Unlock a World of Free Content: Books, Music, Videos & More Await!

ኢማን 🌙тυℬℰ™🌙

Description
<< `በጊዜያቱ እምላለሁ ፤ ሰው ሁሉ በእርግጥ በከሳራ ውስጥ ነው ፤ እነዚያ ያመኑትና መልካሞችን የሠሩት ፥ በእውነትም አደራ የተባባሉት ፥ በመታገስም አደራ የተባባሉት ብቻ ሲቀሩ።` >>
ሱረቱል ዐስር፦(1፥3)

For comment an& cross
▼▼▼▼▼▼▼▼▼▼
@Alhamdulilah25
Advertising
We recommend to visit

ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ

Last updated hace 1 día, 17 horas

ለማንኛውም አስተያየት እና ጥቆማ 👉 @Esat_tv_comment_bot

🇪🇹ኢሳት የኢትዮጵያ አይን እና ጆሮ🇪🇹

Last updated hace 5 días, 6 horas

Last updated hace 5 días, 19 horas

1 день, 13 часов назад

በዚህ ታሪክ ውስጥ አላህ ምን ያህል ለባሮቹ ሩህሩህ፣ ያሻውን የሚያደርግ ኃያል ጌታ እንደሆነ እንረዳ ዘንድ እናስታውስ ላመኑት ይጠቅማልና ማስታወስ
Mahi Mahisho

ውልደታቸው በፓኪስታን ዋና ከተማ ነው። በዘመናችን አንቱታን ያተረፉ ከኒውሮሎጂ የህክምና ዘርፍ ጠበብቶች ውስጥ በግንባር ቀደምትነት የሚጠቀሱ  ስመ-ጥር ስፔሻሊስት ናቸው። ሕክምና ለመስጠት ከሀገር ወደ ሀገር ከከተማ ወደ ገጠር ስለሚዘዋወሩ በስራቸው ባህሪ ከባድነትና እረፍት አልባነት ጋር ተደማምሮ ህመምተኞች እሳቸውን በቀላሉ ለማግኘት ይቸግራቸዋል። ከስድስት ወራቶች እስከ ዓመት ቀጠሮ መጠበቅ ግድ ይላል።

እነሆ ዛሬ እዛው ፓኪስታን ውስጥ በሽተኞችን ለማከም ቀጠሮ ይዘዋል። ካሉበት ከተማ ወደ ሌላ ከተማ ለመሄድ በአውሮፕላን ጉዞ ጀምረዋል። ብዙም ሳይርቁ የተሳፈሩበት አውሮፕላን በገጠመው ጭጋጋማና መጥፎ የአየር ሁኔታ በአንድ ትንሽ ከተማ አየር ማረፊያ ለማረፍ ተገደዱ። ከአውሮፕላኑ ወርደው የአየር ሁኔታው እስኪሻሻል ቢጠብቁም እንዳሰቡት ሳይሆንላቸው ቢቀር የአውሮፕላኑን ፓይለት የጉዟቸው መዳረሻ ወደሆነችው ከተማ ለመድረስ ምን ያህል ጊዜ እንደሚፈጅ ጠየቁት። ፓይለቱም ሶስት ስዓት እና ከዛ በላይ እንደሚሆን ነገራቸው። ዶክተሩ አንድ የሚያስጨንቃቸው ነገር አለ።  ብዙ ህመምተኞች የእሳቸውን እርዳታ በመፈለግ በቀጠሯቸው መሰረት የሳቸውን መምጣት በመጠባበቅ ላይ መሆናቸው አሳስቧቸዋልና በዚህ ሁኔታ ለማደር አእሞሯቸው አልፈቀደም። መኪና ይዘው ጉዟቸውን ለመቀጠል ይወስናሉ። ግና ትንሽ ከተጓዙ በኋላ ከባድ ዝናብ መንገዳቸውን ገታው። መንገዱ ጭቃማ ስለሆነ  መኪናቸውን መንቀሳቀስ ባለመቻሏ አሁንም በድጋሚ ባሉበት ስፍራ ለመቆየት ተገደዱ። አሁን ያሉበት መንደር ደግሞ በጣም ሩቅ የሆነ ገጠራማ መንደር ሲሆን ዝናቡ እስኪያባራ ከመኪናቸው ወርደው ሰላት ለመስገድ አሰቡ። ውሃ እና መስገጃ ፍለጋ ወደ አንድ ቤት አቀኑ።

