ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።
@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna
#ኢትዮጵያ
Last updated 2 months, 3 weeks ago
Last updated 2 months, 2 weeks ago
ይህ ስለ Manchester United መረጃዎችን የሚያገኙበት የ Telegram ቻናል ነው 🇪🇹
--------------------------------------------------------------
☞︎| ስለ ማንቸስተር ዩናይትድ ትኩስ መረጃዎች
☞| ቀጥታ ስርጭቶች ከየስታድየሞቹ
☞| የዝውውር ዜናዎች
☞| ስለ ማንችስተር ዩናይትድ ታሪኮች
📩 ለማስታወቂያ ስራ DM :- @Marcoabdu
Last updated 1 month, 1 week ago
በትግራይ ክልል ጊዝያዊ ምክር ቤት ተቋቋመ
በትግራይን ክልል የዛሬ ሁለት ሳምንት ገደማ የተቋቋመውን ጊዝያዊ አማካሪ ካውንስል የሚተካ ጊዝያዊ ምክር ቤት ነው በዛሬው ዕለት የተቋቋመው።
የትግራይ ጊዝያዊ አስተዳደር አማካሪ ካውንስል የተቋቋመበትን ደምብ ቁጥር 10/2016 የተሻሻለም ሲሆን በዛሬው ዕለት በተደረገ ስብሰባም በ53 የድጋፍ ድምፅ፣ በአንድ ተቃውሞና ሁለት ድምፀ ተአቅቦ አማካሪ ካውንስሉ ፈርሶ ጊዝያዊ ምክርቤት በይፋ ተቋቁሟል።
የአማካሪ ካውንስል ምስራተው የክልሉ መደበኛ ምክር ቤት በፕሪቶርያው ስምምነት መሰረት መፍረሱ ተከትሎ የትግራይ ጊዝያዊ አስተዳደር ማቋቋምያ ሰነድ ጥር 2015 ዓ/ም ሲፀድቅ የተነሳ ሀሳብ መሆነለ ይታወሳል።
ህገወጥ ኬላዎችን የማስነሳት ኃላፊነት የክልል መንግስታት ቢሆንም በአግባቡ ግን ተፈፃሚ መሆን አልቻለም ሲል የጉምሩክ ኮሚሽን አስታወቀ!
ኮሚሽኑ እንዳለው በኢትዮጵያ የንግድ ቁጥጥር ኬላን የማቋቋም እና የማስተዳደር ስልጣን የፌደራል መንግስት ቢሆንም በየአካባቢው ህገ-ወጥ ኬላዎች ተዘርግተው የንግድ እንቅስቃሴን እያወኩ መሆኑን አረጋግጧል።ይህን ተከትሎ በኢትዮጵያ ትላልቅ የንግድ መስመሮች የማላውቃቸው ከ280 በላይ ህገ-ወጥ ኬላዎች ተዘርግተው አግኝቻለው ብሏል።
የጉምሩክ ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ ደበሌ ቀበታ በየአካበቢው የተዘረጉ እነዚህን ኬላዎች ለማስነሳት የክልል መንግስታት ሀላፊነት የተሰጣቸው ቢሆንም በአግባቡ አልተፈፀመም ሲሉ የአሰራር ሂደቱን ተችተዋል።እነዚህን ኬላዎች ያቋቋሙት አካላት ተገቢ ባልሆነ መልኩ ገንዘብ እየሰበሰቡ መሆኑን የጠቀሱት ኮሚሽነሩ ነጋዴዎች በአንድ መስመር ብቻ ተደጋጋሚ ቀረጥ እንዲከፍሉ እየተገደዱ መሆኑንም ማስረዳታቸውን ካፒታል ከኢትዮጵያ ራዲዮ ያገኘው መረጃ ያመላክታል።
Via Capital
@YeneTube @FikerAssefa
አቅመ ደካማወችን በነፃ ሀኪም ጥበቡ
እውነታውን ቻናሉን በመቀላቀል የብዙሀኖችን ድምፅ እንስማ
ታምራዊ ፈውስ እና ሰወች ከነበራቸው ህምም በሽታ ሲፈወሱ ሲመሰክሩ እንባቸው ሲታበስ የምናይበትን ቻናል በመቀላቀል አይተን ተረድተን ለሌሎች ሸር እናድርግ ኢትዮጵያውይነት ደግነት
👇
https://vm.tiktok.com/ZMkQ1pTSL/
ለበለጠ መረጃ
ሀኪም ጥበቡ
0912718883
0917040506 በቴሌግራም በውስጥ መስመር የሚፈልጉትን ያስቀምጡ
👉አድራሻችን አዲስ አበባ አየር ጤና ካራቆሬ ወደመድኀኒአለም 200ሜትር ገባ ይበሉ
ቁጥር 2ባህርዳር ቀበሌ 11ዲያስፖራ በአሮየው
አስፓልት መስጊዱ ፊት ለፊት ያገኙናል ይምጡ
ይፈወስ
https://vm.tiktok.com/ZMkQJh8WX/
የኢትዮጵያ የባንክ ዘርፍ ከጥቂት ሳምንታት በኋላ ለውጭ ውድድር ሊከፈት መሆኑ ተሰማ!
