የልቤ ድርሰት የብዕር ጠብታ

Description
Well come😊
✍️ትኩረት ነጥቦች
፩ ፦ግጥም ፪፦ድርሰት ፫፦ፍልስፍና
፬፦ስዕል ፭፦ሙዚቃ ፮፦ስሜት ፯፦ፎቶ
✍️አላማ
~> በዚህ ቻናል አዳማጭ ያጡ ልቦችን እናንኳኳለን ከዝምታው አለም እንዲወጡ ፣ የልባቸውን ድርሰት የብዕራቸዉን ጠብታ እንዲያጋሩ ፣ የዉስጥ እረፍት እንዲያገኙ እና ወደ ወደፊት ህልማቸው አንድ እርምጃ እንዲጠጉ ማድረግ ነው። inbox @amanytz

የሁሉም ሰው ልብ ደራሲ ነው!!❤️
We recommend to visit

ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ

Last updated 4 months, 1 week ago

Last updated 4 months ago

ይህ ስለ Manchester United መረጃዎችን የሚያገኙበት የ Telegram ቻናል ነው 🇪🇹
--------------------------------------------------------------
☞︎| ስለ ማንቸስተር ዩናይትድ ትኩስ መረጃዎች
☞| ቀጥታ ስርጭቶች ከየስታድየሞቹ
☞| የዝውውር ዜናዎች
☞| ስለ ማንችስተር ዩናይትድ ታሪኮች

📩 ለማስታወቂያ ስራ DM :- @Marcoabdu

Last updated 3 months ago

3 months ago
.

.
.
ከስድስት ወር በላይ ጣቶቼ እርሳስና ወረቀትን ሳያስማሙ ከርመው ነበር። ናፍቆታቸውም እንዲህ በዕለተ ሮቡ ተወግቷል!
ታዲያ🙄 ሳለኝ እያላቹህ ፎቶ ለምትልኩ ሰዎች ማለት እምፈልገው.. "ሞኛቹህን ፈልጉ እኔ Hustle ላይ ነኝ See You in Next ላይፍ!!"😁😇

ባለፈው Free Package ሰጥቼ ነበር። ድጋሚ ቢያንስ ለ10 ሰዎች ለመስጠት አስቢያለሁ..!
መቼ🙄?
ቀኑን አንድ ቀን አሳውቃቹሃለው!🤓

don't forget to rate⭐️

✍️Aman😑 YTZ
@amanytz

join and share
@YelbeDrset
@YelbeDrset

inbox me @amanytz
✍️✍️✍️✍️✍️✍️

3 months, 1 week ago

#እናት_ዋ_ጎንደር!

"ጎንደር" ስሙ በራሱ ሲነሳ ሰውነት ይወራል.. ከሰሞነኛ የኮሪደር ልማት ላይ የምትገኘው ጎንደርን በየሚዲያው እከታተላለሁ። የተሰሩት ስራች እጅግ ደስ ይላሉ። የጎንደር ማህበረሰብም ደስተኛ ይመስለኛል። ታዲያ ምን ለማለት ፈልጌ ነው? ከተሰሩት ስራዎች ውስጥ "የፋሲል ግንብን" ሳይ ከላዩ ላይ የነበሩ የነገስታት፣ የጦረኞችና የአገልጋዬች መንፈስ የተነሳ ይመስላል..የሆነ ነብስ የሌለው ቅርፅ ብቻ የሆነ ያህል ተሰማኝ..