በሩን በዝግታ አንኳኩ። እድሜያቸው  ገፋ  ያለ አንዲት  አዛውንት በሩን ከፈቱ። ምን ልርዳችሁ በማለት ጠየቁ። ዶክተሩም ሰላምታ ካቀረቡ በኋላ ሰላት ለመስገድ ስለፈለኩኝ ጥቂት  ውሃ እና መስገጃ ፈልጌ ነው በማለት ጠየቁ። መርሃባ ግቡ በማለት ውሃ እና መስገጃ አቀረበችላቸው። ሰግደው እንደጨረሱ ሙስልሟን ሴት አመስግነው ሊወጡ በመራመድ ላይ ሳሉ አልጋ ላይ የተኛ ሰው ተመለከቱ “ምነው?.. ምን ገጥሞት ነው?” ብለው ጠየቁ።  ሴትዮዋም ታሪኩን ታወጋ ጀመር “እዚህ ቤት ውስጥ የምንኖረው እኔና ይህ የምትመለከቱት ልጄ ነው። ለረጅም ጊዜ በያዘው ህመም በመሰቃየት ላይ ነው። በተደጋጋሚ የተለያዩ ሐኪሞች ጋር በመሄድ ሕክምና እንዲያገኝ ብሞክርም ሳይሳካ ቀረ። ዶክተሮች ወደ ታዋቂ ስፔሻሊስት ዶክተር እንድሄድ በሰጡኝ ጥቆማ መሠረት ወደተባለው ዶክተር ዘንድ ሄጄ ነበር። ነገር ግን ዶክተሩ ብዙ በሽተኞች ስለሚያስተናግዱ እሳቸውን ማግኘት እንደማይቻልና ከ6 ወር በሃላ እንድንመለስ ቀጠሮ ተሰጥቶን ወደ ቤት ተመለስን” አሉ አዛውንቷ ትክዝ ብለው መሬት እንዳቀረቀሩ ንግግራቸውን ቀጠሉ “እኔ አቅመ ደካማ አዛውንት ነኝና ልጄን ይዤ ወደ ቤት ተመለስኩ። አላህን ቀንና ማታ እየለመንኩት ነው። አልሀምዱሊላህ እስካሁን ነብሱ አለች...” አሉ አዛውንቷ እምባ እየተናነቃቸው።

ዶክተሩ  የሴትዮዋን ንግግር በጥሞና አድምጠው ሲጨርሱ ”ማን የሚባል ዶክተር ጋር ነው ዶክተሮች እንድትሄዱ የነገሯችሁ?” አሉ። “አንድ ታዋቂ የሆነ ስሙ ዶ/ር ኢሻም የሚባል ሀኪም ዘንድ እንድሄድ ነበር የተነገረኝ” በማለት ለዶክተሩ ምላሽ ሰጡ። የሰሙትን ነገር ለማመን የከበዳቸው ዶክተር እራሳቸውን መቆጣጠር ተስኖዋቸው  እምባቸውን ማፍሰስ ጅመሩ። አስከተሉና "አላህ ዱአዎትን ሰምቶ ምላሽ ሰጥቷል” አሉና ንግግራቸውን አስከተሉ “ህመምተኞችን ለመርዳት ወደሌላ ከተማ ቀጠሮ ነበረኝ። በአውሮፕላን ጉዞዬን ጀመርኩ ግን በመጥፎ የአየር እክል ምክንያት ሳይሳካ ቀረ እንደገና በመኪና ጉዞዬን ለመቀጠል ሞከርኩ። በከባድ ዝናብ እና ጭቃ እዚህ መንደር ለመቆየት ተገደድኩ ...” በማለት ተናገሩ። ለመጀመሪያ ጊዜ ታሪኩን ስሰማ እንባዬን መቆጣጠር አልቻልኩም ነበር ይላሉ ታሪኩን የተረኩልን ሙፍቲ ሜንክ።

