Infinite Entertainment, Zero Cost: Get Your Free Books, Music, and Videos Today!

ኢትዮ መረጃ - NEWS

Description
ኢትዮጵያን መውደድ ባትችል አትጥላት

ማክበር ባትችል አታዋርዳት
ማራመድ ባትችል አታዘግያት
መጠበቅ ባትችል አትበትናት።
ይህን በማድረግ ታሪክ ባትሠራም ታሪክ አታበላሽም።

ለአስታየት @ethio_merjabot
@biruke_promotion
Advertising
We recommend to visit

ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ

Last updated hace 1 día, 17 horas

ለማንኛውም አስተያየት እና ጥቆማ 👉 @Esat_tv_comment_bot

🇪🇹ኢሳት የኢትዮጵያ አይን እና ጆሮ🇪🇹

Last updated hace 5 días, 6 horas

Last updated hace 5 días, 19 horas

4 days, 10 hours ago
**የአዉሮፓ ህብረት ፤ "የኢትዮጵያ መንግስት ለአመታት …

**የአዉሮፓ ህብረት ፤ "የኢትዮጵያ መንግስት ለአመታት በህብረቱ አባል ሀገራት ዉስጥ በህገወጥ መንገድ የኖሩ ዜጎቹን ለመመለስ ቸልተኛ ነበር" ሲል ኢትዮጵያዊያን ቪዛ የሚያገኙበትን መንገድ አጠበቀ

የኢትዮጵያ ዲፕሎማቶች እና ባለስልጣናት አሁን ለጉዞ ቪዛ መክፈል አለባቸውም ተብሏል**

የአዉሮፓ ህብረት ፤ የኢትዮጵያ መንግስት ለአመታት በህብረቱ አባል ሀገራት ዉስጥ በህገወጥ መንገድ የኖሩ ዜጎቹን ለመመለስ ቸልተኛ ነበር ሲል ወቅሷል። በዚህም የተነሳ ኢትዮጵያዊያን ቪዛ የሚያገኙበትን መንገድ ማጥበቁን አስታዉቋል።

ዳጉ ጆርናል ከአሶሴትድ ፕረስ ዘገባ እንደተመለከተው ፤ የአውሮፓ ህብረት ዋና መስሪያ ቤት ለኢትዮጵያውያን ዜጎች ቪዛ ለመስራት የሚፈጅባቸዉን ጊዜ በሶስት እጥፍ መጨመሩን ነዉ።

ከዚህ ቀደም ኢትዮጵያዊያን በ15 ቀናት ዉስጥ ቪዛ ያገኙ ነበር የተባለ ሲሆን በዚሁ ዉሳኔ መሰረት ወደ 45 ቀናት ከፍ እንዲል ተደርጓል። ይህም የኢትዮጵያ መንግስትን በህገወጥ መንገድ በአዉሮፓ ይኖራሉ የተባሉ ዜጎችን እንዲመልስ ጫና ለመፍጠር ነዉ ብሏል ዘገባው።

ወደ ኢትዮጵያ እንዲመለሱ ከታዘዙ ሶስት ሰዎች መካከልም አንዱ ብቻ መመለሱ በህብረቱ የመንግስትን ተባባሪነት ጎድሎታል የሚለዉን ክስ ለማሳያነት ቀርቧል። ይህም በፈቃዳቸዉም ይሆን ካለፍላጎታቸዉ ህገወጦችን ለመመለስ የሚደረገዉን ሂደት አጓቶታል ብሏል።

በዚህ ዉሳኔ መሰረትም የኢትዮጵያ ዲፕሎማቶች እና ባለስልጣናት አሁን ለጉዞ ቪዛ እንዲከፍሉ ይገደዳሉ መባሉን ዳጉ ጆርናል ከዘገባው ተመልክቷል። አብዛኞቹ ኢትዮጵያዊያን የቪዛ ቀናቸዉም ቢያልፍ የአዉሮፓ ምድርን ለቅቀዉ እንደማይወጡ ህብረቱ ገልጿል።

@sheger_press
@sheger_press

4 days, 15 hours ago

የዩትዩብ ገፃችንን subscribe በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ👇👇
https://youtube.com/@Megenagnadaily?si=hYe79ngYPK8k3nbM

4 days, 20 hours ago

በትግራይ ታጣቂዎች ቁጥጥር ስር በዋሉ የራያ እና አላማጣ አካባቢዎች ህይወት ምን ይመስላል?

