ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።
@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna
#ኢትዮጵያ
Last updated 2 months, 3 weeks ago
Last updated 2 months, 2 weeks ago
ይህ ስለ Manchester United መረጃዎችን የሚያገኙበት የ Telegram ቻናል ነው 🇪🇹
--------------------------------------------------------------
☞︎| ስለ ማንቸስተር ዩናይትድ ትኩስ መረጃዎች
☞| ቀጥታ ስርጭቶች ከየስታድየሞቹ
☞| የዝውውር ዜናዎች
☞| ስለ ማንችስተር ዩናይትድ ታሪኮች
📩 ለማስታወቂያ ስራ DM :- @Marcoabdu
Last updated 1 month, 1 week ago
This week is also known as “Hercules’s fast.” The naming is related with the finding of the Holy Cross that the Lord was crucified on. The King regained back the cross from the theft committed by King of Persia, Cyrus. Then, the people pronounced it to the King demanding justice. The King brought back the Cross onwards a battle with the Persian King. But after his triumph on the war, he faced another trial. The rule of Church on killing stated that “a person who killed shall fast his entire life.” Therefore, the people fasted the fasting King Hercules’s was order to fast by distributing the age of the King amongst themselves. In the commemoration of him, the first week is known as “The Fast of Hercules” and all Christians fast it. (Book of Ethiopian Synaxarium Megabit 10)
Though Zewerede is not included amongst the forty days our Lord fasted, the Church made order and included it amongst The Great Lent. We then fast it as an order but not by owns will.
May God’s mercy be upon us throughout this fast; Amen!
He Who Comes Down
The First Sabbath of “The Great Lent” according to our Holy Church’s teachings is known as “Zewerede” to mean “He Who Comes Down.” Saint Jared’s hymn for this holiday states about The Holy Son Coming from the heavens as He vowed to the first mankind Adam and for the salvation of all human race. (Book of Tsome Deguua)
This week is the commemoration of the Lord Who Came Down from His mysterious in highness and everlasting holiness and be revealed on this vain world, in search of man by His unconditional love.
Saint Athanasius said, “For this purpose, then, the incorporeal and incorruptible and immaterial Word of God entered our world. In one sense, indeed, He was not far from it before, for no part of creation had ever been without Him Who, while ever abiding in union with the Father, yet fills all things that are. But now He entered the world in a new way, stooping to our level in His love and Self-revealing to us. He saw the reasonable race, the race of men that, like Himself, expressed the Father's Mind, wasting out of existence, and death reigning over all in corruption. He saw that corruption held us all the closer, because it was the penalty for the Transgression; He saw, too, how unthinkable it would be for the law to be repealed before it was fulfilled. He saw how unseemly it was that the very things of which He Himself was the Artificer should be disappearing. He saw how the surpassing wickedness of men was mounting up against them; He saw also their universal liability to death. All this He saw and, pitying our race, moved with compassion for our limitation, unable to endure that death should have the mastery, rather than that His creatures should perish and the work of His Father for us men come to nought, He took to Himself a body, a human body even as our own. Nor did He will merely to become embodied or merely to appear; had that been so, He could have revealed His divine majesty in some other and better way. No, He took our body, and not only so, but He took it directly from a spotless, stainless virgin, without the agency of human father--a pure body, untainted by intercourse with man. He, the Mighty One, the Artificer of all, Himself prepared this body in the virgin as a temple for Himself, and took it for His very own, as the instrument through which He was known and in which He dwelt. Thus, taking a body like our own, because all our bodies were liable to the corruption of death, He surrendered His body to death instead of all, and offered it to the Father. This He did out of sheer love for us, so that in His death all might die, and the law of death thereby be abolished because, having fulfilled in His body that for which it was appointed, it was thereafter voided of its power for men. This He did that He might turn again to incorruption men who had turned back to corruption, and make them alive through death by the appropriation of His body and by the grace of His resurrection. Thus He would make death to disappear from them as utterly as straw from fire.” (On the Incarnation: Saint Athanasius page 6)
The first Sabbath “Zewerede” is also known as “Adam’s Week.” The Lord and Savior Jesus Christ Came Down and Be Born from the Virgin Saint Mary, to search for Adam, raise him from his failure; take him out from hell and for the fulfillment of the prophecy. The Apostle Paul said, “But when the fullness of the time had come, God sent forth His Son, born of a woman, born under the law.” (Galatians 4:4)
ዘወረደ
እንኳን አደረሳችሁ!