አላህ ይህን ውድ ዶክተር የዚህችን አቅም አልባ እና ልጇን ምታስታምም አዛውንት ቤት ድረስ አምጥቶ በራቸውን እንዲያንኳኩ ሲያስደርግ፣ ሩቅ እና ገጠራማውን መንደር አቆራርጦ አላህ በችሎታው ቤት ድረስ ሲያመጣው ከማየት በላይ ሚያስደንቅ ነገር አለመኖሩን እናስታውስ ላመኑት ይጠቅማልና ማስታወስ።

አላህን የያዘ ምን አጣ
አላህንስ ያጣ ምን አገኘ

@sineislam
@sineislam

3 дня назад

ቢስሚላሂ ረሕማኒ ረሒም - መልካም ምክሮች

1- ቀንህን ከምትጀምርባቸው ነገሮች ሁሉ ዚክር እና ሶላት ምርጦቹ ናቸው!!

2- ወንጀል ብትሰራም ባትሰራም ምላስህ ሌት ተቀን አላህን እስቲግፋር ከመጠየቅ አይቦዝን!

3- በዱዐ አትዘናጋ ለመዳን ወሳኙ መሳሪያ እሱ ነውና!!

4- ከመናገርህ በፊት ቃላቶችህን የሚፅፉ መላኢካዎች አጠገብህ እንዳሉ አትዘንጋ!!

5- ትልቅ ማእበል ቢያጋጥምህ እንኳ አሁንም መውጫ እንዳለህ አስብ!!

6- አለንጋ ጣቶችህ የበለጠ የሚያምሩት ዚክር ላይ ሲሳተፉ ነው!!

7- ለዱዐ ምላሽ የምታገኝበትን እድል ሐራም በመብላት አትዝጋው!!

8- የመጥፎ ጥርጣሬ አባዜ ከሌለብህ ደስተኛ ሁነህ ትኖራለህ!!

9- በጋዜጣና በሞባይል ፍቅር ከመውደቅህ በፊት በቁርአን ፍቅር ውደቅ!!

10- የሰው ልጅ ነፍሱ አመፀኛ ናትና በአላህ ትዛዝ ላይ አስገድዳት!!

11- ያንተ አሮጌ ልብሶች ለድሃ አዳድሶች ናቸው!!

12- ምድርን ስትሰናበት ካንተ ጋራ መቃብር የሚገባ ስራ ይኑርህ!!

13- ሀሜተኛ ሰው ካጋጠመህ 'አላህን ፍራ' ለማለት አትፍራ!!

14- ህይወት በተፈጥሮ ውብ ናት፣ ከኢማንና ከተስፋ ጋር ደግሞ እጅግ ውብ ናት!!

15- የምትቸኩልለት ነገር ሁሉ ከሶላት የሚበልጥ አይደለምና ተረጋግተህ ስገድ!!

16- ህይወት እኛ ከምንገምተው በላይ በጣም አጭር ናትና ከዚህም ከዚያም ጋር አትጋጭ!!

17- የጭንቀት ሁሉ መንስኤው ከአላህ ﷻ መራቅ ነውና በተቻለህ አቅም ከአላህ ላለመራቅ ሞክር!!