ካሳለፍነው ሳምንት ጀምሮ የትግራይ ታጣቂዎች ወደ ራያ እና አላማጣ አካባቢዎች መግባታቸውን ተከትሎ የዳግም ጦርነት ስጋት ደቅኗል።

የአማራ ክልል በህወሃት ታጣቂዎች ወረራ ተፈጽሞብኛል ቢልም የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳድር ግን ተግሩን እየፈጸሙ ያት የፕሪቶርያ የሰላም ስምምነት ጠላቶች ናቸው ብሏል።

የራያ እና አላማጣ አካባቢ ነዋሪዎች በፌደራል መንግስት “ተከድተናል የሚል ስሜት ውስጥ መግባታቸውን” ተናግረዋል።

የትግራይ ታጣቂዎች ከአላማጣ 15 ኪሎ ሜት ራዲያስ ውስጥ ሆነው በየቀኑ ተጨማሪ ሀይል እያስገቡ እንደሆነም ነው ነዋሪዎቹ የሚናገሩት።

ካሳለፍነው ሳምንት ጀምሮ የትግራይ ታጣቂዎች ወደ ራያ እና አላማጣ አካባቢዎች መግባታቸውን ተከትሎ የዳግም ጦርነት ስጋት ደቅኗል።

የአማራ ክልል በህወሃት ታጣቂዎች ወረራ ተፈጽሞብኛል ቢልም የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳድር ግን ተግሩን እየፈጸሙ ያት የፕሪቶርያ የሰላም ስምምነት ጠላቶች ናቸው ብሏል።

የራያ እና አላማጣ አካባቢ ነዋሪዎች በፌደራል መንግስት “ተከድተናል የሚል ስሜት ውስጥ መግባታቸውን” ተናግረዋል።

የትግራይ ታጣቂዎች ከአላማጣ 15 ኪሎ ሜት ራዲያስ ውስጥ ሆነው በየቀኑ ተጨማሪ ሀይል እያስገቡ እንደሆነም ነው ነዋሪዎቹ የሚናገሩት።

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news

1 week, 5 days ago
ትጥቅ አንግበው የሚታገሉ አካላት ወደ ሀገራዊ …

ትጥቅ አንግበው የሚታገሉ አካላት ወደ ሀገራዊ ምክክር መድረክ እንዲመጡ ጥሪ ቀረበ

ትጥቅ አንግበው የሚታገሉ አካላት ወደ ሀገራዊ ምክክሩ መድረኮች እንዲመጡ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ጥሪ አቀረበ፡፡

ግጭት ሕይወትና ንብረትን ያጠፋል እንጂ ችግርን እንደማይፈታ የገለጹት የኮሚሽኑ ምክትል ዋና ኮሚሽነር ሂሩት ገ/ሥላሴ÷ ታሪካዊ አጋጣሚ በሆነው ሀገራዊ ምክክር በመሳተፍ ሐሳብን በማቅረብ መግባባት እንደሚገባ አስገንዝበዋል፡፡

በዚህም ትጥቅ አንግበው እየታገሉ ያሉ አካላት ወደ ምክክሩ እንዲመጡ ከፍተኛ ጥረት ሲደረግ መቆየቱን አስታውሰው÷ አሁንም ወደ ምክክሩ እንዲመጡ በመጠየቅ ሲመጡም ጥበቃ እንደሚደረግላቸው አረጋግጠዋል፡፡

ኮሚሽኑ የሚያመቻቻቸው መድረኮችም ማንኛውም ሰው በነጻነት የሚሳተፍባቸው መሆናቸውን አስረድተው÷ ትጥቅ አንግበው የሚታገሉ አካላት ወደ ሀገራዊ ምክክር መድረኩ እንዲመጡ ጥሪ አቅርበዋል፡፡(ኤፍ ቢ ሲ)

