ኪዳንና ነገረ ድኀነት በቂ ግንዛቤ አግኝተውበት እምነታቸውን በማጽናት ከክርስቶስና ከቅዱሳን ጋር ተጣብቀው በምድር ሰማያውያንን መላእክትን መስለው ተዋሕዶዊ አኗኗርን ገንዘብ አድርገው ተመላልሰውበታል፡፡ ይህ መጽሐፍ ቅዱሳን ከአምላካቸው ጋር ያደረጉትን ቃልኪዳንና በተሰጣቸው ቃል ኪዳን እኛ እንዴት መጠቀም እንዳለብን የሚተነትን ብቻ ሳይሆን፣ ነገረ ድኅነትን ተተርሰው ለሚነሡ ጥያቄዎች መልስ የሚሰጥ፣ ተግባራዊ ምልልሳችን በክርስትና ሕይወታችን ውስጥ ያለውን ፋይዳ፣ ስለንስሐና ሒደቶቹም በቂ ግንዛቤ እንዲኖረን ያበቃናል፡፡ መጽሐፉ በሰባት ምዕራፎች የተከፈለና በ188 ገጾች ተሰንዶ ለአንባቢያን በሚመች መልኩ የተዘጋጀ ግሩም መጽሐፍ ነው፡፡ ገዝታችሁ አንብቡት ትጠቀሙበታላችሁ፡፡
የተወሰነ ቅጅዎች ስላሉን በግዮን መጻሐፍት መደብር ታገኙታላችሁ።
ቅድስት ቤተ-ክርስቲያን አምጣ የወለደችው የመምህረ ወንጌል የዲ/ን ያረጋል አበጋዝ የተወሰኑ የመጽሐፍ
ቅጂዎች ስላሉን ማግኝት ትችላላችሁ።
በግዮን መጽሐፍ መደብር ደርዛቸውን የጠበቁ ነባርና አዳዲስ መጽሐፍቶችን ያገኛሉ። ለበለጠ መረጃ
በ0913083816/0931144330
"የክርስቶስ ቤዛነት ይህ ነው፦ እርሱ ስለተሸከማቸው ዘግናኝ ሕማሞች እና ኃጢኣቶች እስካሁን ድረስ ያለማቋረጥ ይናገራል። ኃጢኣት የማያውቀውን እርሱን እግዚአብሔር አብ ስለእኛ ሲል 'ኃጢኣት እንዲሆን' አደረገው። አመንዝራው፣ ስድ ሆኖ የሚበድለው፣ ቆሻሻ በሆኑ ተግባራት አረንቋ ውስጥ የሚዛቅጠው እና ኃፍረት አልባ በሆኑ ተግባራት የሚበላሸው ሁሉ ከክርስቶስ ሲሸሽ ድምጹ በኋላው ይከተለዋል። ይኸውም 'የተወደድህ ልጅ ሆይ፥ ና! ኃጢኣቶችህ ከእኔ ጋር ናቸው፤' እያለ የሚጣራ የእግዚአብሔር ልጅ ደም ነው! ገና የሠራሃቸው ዕለት ነው በምልዓት የተሸከምኳቸው። ካሣውን ከፍያለሁ፦ ሐፍረት ተጭኖብኛል፤ ተገርፌያለሁ፤ ደቅቄያለሁ፤ ተሰቅያለሁ፤ እንዲሁም መርገምን ተሸክሜያለሁ። ለአንተ የይቅርታ እና የንጽሕና ተግባራትን እንዲሁም ይገባኛል የምትልበትን ጸጋ አዘጋጅቼልሃለሁ። ና! ለአንተ መከራ የተቀበልኩትን ያህል በአንተ ደስ ይለኝ ዘንድ ና! የመዳንን ዘውድ እደፋልህ ዘንድ፣ ፍቅሬን እና መንፈስ ቅዱስን በአንተ ላይ አፈስስ ዘንድ፣ እንዲህ አድርጌ ወደ አባቴ አቀርብህ ዘንድ ና! አንተ ከበጎቼ ሁሉ እጅግ ውዱ ነህ፤ እኔ ደሜን እስከመክፈል ደርሼ ከፍ ያለ ዋጋ ሰጥቼሃለሁና።"
የክርስቶስ ስሞች፣ ገጽ 135-36።
የዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ የኤፌሶን ወንዝ መጽሐፍ
ነገ ቅዳሜ በግዮን መጻሕፍት ታገኙታላችሁ።