@sineislam
@sineislam

4 дня, 5 часов назад

በየቀኑ ባነበውም በየቀኑ ይገርመኛል
.
ከእለታት አንድ ቀን ነቢዩ ሙሐመድ ሰ.ዐ.ወ ዘንድ አንድ ከገጠርየመጣ ኑሮው ያልሰመረለት (ድሃ) ግለሰብ ሰሃን ሙሉ ወይን ስጦታ ያመጣላቸዋል፡፡

ነቢዩም ሰ.ዐ.ወ ስጦታውን ተቀብለው ወይኑን መብላት ጀመሩ..የመጀሪያውን ጎርሰው ፈገግ አሉ..ሁለተኛውንም ጎርሰው ፈገግ አሉ..

ግለሰቡም እጅጉን ተደሰተ..የነቢዩ ጓዶች (ሰሃቦች) ሁሌም ለነቢዩ ሰ.ዐ.ወ ስጦታ
ሲመጣላቸው ስለሚያካፍሏቸው ይህንን (ጣፋጭ) ወይን እንዲያካፍሏቸው በጉጉት ይጠብቃሉ..

የአላህ መልእክተኛ ግን ሳያካፍሏቸው እያንዳንዱን የወይን ፍሬ እየበሉ እና ፈገግ እያሉ ሁሉንም በልተው ጨረሱ.. ስጦታ አቅራቢው እጅግ በጣም ተደሰቶ..ስጦታውንም ስለወደዱለት አመስግኖ ሄደ..

አንድ የነቢይ ሰ.ዐ.ወ ጓድ (ሰሃባ) ጠጋ ብሎ ነቢዩን ጠየቃቸው ‹‹የአላህ መልእከተኛ ሆይ..ምነው ሳያካፍሉን?››

እሳቸውም ሰ.ዐ.ወ ፈገግ ብለው መለሱ ‹‹ሰወዬው መደሱቱን አይታችኋል አይደል?!..

ወይኑን ስቀምሰው በጣም ይመር ነበር..ባካፍላችሁ አንዳችሁ ግለሰቡን የሚያስከፋ እና ደስታውን የሚያደፈርስበትን ነገር እንዳታሳዩት ብየ ስለሰጋሁ ነው ብለው መለሱላቸው;;;;;

ሀቢቢ  የኔ  ነቢይ  እናቴም  አባቴም  ህይወቴም  ፊዳ  ይሁንሎት።

@sineislam
@sineislam

1 неделя, 3 дня назад

ከልብ የመነጨ ወደ ልብ የሚገባ ነብያዊ ሀዲሶች ۵۵ ═ ۵ ═ ۵ ═ ۵ ═ ۵ ═ ═ ۵ ═ ۵ ═ ۵ ═ ۵ ═ ۵۵

✔️ 1☞!!! ምቀኝነትን ተጠንቀቁ እሳት እንጨትንእንደሚበላውሁሉ ምቀኝነት ከይር ነገርን ይበላል

✔️ 2☞ !!!ሀሜት ምን እንደሆነ ታውቃላችሁን? በማለትነብዩ ሰ ዐ ወ ጠየቁ ሰሀቦችም አላህና መልእክተኛውያውቃሉ አሉ (ወንድምህ በሚጠላው ነገርማንሳት ነው አሏቸው) የምናነሳበት ነገር ያለበትስ ቢሆንሲሏቸው የምትለው ነገር ካለበት አማሀው ከሌለበተደግሞ ቡህታን ጫንክበትይባላል

✔️ 3 ☞ !!! አማኝን ሰው መርገም እንደመግደል ይቆጠራልተራጋሚዎች የቂያም ቀን ሽማግሌም ሆነ ምስክርአይሆኑም

✔️ 4 ☞ !!! የቂያም ቀን መጥፎ ደረጃ ካላቸው ሰዎችመካከል አንዱ ከሚስቱ ጋር ሚስጥር አውርቶ ሚስጥሯንየሚዘራ ነው

✔️5 ☞ !!! ሰዎችን ለማሳቅ ብሎ ውሸትን የሚያወራ ሰውወየውለት

✔️ 6 ☞ !!! ነብዩ ሰ ዐ ወ ወለድ በይና አብይን ረገሙእያወቀ ወለድ የሚበላት አንዲት ዲርሀም ቅጣት ከሰላሳስድስት ዝሙት ቅጣት የበረታ ነው አሉ