ምስሉን እያየሁ ግቢው ወደተመሰረተበት 1628 ዓ.ም በሐሳብ ሄዱክ.. ያኔ ሲገነባ እንዲህ አይነት መልክ ነበረው ይሆን..? አሁን የምናየው የታደሰው የፋሲል ግንብ ያ በአፄ ፋሲለደስና ከርሳቸው ቀጥለው በመጡ ነገስት የተሰራው ፋሲል ግንብ ነው ማለት ይቻላል?? ይሄ አንድ የፍልስፍና መጽሐፍ ላይ ያነበብኩትን ሐሳብ ይመስላል.. ሐሳቡ እንዲህ ይላል('ባጭሩ)፦ "አንዲት ሰው ሁሉ እሚያውቃ "የቴሰስ መርከብ" ነበረች። ታዲያ ይቺ መርከብ ያረጀች ነበርች በመሆኑም መንገድ ላይ እያለች አሮጌውን ባህሩ ላይ እየጣሉ የሚታደሰውን እያደሱ እያንዳንዱ የመርከቧ ክፍል ተስተካክሎ ወደ ሐገር ተመለሱ.. ገና በባህር ላይ ከሩቅ ሰውች አይተው "የቴሰስ መርከብ" መጣች ብለው ወደ ወደቡ ተጠጉ ግን መርከቧ ከወደቡ ደርሳ መልሕቋን ስትጥል ሰዎች ሊያውቋት አልቻሉም ምክኒያቱም ተቀይራለች..በውስጧ የሚያውቋቸውን ሰዎች ብትይዝም ስትሄድ ያዩዋት መርከብ አደለችም..!!

1ኛ፦ ይቺ የቴሰስ መርከብ ናት ማለት ይቻላል??
2ኛ፦ ስትቀየር የተጣሉትና የታደሱት ክፍሎቿ ከባህር ላይ ቢሰበሰቡ አንድ መርከብ ይሰራሉ ታዲያ ሁሉት ሆኑ ማለት አደል የትኛዋስ የቴሰስ መርከብ ትባላለች?
3ኛ፦ ስትታደስ ምን አልባት ሳቀየር የቀረ የሆነ ጣውላ ይኖራል ስለዚህ ያልተቀየረ ክፍል ስላላት ይቺ የቴሰስ መርክብ ናት ማለት ይቻላል??

እና ምን ለማለት ነው አንባቢ ሆይ!
ይሄ ፋሲል ግንብ አዲሱ ፋሲል ግንብ ነው ወይስ ታሪካዊው ቅርስ ነገስታት የዳሰሱት..የእጃቸው ወዝ ያረፈበት.. ጀግኖች የተሰበሰቡበት.. ሊቆች የተቀኙበት..ወይዛዝርቶች ሽርጉድ ያሉበት.. በዳይና ተበዳይ የተዳኙበት.......... አፄ ቴዎድሮስ ኢትዮጵያን ከፍ አድርገው ያዩበት...ያ ፋሲል ግንብ ነው??

መልሱን ለናንተ ተውኩ!🙏

እናትዋ ጎንደር ከፍታሽን ያሳየን!🙏**
✍️**Aman YTZ
@amanytz

join and share
@YelbeDrset
@YelbeDrset

inbox me @amanytz
✍️✍️✍️✍️✍️✍️

3 months, 1 week ago
የልቤ ድርሰት የብዕር ጠብታ
6 months, 1 week ago

#ተከታታይ_ልቦለድ_ታሪክ
.
.
.
#ትንሽ_ስለ..!

ክፍል - ፲፫
.
.
("ምን አልባት ከቆየ ፍቅር ነው።
ምን አልባት ካለቀ የፍቅር ታሪክ ነው፣
እና ምን አልባት ጭራሹን ካልጀመረ ደግሞ ግጥም ነው።")

፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨

የቤተ እምነት ስፍራዎች ለነብስ እና ለአዕምሮ እረፍትን ለልብ ሰላምን ይሰጣሉ።

"ጌታዬ ሆይ ይህ አለም ላንተ ያለኝን ፍቅር ሊሻማኝ በሬ ቁሟል፤ ወደ ቤቴ እንዲዘልቅ አትፍቀድለት! የቤተሰቦቼን ልብ አራርተህ ሃሳቤን እንዲረዱ አድርግ..በተለይ አባቴ በኔ እንዲከፋ አልሻምና የሱን ልብ አደራ..! አይ ይህ ዓለም ያቀረበልሽን ተቀበይ ካልክ ግን..እንደ ፍቃድህ ይሁን!!"
ብላ ሃሳቧን ለፈጠራት ሰንዝራ ዛፍ ስር ቁጭ አለች። ዓይኖቿ ያቀረሩትን እንባ ቢፈስ ደራሽ ወንዝ ሊመስል ይችላል..