@ethio_mereja_news

1 week, 5 days ago

**ቀሲስ በላይ መኮንን ከሰሞኑ "ተሳትፈዉበታል" በተባለው የማጭበርበር ድርጊት የተነሳ የአፍሪካ ህብረት የዉጪ ምንዛሬ የሚያስቀምጥበትን የባንክ ሂሳብ ከኢትዮጵያ ዉጪ ለማድረግ እንዳሰበ ተሰማ

👉🏼 ህብረቱ ለሶስተኛ ጊዜ በሀሰተኛ ሰነድ ልጭበረበር ነበር ያለ ሲሆን "ታማኝ" በተባሉ ሰዎች የተፈጸመው ሙከራ ወደፊት "በባለስልጣናት ላለመሞከሩ ማረጋገጫ ስለሌለኝ ነዉም" ብሏል**
ከሰሞኑ ቀሲስ በላይ መኮንን በሀተኛ ሰነድ 6 ሚሊዮን 50 ሺህ የአሜሪካን ዶላር ገንዘብ ለማዘዋወር ሞክረዋል መባላቸውን ዳጉ ጆርናል ተከታታይ መረጃዎችን አድርሷል። ይህንኑ ተከትሎ ቀሲስ በላይ የተጠረጠሩበት ድርጊት መነጋገሪያ ሆኖ የቆየ ሲሆን ዘ ሪፖርተር ደግሞ አዲስ መረጃ አጋርቷል።

ቀሲስ በላይ በአፍሪካ ህብረት ቅጥር ጊቢ ዉስጥ በሚገኝ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ቅርንጫፍ በመገኘት ሀሰተኛ ሰነድ በመጠቀም ከህብረቱ የሂሳብ ቁጥር ለግንባታ እና ሌሎች ስራዎች ክፍያ በሚል 6 ሚሊዮን 50 ሺህ ዶላር ለማዘዋወር ሲሞክሩ በቁጥጥር ስር ዉለዋል።

ስማቸዉ ያልተጠቀሰ የዘ ሪፖርተር ምንጭ ታድያ ይህንን ድርጊት ተከትሎ የአፍሪካ ህብረት የዉጪ ምንዛሬ የሚያስቀምጥበትን የባንክ ሂሳብ ከኢትዮጵያ ዉጪ ለማድረግ እንዳሰበ ተናግረዋል። ህብረቱ ለሶስተኛ ጊዜ በተጭበረበረ ሰነድ ከባንክ ሂሳቡ ሊወጣ የነበረ ገንዘብን በቁጥጥር ስር ማዋል መቻሉን ያስታወቀ ቢሆንም "እምነትና እዉቅና" ባላቸዉ ሰዎች የተፈጸመዉ ተግባር ወደፊት በባለስልጣናት ለላመሞከሩ መተማመኛ የለኝም በማለቱ መሆኑን ዘገባው አመላክቷል።

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ቅርንጫፍ በአፍሪካ ህብረት ቅጥር ጊቢ ዉስጥ ያለዉ ቅርንጫፉ ከሁለት አስርት ዓመታት በፊት የተከፈተ ሲሆን በዋነኛነት የአፍሪካ ሒሳቦችን በተለይ ለማስተዳደር ነው። ከዚያን ጊዜ ጀምሮም የአፍሪካ የበሽታ መቆጣጠሪያ ማዕከልን ጨምሮ የተቋሙ ከፍተኛ የዉጭ ምንዛሪ ክምችት ያላቸዉ አካውንቶችን በማካተት ቁጥጥር ያደርጋል።

ቀሲስ በላይ በወቅቱ ሀሰተኛ የህብረቱ ማህተም ያረፈባቸዉን ወረቀቶች በመያዝ ለግባታ እና የማሽነሪዎች አቅርቦት በሚል ክፍያዉን መጠየቃቸውን ዳጉ ጆርናል ከዘገባው ተመልክቷል። ክፍያዉ ከመፈጸሙ በፊት ወደ ህብረቱ የስልክ ጥሪ ያደረጉት የባንኩ ሰራኞች የክፍያዉን ትክክለኛነት ለማረጋገጥ ሲሞክሩ የህብረቱ የፋይናንስ ክፍል የማያዉቀዉ መሆኑን እና ክፍያዉ እንዲታገድ ህብረቱ መጠየቁ መረጃዉ ይደርሳቸዋል።