✔️ 7 ☞ !!! አማኝ የሆነ ሰው ወንድሙን ከሶስት ቀን በላይማኩረፍ አይፈቀድም አማኝ ወንድሙን አመት ሙሉያኮረፈ ሰው ደሙን እንዳፈሰሰ ነው

✔️ 8 ☞ !!! ጭንቀቱ የዚህች ዐለም አዱኒያ የሆነ ሰው አላህድህነትን በሁለት አይኖቹ መካከል ያደርግበታል ሀሳቡንይበትንበታል ከዱኒያም የተወሰነለት እንጂ አይሰጠውም

✔️ 9 ☞ !!! ዝምድናን የሚቆርጥ ሰው ጀነት አይገባም

✔️ 10 ☞!!! የማትፈቀድለትን ሴት አካል ከመንካት በብረትወስፌ ራሱን መውጋት ይሻላል ❄️ ያጀመዓ በኔ ብቻ አይቅር ካሉ ❄️ ለህት ወንድም ❄️ ሼር ሼር በማድረግ ያስተላልፉ ❄️ አስተውሉ ሼር ማድረግም ደአዋ ነው

✔️✔️✔️✔️✔️✔️✔️✔️✔️✔️
ታዋቂ ለመሆን ሳይሆን አዋቂ ለመሆን ጣር!

"ወደ መልካም ነገር  ያመላከተ ሰው የሰራውን ሰው ያህል አጅር ያገኛል" ረሱል (ﷺ)

@sineislam
@sineislam

1 неделя, 4 дня назад

⚠️🚫ለዘፈን_አፍቃሪያን_መገሠጫ_ትሆን_ዘንዳ_ይህችን_ታሪክ_አንብቧት 👇👇👇

*ልጁ በጣም ሙዚቃ ማዳመጥ ይወዳል። ጠዋት፣ ማታ፣ቀን፣ለሊት፣ሁልም ጆሮው ላይ ኤርፎን ሰክቶ፣ አላህ ለቁርአን፣እንዲሁም ለተግሰጽ የለገሰውን ጆሮ ለሃራም እናለማይወደው ድርጊት ይጠቀማል።

ታድያ ከዕለታት አንድ ቀን ት/ቱን ጨርሶ፣ ቤት ይገባል። ልቡ የሚገኘው ዛሬ ምን አይነት ዘፈን አውርጄ ላዳምጥ ነው ። ከዚያም ፍራሹ ላይ ጋደም ብሎ፣ ሞባይሉን ከፍቶ፣በማዳመጥ ላይ ሳለ የክፍሉ መብራት ድንገት በኃይል ድርግም ብሎ ይጠፋል ።

ደንግጦ የሞባይሉን ፍላሽ በማብራት፣ ኤርፎኑን ለመንቀል ቢሞክር እንቢ ይለዋል። ከጆሮው ውስጥ የተጣበቀው ኤርፎን፣አልነቀልም ብሎ ብዙ አታገለው። በመጨረሻም ስላልቻለ ለቤተሰቡ ተናገረ።

ቤተሰቡ ሙዚቃ በማዳመጡ ቢናደዱም፣አሁን ለችግሩ መፍትሔ እንፈልግ በማለት በፍጥነት ወደ አቅራቢያው ከአንገት በላይ እስፔሽላይስት ህክምና ወሰዱት።

ዶክቶሮች በድንጋጤ እንዲሁም በመገረም እንዲህ አይነት ሁኔታ አጋጥሟቸው እንደማያውቁና ከአቅም በላይ ስለሆነባቸው ወደ ሌላ የሕክምና ማዕከል ሪፈር ይጽፋለታል። ቤተሰብ በጣም ተጨንቋል።