ዘወረደ ማለት "ከላይ የመጣ፣ የወረደ'' ማለት ነው። ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን "ዘወረደ እምላዕሉ አይሁድ ሰቀሉ ወሚመ ኢያእመሩ እግዚአ ኩሉ ዘየሐዩ፤ አዳምን ለማዳን ከሰማይ የወረደውን አምላክ አይሁድ ሰቀሉት፤ የሰማይ ሥልጣን ያለው የሁሉ ጌታ እንደሆነም ምንም አላወቁም" እያለች በሰንበት ዋዜማ ዜማውን መሐትው (መግቢያ) አድርጋ የሳምንቱን ዜማ በማስተጋባት የጌታችንን ከሰማይ መውረድ ታመሠጥርበታለች፤ ታመሰግንበታለች። (ጾመ ድጓ፥ ዘዘወረደ ዋዜማ)
ይህን ሳምንት በልዕልና በዘለዓለማዊ ቅድስና እና በማትመረመር ጥበብ ራሱን ሰውሮ የሚኖር አምላክ በገሃድ ለሰው ልጅ የተገለጠበትን፣ ዘለዓለማዊ አምላክ ሰውን ከተደበቀበት ለመፈለግ ብሎ ''ኦ አዳም አይቴ ሀሎከ- አዳም ሆይ ወዴት ነህ" እያለ በማያልቅ የፍቅር ድምፅ ፍለጋ ወደ ዱር (ወደ ዓለም) የገባበትን ሳምንት የምንዘክርበት ነው። አምላካችን እግዚአብሔር የሰውን ልጅ ምን ያህል በበዛ ፍቅሩ እንደሚፈልገው፣ ከፍ ላለ ዓላማውም እንዳጨው ያሳየበት፣ ከሁሉም ደግሞ በሕሊና ሊታሰብ የማይችለውን የሰማይ አኗኗሩን ትቶ በሚታይ የአዳም ሥጋ የተገለጠበት፣ መጋረጃው እሳት፣ ዙፋኑ እሳት፣ ልብሱ እሳት የሆነው አምላክ በሚበሰብስ ሥጋ የተገለጠበት፣ በጨርቅ፣ ያንን የሚያስደነግጥ መለኮታዊ ክብሩን ስለ ሰው ልጅ መዳን ተጨንቆ በሕፃን አምሳል ተገልጦ በበረት የተገኘበትን ሳምንት እናስብበታለን። ቅዱስ አትናቴዎስ የእግዚአብሔር ልጅ ለሰው ልጅ ድኅነት ሲል መወለዱን እንዲህ በማለት ይገልጠዋል፡፡ "ለዚሁ ዓላማ (ለሰው ልጅ ድኅነት) የማይበሰብስ፣ የማይሞት አካል ያለው የእግዚአብሔር ልጅ ወደዚህ ዓለም ገባ" (On the Incarnation: Saint Athanasius page 6)
ዘወረደ ከዚህ ትርጉም ባለፈ የአዳም ሳምንት ተብሎ ይጠራል። አዳምን ከጠፋበት ሊፈልግ፣ ከወደቀበት ሊያነሣ፣ ከገባበት ሊያወጣ የትንቢቱ ጊዜ በደረሰ ሰዓት ከብላቴናይቱ ድንግል ተወልዶ ተስፋ አዳም ተፈጽሞበታልና። “ነገር ግን የዘመኑ ፍጻሜ በደረሰ ጊዜ እግዚአብሔር ከሴት የተወለደውን ከሕግም በታች የተወለደውን ልጁን ላከ፤" እንዲል ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ (ገላ.፬:፬)።
ሠለስቱ ምዕት በጸሎተ ሃይማኖት "ዘበእንቲአነ ለሰብእ ወበእንተ መድኃኒትነ ወረደ እምሰማያት፤ ተሰብአ ወተሰገወ እመንፈስ ቅዱስ ወእማርያም እምቅድስት ድንግል፤ ስለ እኛ ስለ ሰዎች እኛን ለማዳን ከሰማይ ወረደ በመንፈስ ቅዱስ ግብር ከቅድስት ድንግል ማርያም ፍጹም ሰው ሆነ" (ጸሎተ ሃይማኖት) እንዲሉ በሥጋ የአዳምን ዘር ለማዳን ሰው ሆኖ ለአዳም የገባውን ኪዳን ፈጸመ። የሥጋ ዘመዳችንም ሆነ። (ሃይማኖተ አበው ዘቅዱስ ጎርጎርዮስ)