ህብረቱ ይህንን ተከትሎም ግለሰቡ እንዲያዙለት ጠይቆ ቀሲስ በላይ በህብረቱ ጠባቂዎች በቁጥጥር ስር ዉለዉ በፌዴራል ፖሊስ ተላልፈዉ መሰጠታቸዉን ዳጉ ጆርናል መዘገቡ ይታወሳል።

የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን የፋይናንሺያል አስተዳደር ዲቪዥን ኃላፊ ማዳሊስቶ ሙኡሶ ሎሌም ወዲያውኑ ለፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን የወንጀል እና የትራፊክ አደጋ ምርመራ ክፍል ደብዳቤ ጽፈዋል ብሏል ዘገባዉ። ኃላፊዉ የተለያየ መጠን ያለው ገንዘብ ከአፍሪካ ህብረት ሒሳብ ወደ አራት ግለሰቦች ሒሳብ እንዲዘዋወር የጠየቁ ሰነዶች ሁሉም ፎርጂድ ናቸው ብለዋል በጻፉት ደብዳቤ።

ከዚህ ክስተት በኋላ የህብረቱ እና የባንኩ  ሰራተኞች ለፖሊስ ቃላቸዉን መስጠታቸው በዘገባዉ ተጠቅሷል።

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፕሬዚዳንት አቤ ሳኖ ለዜና ምንጩ ከሰጡት ቃል ዳጉ ጆርናል እንደተመለከተው "በመሠረቱ ጥሬ ገንዘብ በውጭ ምንዛሪ ብቻ ሊሰጥ አይችልም ። ለማጭበርበር የሞከረዉም ግለሰብ መጥቶ መጠኑን በጥሬ ገንዘብ ሲጠይቅ ይህን እንኳን አያውቅም ነበር ማለታቸዉን ነዉ።

አክለዉም " ግለሰቡ እዚህ አገር የዶላር አካውንት ከሌለው ገንዘቡ ቢተላለፍም እንኳ የትም ሊደርስ አይችልም።  አጭበርባሪዎች በየቀኑ ወደ ባንካችን ይመጣሉ።  ባንክ ስለምንሰራ የተለመደ ነው።  እኛ ግን ሁልጊዜ ከመሳካታቸው በፊት እናጣራለን።  ለፍርድም እየወሰድናቸው ነው። የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የደንበኞቹን ሒሳቦች የመጠበቅ ኃላፊነት አለበት።  ያንንን እያደረግን ነው።  የአፍሪካ ህብረትም እስካሁን ድረስ ቀጥተኛ ቅሬታ አላቀረበብንም" ሲሉ አቶ አቤ መናገራቸውን ዳጉ ጆርናል ተመልክቷል።

"ማጭበርበር ሲያጋጥም ይህ ለሶስተኛ ጊዜ ነው" ያሉት ስማቸው ያልተጠቀሱት የዜና ወኪሉ የአፍሪካ ህብረት ምንጭ" አሁን ማጭበርበሩ በተከበሩ ሰዎች እየተሞከረ ስለሆነ ተጨንቀናል" ብለዋል። ይህ ድርጊት  "ባለስልጣናት አንድ ቀን ተመሳሳይ ነገር ላለማድረጋቸዉ ምንም አይነት ዋስትና የለንም" ያሉም ሲሆን  "እምነት እያጣን ነው" ብለዋል።

ባለስልጣኑ አክለዉም በዚህ የተነሳ "ኢትዮጵያ ውስጥ ለደሞዝ አነስተኛ መጠን ያለው ፎሬክስ(የዉጪ ምንዛሪ ) ለመያዝ ወስነናል ፤ የድርጅቱን ገንዘብ ከኢትዮጵያ ውጭ ማቆየት እንድናስብ ያስገድደናል" ሲሉ ስማቸው እንዳይገለጽ የፈለጉ የአፍሪካ ህብረት ባለስልጣን መናገራቸውን ዳጉ ጆርና ከዘገባው ተመልክቷል።