ልጁ ምንም አያወራም፣ ዝምታን ተከናንቦ አይኑን ያቁለጨልጫል።በአብዋራ የተሞላ ፀጉሩን እያከከ በዙሪያው ያሉ ሰዎች የሚያወሩትን ለማዳመጥ ይሞክራል።

ነገር ግን ምንም ነገር አይሰማውም። ጆሮው ደን ቁሯል። አላህ የሰጠውን ጆሮ ቁርአንን ለማዳመጥ ሳይጠቀም ሙዚቃ አዳምጦበታል። በዚህም የፀፀተው ይመስላል።

ወደ ሌላ ሕክምና ማዕከል ተጉዘው ከከባድ የ 2፡00ሠዓት ቀዶ ጥገና ሕክምና በኃላ ኤርፎኑ ለብቻው መወገድ ስላልቻለ ሁለቱ ጆሮዎች፣ከቦታቸው ተነቅለው የማዳመጥ ፀጋን አሳጥቶት ከሕክምና ማዕከሉ ወደ ቤት ተመለሰ። ከዚያ በኃላም ጤና እያለው ያልቀራውን ቁርአን ለማንበብ ይታገላል። ሕይወቱንም በፀፀት እና በማልቀስ ለመግፋት ተገዷል።

ኢኽዋኒ ወ አኽዋቲ አላህ የሰጠንን ፀጋ እሱን ለማመስገን እንጂ፣እሱን ለማስቆጣት አንጠቀመው። ሙዚቃን ከመስማት ርቀው፣ ቁርአንን በማዳመጥ ከሚረኩት ያድርገን!!!
አላሁመ አሚን!

በተቻለን አቅም ለሌሎች በማድረስ ከሀራም ነገራቶች እንዲርቁ  ሰበብ  እንሁናቸው ።

@sineislam
@sineislam

1 неделя, 5 дней назад

logo መስራት የምትችሉ graphics designer አላቹ?

2 месяца, 1 неделя назад

ትኩረት ለትውልድ ተስፋ ተማሪዎች

ዓለም ባንክ አካባቢ የሚገኘው «የትውልድ ተስፋ» በሚባል ትምህርት ቤት የሚገኙ ሙስሊም ተማሪዎች ላይ ጭቆና እየተፈጸመ የሚጠቁሙ መረጃዎች ደርሰውኛል።

በትናንትናው ዕለት መለትም የካቲት 12/06/2016 ዓለም ባንክ አደባባይ ከፍ ብሎ ኢማሙ አሕመድ መስጅድ አቅራቢያ የሚገኘው የትውልድ ተስፋ ት/ቤት ዳይሬክተር የሆነውና ከታች በምስሉ ላይ የሚታየው ምስክር ጌታነው የሚባል በብስራት ሬድዬ የአሻም ኘሮግራም አዘጋጅና አቅራቢ የሆነ ግለሰብ የት/ቤቱን የሙስሊም ተማሪዎች ጀማዓህ አሚሩንና ቁጥራቸው 9 የሚደርሱ የተማሪዎች ወኪሎችን ወደ ወደ ፌዴራል ፖሊስ እና የአዲስ አበባ ፖሊሰ ኮሚሽንን እንዲሁም የኮልፌ ቀራንዬ ፖሊስ መምሪያ ኃላፊዎችን በመጥራት በቁጥጥር ስር እንዲውሉ አድርጎ ኮልፌ ክ/ከተማ ፖሊስ መምሪያ እስር ቤት እንዲታሰሩ አድርጓዋል።