. . .

አለምነህ ወደ ሰማዕቱ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን ቅጥር ግቤ ከዘለቀ በኋላ ጸሎቱን ማድረስ፣ ምኞቱን ማሰማት ጀመረ.. ምኞቱና ጸሎቱም እንዲህ ይል ነበር..

'እማውቀው ይመስለኛል!'

ምኑን?

'ጸሎትና ምኞቱን'

እውነት?

'አዎ!..ይመስለኛል..አዕምሮዬ ላይ ያቃጭላል..ለምን እንደሆነ እንጃ! የት እንደመጣም አላውቅም!!'

ግድ የለም ረጋ በልና ንገረኝ እስኪ..?

'እሽ.. እ.. ሰ ማ ዕ ቱ..'

በል አይዞህ..

"ሰ ማ ዕ ቱ አባቴ.. እባክህ የመኖር ብርታትን ስጠኝ! ከህያውነቴ ላይ ህይወትን ዝራ.. መንፈሴንም አነቃቃው.. ልቤንም በተስፋ ሙላው.. በዚህ ዓለም ለመኖር እሚገፋኝ ብርቱ ምክኒያት ፍጠርልኝ.. በራሴ ታሪክ ዋና ገፀባህሪ ባልሆንኳን ጥሩ ረዳት ተዋናይ አድርገኝ!.. ማስተዋልና ጥበብን ስጠኝ.. እናቴን እድሜና ጤና ሰተህ አቆይልኝ.. ሐገራችንን ባርክ..አሜን።" እንዲህ ብየ ጸለይኩ.. ማለቴ ጸለየ.. እራሴን አመመኝ.. ወደ ቤት ልሂድ በቃ!!!

ቆይ እንጂ..

'አይ ልክ ያልሆነ ነገር አለ!'
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨

ሎዛ ቀኑ ለመምሸት ሲያስገመግም አይን ያዝ ማድረግ ሲጀምር ከቤተክርስቲያኑ ወጣችና ወደ ቤቷ ጠደፍ ስትል ድንገት እንደርሷ እሚጣደፈው አለምነህ ጋር ተጋጨች እና "ይቅርታ" ብላው ሳታስበው ፈገግ አለችና መንገዷን ቀጠለች.. አለምነህ በበኩሉ ፈገግ በማለቷ አፉ ተለጉሞ ምንም ሳይል ስትሄድ ቆሞ አያትና ለራሱ "በምሽት እሚታይ ፈገግታ! ወይ ግሩም!" አለ.. አዳሩንም እስኪገርመው ድረስ ፈገግታዋን እያሰበ ነጋ..

በሚቀጥለው ቀን በተመሳሳይ ሰዓት ከቤተክርስቲያን መልስ ከማያውቃት ልጅ ጋር የተጋጩበት ቦታ ላይ ቆም አለና ድጋሚ ትጋጨው ይመስል ጠበቀ..
  በራሱ ተገረመ.. "ምን ሁነህ ነው እዚህ የቆምክ? ኧረ ተንቀሳቀስ ባክህ ሰው ይስቅብሐል!" አለው ጭንቅላቱ..
አለምነህም እንደማፈር አንገቱን ደፍቶ እርምጃ ሲጅምር.. ከየት መጣች ሳትባል ሎዛ አሁንም ተጋጨችው.. አሁን ግን አለምነህ ባላወቀው ሐይል ተገፍቶ.. 'እያየሽ አትሄጅም?' አላት..(ማለት የፈለገው እንዳልሆነ ግልፅ ነው)

'በጣም ይቅርታ..!'  አለችውና ፈገግ ሳትል ወደ መንገዷ ዞረች..
አለምነህ አሁንም ሳያስበው.. 'ትናንትም'ኮ እዚሁ ቦታ ላይ ተጋጭተሽኛል?' አላት..