Via The Reporter

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news

1 week, 5 days ago

መርጌታ  በረከት ነኝ
0948166390

1🌿 መፍትሔ_ሥራይ (የጠላት ድግምት መሻሪያ)
2🌿ለቡዳ
3🌿ለቁራኛ
4🌿 #መጠብቅ (ከጠላት ከሚላክ ሟርት የሚጠብቅ)
5🌿ለጋኔን
6🌿ለማንኛውም ዓይነት በሽታ መፍትሔ
7🌿ለራእይ (በህልም የሚያሳይ)
8🌿  ለፀር (ለጠላት)
9🌿ዓቃቤ_ርእስ (ጠላት እንዳይጎዳን የሚጠብቅ)
10🌿 ለዘኢያገድፍ (ለትምህርት የማያስጠፋ የማያስጥል)
12🌿ለመፍትሔ_ሀብት(ሀብቱ በጠላት ድግምት ለተሰወረበት)
13🌿 መስተፋቅር
16🌿ለሌባ(እንዳንሰረቅ እንዳንዘረፍ የሚጠብቅ)
17🌿የትዳር አጋር ላጣ ወይም ላጣች
የሚያስገኝ
18🌿ለምስያጥ ለገበያ (ገበያ እንዲቀናን እንድናገኝ)
21🌿ለዓይነ_ጥላ (የፍራቻ መንፈስ ማስለቀቂያ)
22🌿ለልሳነ_ሰብእ
23🌿ለበረከት
24🌿ለእግረ_መልስ (ጥሎ ለጠፋ ሰው መመለሻ ማምጫ)
26🌿ጸሎተ_ዕለታት
27🌿ለጽሑፍ ለስእል ለከበሮ ለበገና ለክራር በእጂ ለሚሰሩ
28🌿ንባብ ስናነብ ቀልጣፋ የሚያረግ
29🌿ለከበሮ
31🌿ለሙግት
36🌿ለጥይት (ጥይት የማያስመታ)
37🌿ለዱላ( ዱላ የማያስመታ)
38🌿መንስኤ_እስኪት (ለወንድ የመራቢያ አካሉ ለደከመ ላነሰ)
40🌿ለአይነ_ሰብእ (ከሰው አይን የሚጠብቅ)

በ0948166390
ይደውሉልንወይም በውሥጥ መሥመር  በመጫን ያውሩን
👇👇👇👇👇https://t.me/+elwAyVGFAiY4OWRk

2 months, 1 week ago

እናት ፓርቲ፣ መኢአድ፣ ኢሕአፓና አንድ ኢትዮጵያ ዲሞክራሲያዊ ፓርቲ፣ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የተመሳሳይ ጾታ ግንኙነትን ያበረታታል የተባለውንና የአፍሪካ፣ ካሪቢያንና ፓሲፊክ አገራት ከአውሮፓ ኅብረት ጋር የተፈራረሙት የሳሞአ የንግድና ኢኮኖሚ ትብብር ስምምነት እንዳያጸድቅ ዛሬ ባወጡት መግለጫ ጠይቀዋል።

ፓርቲዎቹ፣ ኢትዮጵያ የፈረመችውን ይሄንኑ ስምምነት "ትውልድ አምካኝ" እና "አገር እና ማንነትን አጥፊ" ብለውታል። ምክር ቤቱ የስምምነቱን መጽደቅ ማስቀረት ካልቻለ፣ ቢያንስ ከግብረ ሰዶም ጋር የተያያዙ አንቀጾች ከስምምነቱ "እንዲወገዱ" ወይም "እንዲታረሙ" እንዲያደርግ ፓርቲዎቹ ጠይቀዋል።