ሌላኛው ይህ ሳምንት ጾመ ሕርቃል በመባል ይታወቃል። ይህም በ፮፻፲፬ ዓ.ም የፋርስ ንጉሥ ኪርዮስ ኢየሩሳሌምን ወርሮ፣ አብያተ ክርስቲያናትን ዘርፎ እና መዝብሮ ክርስቲያኖችን ማርኮ ንግሥት ዕሌኒ ካሠራችው ቤተ መቅደስ የክርስቶስን መስቀል ዲያቆናትን አሸክሞ በምርኮ ወሰደ። ከምርኮ ያመለጡ ክርስቲያኖች ወደ ሮሙ ንጉሥ ከ፲፬ ዓመት በኋላ በ፮፻፳፰ ዓ.ም ለንጉሥ ሕርቃል ጩኹታቸውን ያሰማሉ፤ እርሱም በፋርሱ ንጉሥ በኪርዮስ ላይ ድል አግኝቶ መስቀሉን መለሰላቸው። በሕገ ቤተ ክርስቲያን ‹‹ሰው የገደለ ዘመኑን ሁሉ ይጹም›› የሚል በሐዋርያት ስለተደነገገ የንጉሡን ዕድሜ ተከፋፍለው አንድ ሳምንት ደርሶባቸው ስለ ንጉሡ ጾመወለታል፤ በዚህም የእርሱ መታሰቢያ ይሆን ዘንድ ይህ ሳምንት ጾመ ሕርቃል በመባል ይጠራል። እኛም ይህንን ዋቢ አድርገን እንጾማለን። (ምንጭ፡- ስንክሳር ዘወርኀ መጋቢት ፲)
ዘወረደ ከአርብዓው ዕለት የሚካተት ባይሆንም ቤተ ክርስቲያን ትእዛዝ አድርጋ ከአርብዓው ዕለታት ጋር ደምራ እንድንጾም ሕግ ሠርታለታች። እኛም እንደ ፈቃድ ሳይሆን እንደ ትእዛዝ ተቀብለን እንጾማለን።
ቅዳሴ፡- ቅዳሴ እግዚእ
"ዘበእንቲአነ ለሰብእ ወበእንተ መድኃኒትነ ወረደ እምሰማያት፤ ተሰብአ ወተሰገወ እመንፈስ ቅዱስ ወእማርያም እምቅድስት ድንግል፤ ስለ እኛ ስለ ሰዎች እኛን ለማዳን ከሰማይ ወረደ በመንፈስ ቅዱስ ግብር ከቅድስት ድንግል ማርያም ፍጹም ሰው ሆነ፡፡" ወንጌል (ዮሐ.፫፥፲-፩፬)
ምስባክ ዘነግህ:- (መዝ.፪፥፲፩) "ዘበእንቲአነ ለሰብእ ወበእንተ መድኃኒትነ ወረደ እምሰማያት፤ ተሰብአ ወተሰገወ እመንፈስ ቅዱስ ወእማርያም እምቅድስት ድንግል፤ ስለ እኛ ስለ ሰዎች እኛን ለማዳን ከሰማይ ወረደ በመንፈስ ቅዱስ ግብር ከቅድስት ድንግል ማርያም ፍጹም ሰው ሆነ"
ምስባክ ዘቅዳሴ:- (መዝ.፪፥፲፩) “ተቀነዩ ለእግዚአብሔር፤ ወተሐሠዩ ሎቱ በረዓድ፤ አጽንዕዋ ለጥበብ ከመ ኢይትመዐዕ እግዚአብሔር፤ ለእግዚአብሔር በፍርሃት ተገዙ፤ በረዓድም ደስ ይበላችሁ፤ ጌታ እንዳይቆጣ ተግሣጹንም ተቀበሉ፡፡”
መልእክታት:-
ሠራኢ ዲያቆን ዕብ.፲፫፥፲፯
ንፍቅ ዲያቆን ያዕ. ፬፥፮- ፍጻሜው
ንፍቅ ካህን የሐዋ. ፳፭፥፲፫-ፍጻሜ
ስብሐት ለእግዚአብሔር፤ አሜን!
https://youtu.be/94wfdG3stKc?si=F8wkB7hMt2KEYQ93
የአርማንያ ሰማዕት |አርሴማ|
ለሰማያዊ ክብር በወንጌል|፪| ያስጌጠሽ
ለቃሉ ምስክር አምላክ የጠራሽ።
የአርማንያ ሰማዕት|፪| አርሴማ አንች ነሽ፣
አዝ...........