የእስራቸው ምክንያት ከዚህ ቀደም የት/ቤቱ የፕሮቴስታንት ተማሪዎች በሙስሊም ተማሪዎች ላይ በሚሰራ ሲሕር ቁጥራቸው  7 የሚደርሱ ተማሪዎች  በተከታታይ እዚያው ት/ቤት ግቢ ውስጥ ራሳቸውን ስተው እየወደቁ  ከትምህርት ገበታቸው ተቋርጠዋል። ነገሩ እየከፋ ሲመጣ የተማሪዎቹ ወኪል የሆኑ ተማሪዎች ለዚሁ  ዳይሬክተር አቤቱታ ቢያቀርቡም "አጉል ስም ማጥፋት ነው!" በሚል ለጉዳዩ እልባት ለመስጠት ፈቃደኛ ሳይሆን ይቀራል ሙስሊም ተማሪዎቹ ተስፋ ሳይቆርጡ ጉዳዩን ለወላጅ ኮሚቴ አሳውቀው  ወላጅ ኮሚቴ ቢጠይቀውም ፈቃደኛ ሊሆን አልቻለም። በመጨረሻም በሲሕር አድራጊነት የሚጠረጠሩ 3 ልጆችን ቀሪው ሙስሊም ተማሪ እንዲጠነቀቃቸው ይፋ አደረጉ።
በዚህ ምክንያትም ትናንት የተለያዩ የፖሊስ አካላትን በማስመጣት 9 ተማሪዎችን አሳስሯል። የታሰሩት ተማሪዎች ስም ዝርዝር፦

1   ዐብዱርረሕማን ሲራጅ
2   ሙሐመድ ዐብዱሽኩር
3   አይመን ኑሪ
4   ጂብሪል ሸምሱ
5   ሒክማ ዑመር
6   ሲያም አሕመድ
7  ሱመያ ኑደሞ
8   ሙኒር ኸድር
9   ..............

የአዲስ አበባ መጅሊስ፣ የኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ መጅሊስ፣ የክፍለ ከተማው አስተዳደርና ሌሎችም በየደረጃችሁ የሚመለከታችሁ አካላት በሙሉ ተገቢውን አስቸኳይ መፍትሄ ልታበጁ ይገባል።

በሆነ ባልሆነው ሙስሊም ተማሪዎችን እየጨቆኑ ከትምህርት ገበታቸው ማፈናቀል መቆም አለበት።

2 месяца, 1 неделя назад

*# ከቁርኣን ጋር ያለን ትስስር እንዴት ነው……!!!
__
በጊዜህና በስራህ ውስጥ በረከት ካጣህ
የልብ ድርቀትና ፅልመት ከተሰማህ
ጭንቀት፣ውጥረት፣ሐዘን ከወረረህ
ቆም በልና ከቁርኣን ጋር ያለህን ግንኙነት ፈትሽ!
__
« ልባችን ቢፀዳ ኖሮ፣ከአላህ ንግግር ባልጠገበ ነበር
ወዳጅ ከወዳጁ ንግግር እንዴት ይጠግባል !! »

ሰዪዲ ዑስማን ቢን ዐፍ’ፋን (رضي الله عنه)
📚አል–ጀዋቡል–ካፊ#ሼር
◈•┈┈┈┈•✿❁✿•┈┈┈┈•◈
@sineislam
➢* @sineislam

2 месяца, 2 недели назад

ሁላቹንም ለአላህ ብዬ እወዳቸዋለሁ 😍😍😍❤️😘😘😘😘😘

4 месяца, 2 недели назад

#እኔ ምላቹ ሱሪ በሂጃብ የምትለብሱ😳 ሴቶች ግን #ጭንቅላታችሁ ብቻ ጀነት እንዲገባ ፈልጋችሁ ነዉ😏😇🤷‍♀
🔰🔰🔰🔰🔰🔰
🔰🔰🔰🔰🔰🔰

We recommend to visit

ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ

Last updated hace 1 día, 17 horas

ለማንኛውም አስተያየት እና ጥቆማ 👉 @Esat_tv_comment_bot

🇪🇹ኢሳት የኢትዮጵያ አይን እና ጆሮ🇪🇹

Last updated hace 5 días, 6 horas

Last updated hace 5 días, 19 horas