ሎዛም ባለመገረም 'እውነት! ..ይቅርታ..ወንድም ስለቸኮልኩ ነው።' አለችው..

አይ ሁለቴማ ይቅርታ የለም! ባይሆን ፈገግ በይ!! ሊላት አስቦ ተወው እና.. እሽ..ብሏት ፊቱን ዞረ.. እርሷም ሳታመነታ ሄደች.. "ኧረ አለምነህ ነጋ! ምን ነካህ? ሆ!" አለ ለራሱ..
ባይሆን አሁን በደንብ አይቷታል.. እርሷም ድጋሚ ብታየው ታውቀዋለች..
.
.
.

..ይቀጥላል..

✍️Aman? YTZ
@amanytz

join and share
@YelbeDrset
@YelbeDrset

inbox me @amanytz
✍️✍️✍️✍️✍️✍️

6 months, 2 weeks ago

.
.
እንደምን አላቹህ ቤተሰቦች?

"ቀጠሮ ደረሰ
እየገሰገሰ.."
እንዲል የቡሄ ጨፋሪ፤ ዛሬ ልቦለዱን እምንቀጥልበት ቀን ነበር ሁኖም በቀጠሮዬ ሰዓት አልተገኘሁም። ይህም ማለት እኔ Pure ሐበሻ ነኝ? + Lazy?.. So ክፍል አሰራ ሁለት ላይ እንዳቆመ ከዚያ ቀጥሎ ያለው እንኳን እዚህ አዕምሮየ ላይም አልተፃፈም?‍♂️ እና ያው እንደ ሁልጊዜው? ይቅርታ!?
ሰሞኑን Depressed ሳልሆን አልቀርም፤ እና ያው ታገሱ ለማለት ነው ይሄ ሁሉ..ታገሱሱሱ??

'እስከ መቼ???☹️' ( እሚል አይጠፋም!?)

እስከ..ትንሽ??
.
.
.

✍️ Aman? YTZ
@amanytz

6 months, 3 weeks ago

.
.
#ለጊዜ_ጌታ_የተፃፈ_ደብዳቤ!
.
.
ፈጣሪዬ ሆይ በሰማያት የምትኖር..
ብዙ መንገድ መተናል፣
ብዙ ትዝታዎችን ቋጥረናል፣
ብዙ ተስፋዎችን ሰንቀናል፣
ብዙ ሰዎችን አቅርበናል፣
ልብ ለልብ ተሳስረናል፣
መኖር አስከፊ ገፅ ቢኖረውም!
ለመሰንበት ጓጉተናል፣
ገና መኖርን ናፍቀናል፣
አዲስ ትዝታዎችን መመስረት አስበናል፣
በጥልቅ ፍቅር ወድቀናል፣
አብሮ ማርጀትን ተመኝተናል፣
ሞትን አርቀህ ትንሽ ጊዜ ስጠን ብለናል፣

እባክህ ጌታ ሆይ..
ቅጣት ያልካት ምድር አቅፋ አኑራኛለች፣
ስረግጣት ቢመራት ልትውጠኝ 'ጠብቃለች..!
እማይቻልህ የለ
ሁሉ በጅህ አይደለ!
በቃ ጊዜን አቁመው ቀናተም ይዘግዩ፣
የሰው እድሜ ይርዘም የወጣትነቱ፤

ኧረ ባክህ ጌታ ያላየነው አለ..
አታሳልፍብን ትንፋሽህን አትንሳን
ከመምጣታችን በፊት መቆየት እንሻለን..
ወይ ደግሞ ሁሉም ይቅር! ሁሉም ባንዴ ይጥፋ፣
የቀደመው ሞቶ! ቀሪው ከሚከፋ!
ወይ ሁሉም ባንድ ይሁን..!!
.
.
.