የምሥጢር ዋሻ ነሽ የሰማይ ሙሽራ፣
በዓለማት ሁሉ ክብርሽ የሚያበራ።
ምግባር|፪| እና እምነትን አስተባብረሽ ይዘሽ፣
በመንግሥተ ሰማይ አክሊል ተቀዳጀሽ።
አዝ.........
በእውነት ቢያምርም የሰው ልጅ ውበቱ፣
ምግባር ከታጣበት በሰማይ አባቱ።
ያልሆነለት|፪| እሱ ውበት ሃይማኖቱ፣
ብለሽ ተናግረሻል ይቀራል በከንቱ።
አዝ.....
የጽናት ምስክር ለቃለ ወንጌሉ ፣
ከሁሉ ይበልጣል የፈጣሪ ኃይሉ።
ጸንተው|፪| ለሚኖሩ በሃይማኖታቸው ፣
አርሴማ እናታችን አብነት ሆንሻቸው።
አዝ........
ለሰማያዊ ክብር ሰለሆንሽ ምክንያት፣
እኛ እንልሻለን የሁላችን እናት።
ለምናምን|፪| ሁሉ በምልጃ ኪዳንሽ፣
ምሕረትን አሰጪን ለምነሽ ከአምላክሽ።
አገልግሎቴን አከብራለሁ!
በእያንዳንዳችን ሕይወት ውስጥ “አገልግሎት” የሚለው ቃል በተለያየ መልኩ ሊገለጽ ይችላል፡፡ ሰው በግሉ፣ ከቤተ ሰቡ እንዲሁም ከማኅበረሰቡ ጋር ከሚያከናውናቸው ተግባራት ውስጥ “አገልግሎቴ” ብሎ የሚያስባቸው ምግባሮች ሊኖሩት ይችላሉ፡፡ ለዚህም ዕውቀት ይኑረው አይኑረው ለማወቅ ቢያዳግትም ከቤተ ክርስቲያን አስተምህሮ ግን አገልግሎትን ማወቅ፣ መረዳትና መተግበር እንዲችል ግንዛቤ መፍጠር ተገቢ ነው፡፡
ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ “የሰው ልጅ ሊያገለግል ነፍሱንም ለብዙዎች ቤዛ ሊሰጥ መጣ” በማለት በቅዱስ ወንጌል እንደ ነገረን ክርስቶስን የምንመስልበት፣ እርሱን ወደ መምሰል የምናድግበት፣ ነፍሳችንን ለእርሱ የምንሰጥበት የሕይወት መንገድ ነው። (ማቴ. ፳፥፳፰) ስለ ብዙዎቹ በሥጋም፣ በነፍስም፣ በመንፈስም መዛል ራስን ቤዛ አድርጎ በመስጠት የሰዎችን መንፈሳዊ ብስለት፣ ሥጋዊ ጥንካሬ እንዲያገኙ እግዚአብሔርን ደስ የምናሰኝበትና ከእግዚአብሔር ጋር የምንገናኝበት ሕይወት ነው። በቤተ ክርስቲያን አገልግሎት የምናገለግለው ሌሎችን ሰዎች ነው። ለሊሎች መኖር ሌሎችን ማገልገል ደግሞ ክርስቶስን መምሰል ነው።
ከምንም በላይ አስቀድሞ አገልግሎት ለአምላካችን እግዚአብሔር የሚፈጸም ነው፤ ሰውን በአርአያውና በአምሳሉ ሲፈጥረው በምስጋናና በውዳሴ ከመላእክት ጋር አንድ ሆነው ስሙን እንዲቀድሱ ክብሩን እንዲወርሱ ነው፡፡ ስለዚህም ሕገ እግዚአብሔርን እየጠበቅን፣ ሥርዓቱን እየፈጸምንና በመንፈሳዊ ሕይወት ውስጥ ለራስም ሆነ ለሌሎች የምናከናውነው በጎ ምግባር አገልግሎት እንለዋለን፡፡ ከጸሎት ጀምሮ የምንጾመው ጾም፣ የምንሰግደው ስግደት፣ የምንመጸውተው ምጽዋትና ለቤተ ክርስቲያን የምናቀርበው መባ ሁሉ ለፈጣሪያችን የሚቀርብ ነውና አገልግሎት ነው፡፡