ስምምነቱ "ለግብረ ሰዶምና ግብረ ሰዶማዊነት በተዘዋዋሪ መልኩ ጥበቃ የሚያደርጉ፣ የሚደግፉና የሚያበረታቱ" አንቀጾችን አካቷል ያሉት ፓርቲዎቹ፣ ኢትዮጵያ ስምምነቱን እንዳታጸድቅ የኢትዮጵያ ኃይማኖት ተቋማት ጉባዔ በጋራና የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን በተናጥል ጭምር ያሰሙት ተቃውሞ በከንቱ ሊታለፍ እንደማይገባም አሳስበዋል።

ምክር ቤቱ የሳሞአ ስምምነትን ካጸደቀ ግን፣ "የታሪክ ተጠያቂነት ይከተለዋል" በማለት ፓርቲዎቹ አስጠንቅቀዋል። የኢትዮጵያ ወንጀለኛ መቅጫ ሕግ የግብረ ሰዶማዊነት ተግባርን ወንጀል አድርጎ ደንግጓል።

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news

2 months, 1 week ago

የዕድሜ ልክ እስራት ተፈረዶበት፡፡

የኢትዮጵያ መንግስት ሰኞ ዕለት እንዳስታወቀዉ 41 የአልሸባብ ቡድን አባላት እስራት ተፈርዶባቸዋል፡፡

ፍርዱ ከተላለፋቸው መካከል የወታደራዊ መሪዉ የዕድሜ ልክ እስራት ተፈርዶበታል ነዉ የተባለዉ፡፡

ብይኑን የሰጠዉ በድሬዳዋ የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት 4ኛ ምድብ ችሎት ሲሆን፤ ተከሳሾቹ የመከላከያ ምስክር አላቀረቡም በሚል የቅጣት ውሳኔ የተላለፈባቸው ናቸው፡፡

ሁሴን አልመድ/ኤሊያስ ሁሴን/ የመጀመሪያ ተከሳሽ ሲሆን፤ እንደ መንግስት ገለጻ ከሆነ ለአሸባሪዉ ቡድን እንደ መሪ ሆኖ ሲሰራ ነበር፡፡

ሁለተኛዉ ተከሳሽ  ኢብራሂም ጂብሪል የሚባል ሲሆን የበታች ወታደራዊ መሪ ነበር ተብሏል፡፡

የፍትህ ሚኒስቴር የድንበር ተሻጋሪ የወንጀል ጉዳዮች ክፍል ዳይሬክቶሬት ጄኔራል 57 ምስክሮችን እንዲሁም 3መቶ96 የጽሁፍ ማስረጃዎችን ከተመለከተ በኋላ በሽብርተኝነት ወንጀል ክስ መስርቶባቸዉ ነበር፡፡

ሁሉም 41 ተከሳሾች ከ2019 ጀምሮ ሶማሊያ የሚገኘዉ የአልሸባብ አሸባሪ ቡድን አባላት ናቸዉ ያለ ሲሆን፤ ልምምዳቸዉን ካጠናቀቁ በኋላ በ2021 በኢትዮጵያ ሶማሌ ክልል በተፈጸመ ጥቃት ተሳታፊ ነበሩ ብሏል፡፡

በአፍዴር ዞን የተለያዩ አከባቢዎች በስፋት ሲንቀሳቀሱ እንደነበር ደርሼበታለሁ ያለዉ ዳይሬክቶሬቱ፤ በኢትዮጵያ የሽብር ወንጀል ለመፈጸም በማሰብ አብዛኛዎቹ የጦር መሳሪያዎችን ጭምር ሲያቀርቡ ነበር ነዉ ያለዉ፡፡

በወቅቱም 2መቶ65 ንጹህን ዜጎች ህይወታቸዉ ሲያልፍ የሶማሌ ክልል ልዩ ሃይል አባላትን ጨምሮ 3መቶ23 ሌሎች ዜጎች ጉዳት ደርሶባቸዋል፡፡

የኢትዮጵያ መንግስት እንደሚገልጸዉ ደግሞ 13 ሚሊየን 5መቶ ሺህ የሚደርስ የኢትዮጵያ ብር የንብረት ዉድመት ደርሷል ነዉ የተባለዉ፡፡