ሙሉ ገቢው ለግሸን ደብረ ከርቤ ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስትያን ሕንፃ ቤተ መቅደስ እድሳት የሚውል።
በግዮን መጻሕፍት መደብር ነባር እና አዳዲስ መጽሐፍቶችን ዘወትር በልዩ ቅናሽ ያገኛሉ።
እጻጻፋም እንደ ዮሐንሰ ስብከት ፊት ለፊት ነው፡፡ አለማወቅን ሲገስጽ እንደ ዮሐንስ ሰብከት ምሳሩን እያሳየ ነው ድንቁርና ጨለማን ሊያርቅም ዮሐንሰን ችቦ አድርጎ እያሰራ ነው። ከኃጢኦት አረገቋ ሲያጥብም በዮሐንስ የጥምቀትና የትምህርት ባሕር እየዘፈቀ ነው፡፡ ዮሐንሰን መውደድ ማን መውደድ መሆኑ ግልጽ ነው።ከእርሱ መጀከሮም በማን ለመጨረስ መሆኑ የታወቀ ነው ።በእርሱ መደነቅም በእርሱ ጌታ በክርስቶስ ቀርቶ በዮሐንስም ለመደመም እንኳ አቅመ ቢሰ መሆናችንን ለማሳየት መሆኑም የተገለጠ ነው ጌታ ስለዮሐንሰ እርሱ እውነት መስክሮአል እንዳለ ይህ መጽሐፍም፡- ቤተ ክርስቲያን ስለዮሓንስ የያዘችውን እውነት ግልጽ አድርጎ ያወጣ አዘጋጁን አባታችንም የእውነት መሰክር የሚያሰኝ ነው። እንዲያውም ቅዱስ ያሬድ ስለቅዱስ ዮሐንስ ውነቱ አነነ ኣብል በእንተ የተስሰ እና ከርስ እው እግዚኡ እእመረ፣ በዕለት ጥሉ አንደረት ነፍሱ ዲበ ምድር እንዳለው ስለዚህ መጽሐፍ ጠቀሜታ እኔም ብዙ ላለመናገር ብመርጥ መልካም ሳይሆን አይቀርም። በርግጥ መጽሐፉ አባታችንም የቅዱስ ያሬድ ልጅ መሆናቸውን የሚመሰከር ንዜኑ ንዜኑ የሚል መጽሐፍ መሆኑን ላለመመስከር ልላቀቅ አልችልም። ጌታን የሚያገኝ ዮሐንስ ቀድሞ ያስፈልገዋልና : አባታችንም ቀድመው ዮሐንሰ ይዘው ሰለመጡ የጌታን ነገር ሊያስከትሉ ነው ብዬ እንድገምት ማድረጉንም ልደብቅ እልችልም፡፡ እንግዲያውስ አንደ እነርሱ እመጣጥ ከስድስት ወር ልዩነት ሳያሰበልጡ ቶሎ ይዘውልን ይምጡ እያልኩ መማጸኔን ማሳወቅ ከፉ እልመሰለኝም።
ዲያቆን ብርሃኑ አድማሰ
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።
@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna
#ኢትዮጵያ
Last updated 2 months, 3 weeks ago
Last updated 2 months, 2 weeks ago
ይህ ስለ Manchester United መረጃዎችን የሚያገኙበት የ Telegram ቻናል ነው 🇪🇹
--------------------------------------------------------------
☞︎| ስለ ማንቸስተር ዩናይትድ ትኩስ መረጃዎች
☞| ቀጥታ ስርጭቶች ከየስታድየሞቹ
☞| የዝውውር ዜናዎች
☞| ስለ ማንችስተር ዩናይትድ ታሪኮች
📩 ለማስታወቂያ ስራ DM :- @Marcoabdu
Last updated 1 month, 2 weeks ago