በመንፈሳዊ ሕይወታችን በአንድም ይሁን በሌላ ምክንያት በጎውን አስበን ልንተገብር የምንችልው ስለ እግዚአብሔር ቅዱስ ቃል ማወቅና ተግባራዊ ክርስትናን መረዳት ስንችል ነው፡፡ በመሆኑም ከሁሉም ነገር በፊት የቤተ ክርስቲያንን ትምህርት ጠንቅቆ ማወቅ ይገባል፡፡ የፈጣሪያችንን ቅዱስ ፈቃድና ትእዛዝ ለመፈጸም የሚረዳንን አገልግሎታችንን ልናውቅና ልናከብርም ይገባናል፡፡
ለአገልግሎት የሚሰጥ ክብር
ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ለሮሜ ሰዎች በላከው መልእክቱ “ለእናንተም ለአሕዛብ እናገራለሁ። እኔ የአሕዛብ ሐዋርያ በሆንሁ መጠን ሥጋዬ የሆኑትን አስቀንቼ ምናልባት ከእነርሱ አንዳንዱን አድን እንደሆነ አገልግሎቴን አከብራለሁ” በማለት እንደተናገረው በክርስቶስ ክርስቲያን የተባልን ሰዎች ሁሉ በእግዚአብሔር ፊት ተቀባይነትና ተወዳጅነት ያለውን አገልግሎት እናከብር ዘንድ አለን፡፡ (ሮሜ ፲፩፥፲፫)
“አገልግሎቴን አከብራለሁ” ስንልም አገልግሎት የተሰጠን ሹመት ስለሆነ ሹመትን አለማክበር ደግሞ ከክብር ያወርዳል፤ ቅጣት ያመጣል፤ ከንጉሡ ማዕድና ከቤተ ክርስቲያን ኅብረት የሚለይ ስለሆነ አገልግሎትን ማክበር መንፈሳዊ ግዴታ ነው። የቂስ ልጅ የሚሆን ሳኦል ምንም እንኳን ሹመትን ወድዶ፣ ፈልጎ የተሾመ ባይሆንም የጠፉትን የአባቶቹን አህዮች ለመፈለግ እንደሄደ በእግዚአብሔር ፈቃድ በነቢዩ ሳሙኤል ተቀብቶ ቢነግሥም ከቅጣት እንዳልዳነ መጽሐፍ ቅዱስ በ፩ኛ ሳሙኤል ምዕራፍ ፱ ይነግረናል።
የቂስ ልጅ ሳኦል እግዚአብሔር በትልቅ ሕዝብ ላይ ሹሞት ሳለ ሹመቱን በአግባቡ ባለ መጠቀሙ እግዚአብሔር ናቀው፤ አቃለለው፤ መንግሥቱን አሳልፎ ሰጠበት። ዛሬም እግዚአብሔር እኔና እናንተን መርጦ በራሳችን ላይ እንዲሁም በሌሎች ሰዎች ላይ እንደ እየ አቅማችን መጠን ሹሞናል። ለዚህ ከመረጠን ደግሞ ሹመትን አክብሮ መታዘዝ ማገልገል የሁላችን ግዴታ ነው።
አገልግሎት ክርስቶስ ለእርሱ ላለን ፍቅር ማረጋገጫ አድርጎ ያቀረበልን ነው። ቅዱስ ጴጥሮስን ትወደኛለህ? በማለት ሦስት ጊዜ በመጠየቅ “ከወደድከኝ በጎቼን ጠብቅ” እንዳለው ሁሉ እኛም በአገልግሎት አባግዕ የተባሉ ምእመናንን ራሳችንን ጨምሮ በመጠበቅ (ጠብቆም ላልቶም ይነበብ) የተሰጠንን ኃላፊነት ልንወጣ ይገባናል። (ዮሐ.፳፩፥፲፯)
የማያነግሡት ንጉሥ የማያከብሩት ክቡር ማንም የማያበድረው ባለ ጸጋ ሲሆን አገልግሎታችንን ባናከብር ለእግዚአብሔር የሚቀርበት ኖሮ ሳይሆን እንድናገለግል የፈቀደልን፣ ኃይሉን፣ ጥበቡን፣ ማስተዋሉን የሰጠን፣ አበው በእራት ላይ ዳረጎት እንዲሉ በጸጋ ላይ ጸጋ በክብር ላይ ክብር የሚጨምርልን ከፍጹም ፍቅሩ የተነሣ ነው።
ይቆየን!