ተከሳሾቹ ከሽብርተኝነት ወንጀል በተጨማሪ ደግሞ የአልሸባብ ቡድን አባላት በመሆናቸዉም ጭምር ክስ ቀርቦባቸዋል፡፡

መንግስት እንደሚለዉ ከሆነ ተከሰሾቹ 5ጊዜ የመከላከያ ምስክር እንዲያቀርቡ ዕድል ተሰጥቷቸዉ ነበር፡፡

የቡድኑ መሪ ሁሴን አልመድ የዕድሜ ልክ እስራት ሲፈረድበት፤ 19 ተከሰሾች 11 እና 12 አመት ያለ ይግባኝ፤ 8 ተከሳሾች 8 እና 9 ዓመት እንዲሁ ያለ ይግባኝ እና ቀሪ 10 ተከሰሾች ደግሞ 7 እና 8 ዓመት ያለ ይግባኝ ተፈርዶባቸዋል፡፡(ኢትዮ ኤፍ ኤም)

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news

2 months, 1 week ago

መንግስት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን ሰላማዊ ተቃዋሚዎችን ዝም ለማሰኘት ተጠቅሞበታል ሲል ከሰሰ‼️

አምነስቲ ኢንተርናሽናል ባወጣው መግለጫ የኢትዮጵያ መንግስት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን "ታዋቂ ፖለቲከኞችን እና ጋዜጠኞችን" በማሰር ሰላማዊ ተቃዋሚዎችን ለማፈን ተጠቅሟል ሲል ከሷል።

በአማራ ክልል ባለፈው አመት ሀምሌ ወር የታወጀው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ጊዜው ሲጠናቀቅ መንግስት "የሚቀሩ ሰራዎች" መኖራቸውን በመጥቀስ ጥር መጨረሻ ለተጨማሪ አራት ወራት እንዲራዘም አድርጎታል።

የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን መራዘም የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን(ኢሰመኮ)፣ የአውሮፖ ህብረት እና አሜሪካ በሰብአዊ መብት ጉዳይ ችግር ይፈጥራል ሲሉ ስጋታቸውን መግለጻቸው ይታወሳል።አምነስቲ ኢንተርናሽናል አዋጁ ተግባራዊ በሆነባቸው ባለፉት ስድስት ወራት የመንግስት ባለስልጣናት ተጠርጣሪዎችን ያለፍርድ ቤት ትዕዛዝ እንዲይዙ፣ ሰአት እላፊ እንዲጥሉ፣ የመንቀሳቀስ መብት እንዲገድቡ እና ህዝባዊ ስብሰባ እንዲከለክሉ እንዳስቻላቸው ገልጿል።

በመግለጫው የድርጅቱ የምስራቅ እና የደቡባዊ አፍሪካ ቀጣና ዳይሬክተር ቲገሬ ቻንጉታህ መንግስት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን ሰበብ በማድረግ መሰረታዊ መብቶችን መገደብ ማቆም አለበት ብለዋል።ዳይሬክተራ አክለውም እንደገለጹተ "የተራዘመው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ገና በነጋሪት ጋዜጣ አልታተመም። ይህ የግልጽነት ችግር መረጃ የማግኘት እና የህጋዊነት መርህን የሚጥስ ነው እንዲሁም ኢትዮጵያውን ህግ እየተከበረ ስለመሆኑ እንዳያውቁ ያደርጋቸዋል።"

ድርጅቱ በመጀመሪያው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ስድሰት ወራት ወቅት እና ከተራዘመ በኋላ መንግስትን የተቹ አምስት ፖለቲከኞች እና ሶስት ጋዜጠኞች መታሰራቸውን ከቤተሰቦቻቸው ማረጋጠጡን ጠቅሷል።ድርጅቱ እንደገለጸው የታሰሩት ፖለቲከኞች የህዝብ ተወካዮች ምክርቤት አባሉ አቶ ክርስቲያን ታደለ፣ የአዲስ አበባ ምክር ቤት አባሉ አቶ ካሳ ተሻገር፣ የአማራ ክልል ምክር ቤት አባሉ አቶ ዩሀንስ ባያለው፣ የቀድሞ የሰላም ሚኒስቴር ዲኤታ ታየ ደንደአ ሲሆኑ የታሰሩት ጋዜጠኞች ደግሞ አባይ ዘውድ፣ በቃሉ አላምረው እና በላይ ማናየ ናቸው።