✍️Aman? YTZ
@amanytz

join and share
@YelbeDrset
@YelbeDrset

inbox me @amanytz
✍️✍️✍️✍️✍️✍️

8 months, 3 weeks ago

#~~የመስመር_ዳኛ~~ #
.
.
ለእግዜር ያልተዘረጋ እጅ.. ለሰው ልጅ ቢዘረጉት ከማሳፈር በቀር በረከት የለውም!!
.
.
..መኪናው ውስጥ ተደላድሎ እንደተቀመጠ ለመኪና ማቆያ ጠባቂው ወጣት በመኪናው መስኮት በኩል ሶስት የአስር ብር ኖታዎቸን አውለበለበለት.. ጠባቂውም ገስገስ ብሎ በመቅረብ እጥፍ ዘርጋ ልምጥምጥ እያለ በፈገግታ እያመሰገነ ተቀበለ፤..

ታዲያ ይሄኔ አዳፋ የለበሰች፣ አይኗ የደፈረሰ፣ መልኳ የጠወለገ፣.. ህፃን ያዘለች እንስት ወደ ባለ መኪናው በልመና እጇን ዘረጋች..ባለ መኪናው ግን ዝም ብሎ መስኮቱን ዘግቶ መኪናውን አንቀሳቀሰ..

"እንደዘጋህባት! ፈጣሪ ስትለምነው ይዝጋብህ!" አይባል ነገር።

የእንስቷ መልክ ሃዘን አላስነበበም.."ከተገኘ ጥሩ ካልሆነም ምንም አይደል!" እንደማለት..

እጆቿ መፍተልን፣ መስፋትን፣ ማስጌጥን.. ተነጥለው ከሰው ደጅ መጥናት ብርቱ ልማዳቸው እንዳደረጉ ያስታውቃል። በይሉንታ በአዕምሮዋ ሳታንሰላስል እጇ ለልመና ይፈጥናል። እጥፍ ዝርጋ ይላል። ይቺ እንስት ግን ለፈጠራት አምላክ ይህን ያህል ደጅ ፀንታ ይሆን?

ፈጣሪዋስ እንዲህ ሲያያት ምን ይላል!?

አንዱን አዝላ ሶስት እግር ተከል ልጆቿን እያስከተለች የጠወለገው መልኳ እንደ ሻማ መክብብ ባይፈካም፤ ባደፈው አይኗ የዛሬን ወጋገን ባታይበትም፤ የነገን ጀንበሮች አቅፋ ታድራለች።
.
.
.

ነሐሴ 03/2016 ዓ.ም

#የሸገር_ጎዳናዎች

✍️Aman? YTZ
@amanytz

join and share
@Yelbedrset
@Yelbedrset

inbox me @amanytz

9 months ago

.
.
#ያንድ_ምሽት_ሀሳብ

ልማድ ሆኖበት፥ ሌቱ ቢገፋ
ምን ሊጠቅመኝ፥ ነው የማንቀላፋ
ህልም ሸክም ነው፥ ፈቺው ከጠፋ፤

ሳይጎድለኝ ለዛ
ሳያንሰኝ ውበት
የቀን ጨረቃ፥ ላይንሽ ሆኘበት፥
ቀልብን የማይስብ፥ የሳር ቀለበት
መወደዴ ብላሽ
ምኞቴ ዘበት፤

የአሻንጉሊት ላም፥ ጡት እንደማለብ
የፈረስ ሀውልት፥ እንደመጋለብ
ሲሳይሽ ፈልቆ፥ ጣት አያርስም
የትም ብትኖሪ፥ የትም አልደርስም፥

የሚፈሰውን አልፎ ገደቤን
-እንባየን ልሼ
ደረቴን ሰብሮ ፥ የሸሸ ልቤን
ቦታው መልሼ
በፍቅር ፈንታ ፥እረፍት ሸመትሁኝ
ቁርጤን አወቅሁኝ ፤

ለካ ሰው ቢማር፥
ከሊቅ፥ ከመጻፍ፥ ከኑሮ ከእድሜ
ቁርጥን ማወቅ ነው የእውቀት ፍጻሜ::

በእውቀቱ ስዩም
(from= FB page= የመጽሐፍ ዓለም-Book Shelf)

join and share
@Yelbedrset
@Yelbedrset

inbox me @amanytz

9 months, 3 weeks ago

፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨

ቤተሰቦች እንደምን አላቹህ??

፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
"Long Time No See?" እንዲል ፈረንጅ? በኢንተርኔት መገዘት ምክኒያት ጠፍተን ከርመናል እና ያው አሁንም ኢተርኔት ተፈቶ ሳይሆን ባንዱ ሆቴል Wifi ተጎልቸ ነው፤ እና በዚሁ ሳልፍ ሰላምታ ለማስተላለፍ እና በተግስት ቻናሉን ላለቀቃቹህ ቤተሰቦች ምስጋና ላቀርብ ነው!? እዚህ ላይ አንዳንድ አንባቢ? "እና Wifi ካለህ እስከዛሬ ምን ይዘጋሃል እማትፅፍ!!" ይል ይሆናል! ያለማስተባበያ መልሴ እሚሆነው Pure ስንፍና ብቻ ነው!!?‍♂️ እና ለዚያም ይቅርታ!????

መጨረሻ ሳስታውስ ቻናሉ 2K በላይ አባላት ነበሩት አሁን ወደ 1.7K ዝቅ ብሏል ግን ቢሆንም ብዙ አልከፋኝም ያለውን ይባርክ ነው።? እና ለናንተ 1.7K ግን ምስጋናየን አቀርባለሁ??? እንግዲህ በቻልኩት መጠን በሳምንት አንዴም ቢሆን የሆነች ነገር ለማጋራት እሞክራለሁ!! ማንኛውም አይነት ስነ-ጽሑፍ ያላቹህና ማጋራት እምተፈልጉ በውስጥ መስመር አናግሩኝ ምክኒያቱም የቻናሉ አላማ ያ ነውና!!!

በመጨረሻም መልካም ቆይታ
ኢተርኔት እስኪፈታ
እኔ ሸገር ለመሄድ እስኪያበቃኝ
ወይ ሸገርን ማምጫ እስክናገኝ
በትግስት ጠብቁ
ከቤተሰብነት ሳትለቁ???

@YelbeDrset

? @amanytz
? @aman116

፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨

1 year, 2 months ago

.
.
#ገጣሚ_አታፍቅሪ

ገጣሚ

ከሴት መተኛት ምንም
ስሜት አይሰጠው ለእርሱ
ከቃል ነው እንጂ
ከሴት ፍቅር አይዘው እርሱ

       ስለዚህ

አፈቀርኩሽ ወደድኩሽ
ብሎ ቢያወራልሽ
ከሺህ ቃላት ወስዶ
እንድ ቃል ቢነግርሽ
እንዳትሰሚው እርሱን
እንዳታደንቂ ቃላት አጠቃቀሙን

ምክንያቱም

ላንቺ ቃል እምነት ነው
ላንቺ ቃል ፍቅር ነው
ላንቺ ቃል ተስፋ ነው

        ግን

ቃል ለእርሱ ቀላል ነው
በቃ ዝም ብሎ
ፊደል መመስረት ነው
.
.

ገጣሚ ስንታየው ታገሰ

join and share
@Yelbedrset
@Yelbedrset

inbox me @aman116

We recommend to visit

ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ

Last updated 4 months, 1 week ago

Last updated 4 months ago

ይህ ስለ Manchester United መረጃዎችን የሚያገኙበት የ Telegram ቻናል ነው 🇪🇹
--------------------------------------------------------------
☞︎| ስለ ማንቸስተር ዩናይትድ ትኩስ መረጃዎች
☞| ቀጥታ ስርጭቶች ከየስታድየሞቹ
☞| የዝውውር ዜናዎች
☞| ስለ ማንችስተር ዩናይትድ ታሪኮች

📩 ለማስታወቂያ ስራ DM :- @Marcoabdu

Last updated 3 months ago