https://youtu.be/8UWUkNFHHCE?si=NoRSZtySzwCisiQW
የአበውን ርስት /አንሰጥም/(፪) አሳልፈን
እንኖራለን ጸንተን መስቀል ተሸክመን(፪)
እንኖራለን በእምነት ተደግፈን
ያ ኢይዝራኤላዊው ናቡቴ በሰማርያ
የወይኑ ፍሬ ናት የማንነቱ መለያ
አክአብ ድንበርተኛው በወይኗ ጎምጅቶ
ነቃቅሎ ሊጥላት ሊያጠፋት ሽቶ
ያችን መልካም እርሻ ባድማ ሊያደርጋት
ሊገዛት ወደደ በእጥፍ ሊለውጣት
አዝ= = = = =
ተኩላው ለምድ ለብሶ ገብቶ ከበረትሽ
አድብቶ ቢሰራም እንዲፈርስ ስርአትሽ
በሃይማኖት ቆመን ድል እንነሳዋለን
በርትዕት ተዋህዶ የኖሩትን ይዘን
አዝ= = = = =
ጠላት ቢከፋብን ያለ በደላችን
በብዙ መከራ ቢከበብ ዙሪያችን
በእመ ብርሃን ምልጃ ሁሉን እናልፋለን
በእግዚአብሔር ቸርነት በርስት እንኖራለን
አዝ= = = = =
ዛሬም በእኛ ዘመን አክአብ ተነስቷል
ርስት ድንበራችንን ቀን በቀን ይገፋል
እኛም ናቡቴ ነን ሰማዕት እንሆናለን
የተዋህዶን ርስት እናስከብራለን/(፪)"
አደራ አለብኝ!ዓለም አቀፍ የግቢ ጉባኤ ምሩቃን ኅብረት ጉባኤ
የ2017 ዓ.ም 1 ኛ ዙር ቨርቹዋል ጉባኤቀን፡ መስከረም 26/2017 ዓ.ም
ሰዓት፡ ምሽት 2፡00-3፡00
ሁሌም በየወሩ በግቢ ጉባኤያት ምሩቃን ዓለም አቀፍ ኅብረት የቴሌግራም ቻናል
https://youtu.be/GnvpjUnQD_0?si=FtJC4WYm5nfeeqCW
ወንሕነኒ ንትፈሣሕ ዮም ወንግበር በዓለ
በዛቲ ዕለት በዓለ እግዚእነ።
አዝ.........
የድኅነት ምክንያት የሕይወት መገኛ፣
ምልክታችን ነው የተሰጠን ለእኛ።
መስቀል ኃይላችን ነው ለሁሉ ሚያበራ፣
ነጻ የወጣበት አዳም ከመከራ።
አዝ....
ሥጋው ተቆርሶበት ደሙ የፈሰሰበት፣
ጥንተ ጠላታችን ድል የተነሣበት።
አምላክን የቻለ መስቀል ዕፀ ሕይወት፣
የነጻነት አርማ አዳም የዳነበት።
አዝ........
ያዕቆብ ባረከ ኤፍሬም ምናሴን።
በመስቀል አምሳያ ዘርግቶ እጆቹን።
ቀድሞ በነቢያት ምሥጢር ያናገረ፣
አማሌቃውያንን እንዲያ ያሳፈረ።
አዝ..........
ኃይል ያጎናጽፋል የመስቀሉ ምሥጢር ፣
የሙሴ ጦር ጋሻ ጠላት ሚያሳፍር።
ለቀደመ ክብር ዳግም አበቃቸው፣
የመስቀል ምልክት ኅይል ጸወን ሆናቸው።
አዝ.....
ወልድ ቢያፈስበት ደሙን በመስቀሉ፣
ተክሶ ቀረለት የአዳም በደሉ።
እኛ እናከብራለን አምነናል በቃሉ፣
ሕይወት ስለሰጠን ነገረ መስቀሉ።
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።
@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna
#ኢትዮጵያ
Last updated 2 months, 3 weeks ago
Last updated 2 months, 2 weeks ago
ይህ ስለ Manchester United መረጃዎችን የሚያገኙበት የ Telegram ቻናል ነው 🇪🇹
--------------------------------------------------------------
☞︎| ስለ ማንቸስተር ዩናይትድ ትኩስ መረጃዎች
☞| ቀጥታ ስርጭቶች ከየስታድየሞቹ
☞| የዝውውር ዜናዎች
☞| ስለ ማንችስተር ዩናይትድ ታሪኮች
📩 ለማስታወቂያ ስራ DM :- @Marcoabdu
Last updated 1 month, 1 week ago