ድርጅት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ከተራዘመ በኋላ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይን በመተቸት የሚታወቁትን የህዝብ ተወካዮች ምክርቤት አባል የነበሩት ዶክተር ደሳለኝ ጫኔን ማሰሩን ገልጿል።
ዳይሬክተሯ የመንግሰት ባለስለጣናት በጅምላ ማሰራቸውንም ማቆም አለባቸው ብለዋል።ዳሬክተሯ መንግስት ታዊቂ ፖለቲከኞችን እና ጋዜጠኞችን ጨምሮ ሁሉም በአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ የታሰሩ ሰዎች ክስ እንዲመሰረትባቸው ወይም እንዲለቀቁ በማድረግ ሀገራዊ አለምአቀፋዊ ህጎችን ማክበር እንደሚገባው አሳስበዋል።

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news

2 months, 2 weeks ago
የጣይቱ ትምህርት እና ባህል ማእከል ወደ …

የጣይቱ ትምህርት እና ባህል ማእከል  ወደ አገልግሎቱ ሊመለስ ነው‼️

የጣይቱ ትምህርት እና ባህል ማእከል ከአዲስ አበባ ከተማ መስተዳድር ተረክቦት የነበረዉን  120 አመት ያስቆጠረን የቅርስ ቤት የእድሳት ስራ 95% ማጠናቀቁን አስታውቋል።

በአዲስ አበባ ከተማ የቀድሞ አራዳ ምድብ ችሎት ግቢ ዉስጥ የሚገኘዉ የቢትወደድ ሀይለጊርጊስ ወ/ሚካኤል መኖሪያ ቤት የነበረዉ እና የመጀመሪያ ማዘጋጃ ቤት በመሆን ያገለገለው  ጥንታዊ ቤት እድሳት 95 በመቶ የሚሆነዉን ስራ ማጠናቀቁን ማእከሉ በሰጠዉ ጋዜጣዊ መግለጫ ተገልፆል።

ከፍተኛ የቅርፅ ባለሙያዎች ጥናት  እና ከቦታዉ ጋር የሚመጥን የማስፋፊያ ዲዛይን  ተደርጎበታል የተባለው ባህል ማእከልን   ለማጠናቀቅ ሁለት አመት እንደፈጀ ለማወቅ ተችሏል።

ምንም አይነት እድሳት ሳይደረግለት በመቆየቱ  የእድሳት   ሂደቱን አስቸጋሪ  አድርጎታል  የተባለ   ሲሆን የቅርስ ይዘቱን ሳይለቅ ለማደስ ሲባል የጥሬ እቃዎችን ለማግኘት አስቸጋሪ እንደነበር ግንባታዉን የመሩት አቶ ተስፋዬ አዶላ ለኢትዩ  ኤፍኤም    ገልፀዋል።

በአርቲስት አለምፀሀይ ወዳጆ ሀሳብ አመንጪነት ቦታዉን ወደ ባህል ማእከልነት ለመቀየር በማሰብ  በ 2011 ዓ.ም ከ/ከተማ መስተዳድር  ቦታዉን መረከቡ የሚታወስ ነዉ፡፡

ቀሪ ለማእከሉ የሚያስፈልጉ የመብራት ገጠማ እና ሌሎች ስራዎችን በመጨረስ በቅርብ ጊዜ ለአገልግሎት ክፍት እንደሚደረግ እና ለከተማውም አማራጭ የቱሪስት መዳረሻ እንደሚሆን ተጠብቋል።

We recommend to visit

ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ

Last updated hace 1 día, 17 horas

ለማንኛውም አስተያየት እና ጥቆማ 👉 @Esat_tv_comment_bot

🇪🇹ኢሳት የኢትዮጵያ አይን እና ጆሮ🇪🇹

Last updated hace 5 días, 6 horas

Last updated hace 5 días, 19 horas