ኢትዮጵያ በታሪኳ ለመጀመሪያ ጊዜ የባንክ ዘርፉን ለውጭ ውድድር ለመክፈት በዝግጅት ላይ ትገኛለች። ይህን ተከትሎ በአሁኑ ወቅት አዲስ ህግ በፓርላማ እየተገመገመ እና በሚቀጥለው ወር ይፀድቃል ተብሎ እንደሚጠበቅ ተገልጿል።
ይህ ወሳኝ ውሳኔ በሀገሪቱ ኢኮኖሚያዊ ገጽታ ላይ ከፍተኛ ለውጥን የሚያመለክት ሲሆን ይህም ውድድርን ለማሳደግ፣ የአገልግሎት አሰጣጥን ለማሻሻል እና የውጭ ኢንቨስትመንትን ለመሳብ ያለመ ነዉ ተብሏል ።
ርምጃው በኢትዮጵያ መንግስት እና በብሄራዊ ባንክ የተጀመሩት የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያዎች አካል ሲሆን እነዚህ ማሻሻያዎች የተነደፉት የፋይናንስ ሴክተሩን ለማዘመን እና ለሀገር ውስጥ እና ለአለም አቀፍ ንግዶች የበለጠ ምቹ ሁኔታን ለመፍጠር ጭምር ነዉ።
የውጭ ባንኮችን ወደ ኢትዮጵያ የፋይናንስ ምኅዳር ማስገባቱ ፉክክር እንደሚያመጣ የሚጠበቅ ሲሆን ይህም ለተጠቃሚዎች የተሻሻሉ አገልግሎቶችን እና ምርቶችን ሊያመጣ ይችላል ተብሎ ይጠበቃል።
Via Capital
@YeneTube @FikerAssefa
የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በነበረበት ይቀጥላል ተብሏል።
ኢትዮጵያ ተጨማሪ ጦር ወደ ሶማሊያ ልካለች ተባለ!
በፌደራሉ መንግስት እና በጁባላንድ ክልላዊ መንግስት መካከል በተፈጠረው አለመግባባት ቁጥራቸው በውል ያልተገለጸ የኢትዮጵያ ወታደሮች በሶማሊያ ደቡብ ምዕራብ በምትገኘው ዶሎው ከተማ ገብተዋል ሲል ካስሚዳ የተባለው የዜና ድረ-ገጽ ትናንት ዘግቧል።«የኢትዮጵያ መንግስት ትናንት በደርዘን የሚቆጠሩ ወታደራዊ ተሽከርካሪዎች እና በሺዎች የሚቆጠሩ ወታደሮችን ጭኖ በሶማሊያ ዶሎው ግዛት ጌዲኦ ወረዳ ገብቷል» ሲል ዘገባው አመልክቷል።
ዘገባው የሶማሊያ ጠቅላይ ሚኒስትር ሃምዛ አብዲ ባሬ በታችኛው ጁባ ክልል በደቡባዊ ራስ ካምቦኒ ከተማ ከሚያደርጉት ጉብኝት ቀደም ብሎ ነው።የኢትዮጵያ ወታደሮች ወታደራዊ ድጋፍ ላደረጉት የጁባላንድ ክልል ፕሬዝዳንት አህመድ ማዶቤ በመንግስት ሃይሎች ላይ “ወታደራዊ ድጋፍ ሊሰጡ እንደሚችሉ” ቪዛ ጠቁመዋል። ኢትዮጵያ በሶማሊያ የሚገኙ አማፂ ቡድኖችን ትደግፋለች የሚለው ወቀሳ እና የሁለቱ መንግስታት ውዝግብ ተባብሶ የቀጠለው፤ ራሷን እንደ ሀገር ከምትቆጥረው እና ሶማሊያ የግዛቴ አካል ከምትላት የሶማሌላንድ ሪፐብሊክ ጋር የመግባቢያ ሰነድ መፈራረማቸውን ተከትሎ ነው።
Via DW
@YeneTube @FikerAssefa
በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ የመንግስት ሰራተኞች በቅርቡ ከስራ ሊቀነሱ እንደሆነ ታውቋል
ከሰሞኑ የፀደቀው የመንግስት ሰራተኞች አዋጅ "ተቋማት ተልዕኳቸውን በብቃት እንዲፈፅሙ የሚያስችል ነው" ቢባልም ከአዋጁ ጋር ተያይዞ በርካታ የመንግስት ሰራተኞች ከስራ ሊቀነሱ እንደሚችሉ ስማችን አይጠቀስ ያሉ ሁለት የመንግስት ምንጮች ለመሠረት ሚድያ ተናግረዋል።
የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሰው ሃብት ልማት ሥራ ስምሪትና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ዶ/ር ነገሪ ሌንጮ በአዋጁ አላማና አስፈላጊነት ዙሪያ ሰፊ ማብራሪያ ሰጥተው በነበሩበት ወቅት ስለ ሰራተኛ ቅነሳው ያነሱት ነገር ባይኖርም በመንግስት አቅጣጫ ከተያዘባቸው ጉዳዮች አንዱ "ከሚያስፈልገው በላይ የመንግስት ሰራተኛ አለ" የሚለው ዋናው መሆኑን ምንጮቹ ጠቅሰዋል።
በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግስት ዋና ተጠሪ ሚንስትር አቶ ተስፋዬ በልጅጌ ሂደቱ የግለሰቦችን መብት ያለአግባብ እንዳይጎዳ ሚዛኑን አስጠብቆ በመሄድ ረገድ ተገቢው ጥንቃቄ ይደረጋል ቢሉም በርካቶች ከስራቸው እንደሚቀነሱ እንደማይቀር ታውቋል።
የረቂቅ አዋጁን ይዘት በአግባቡ ባለመረዳት በአንዳንድ የሚዲያ ተቋማት የተዛቡ መረጃዎች እየተላለፉ እንደሆነ የሚናገሩት ዶ/ር ነገሪ በበኩላቸው ግልፀኝነት በሚያስፈልጋቸው ጉዳዮች ላይ በመወያየት ረቂቅ አዋጁን የበለጠ ለማዳበር እና ህዝቡ ትክክለኛ መረጃ እንዲያገኝ ለማድረግ ይደረጋል ብለዋል።
አዋጁ እንደ ፍርድ ቤት፣ አቃቤ ህግ፣ ፖሊስ፣ መከላከያ፣ እና ደህንነትን የመሳሰሉ ተቋማት ውስጥ የብሄር ስብጥር ለማድረግም ያለመ መሆኑን የጠቁሙት ምንጮች አዋጁ "የብሔር ብሔረሰቦች ብዙሃነት እና አካታችነት ስርዓትን ይገነባል" በሚል በመንግስት እንደታሰበ አስረድተዋል።
የዚህን የመንግስት ሰራተኞች ቅነሳ የሚጠቁም ነገር ግን ብዙ ሰው ልብ ያላለው አንድ መረጃ በአንድ የመንግስት ሚድያም ተለቆ ነበር።
"ሲቪል ሰርቪሱ ሀገሪቷ ከምትሸከመውና አገልግሎቱ ከሚፈልገው በላይ የበዛ መሆኑ ተጠቆመ" የሚል መረጃ ባለፈው ሳምንት በኢትዮጵያ ፕረስ ድርጅት ተሰራጭቶ የነበረ ሲሆን በአሁኑ ወቅት ያለው የሲቪል ሰርቪሱ ቁጥር ሀገሪቷ ከምትሸከመውና አገልግሎቱ ከሚፈልገው በላይ የበዛ መሆኑን ዶ/ር ነገሪ መናገራቸውን ዘግቦ ነበር።
ዶ/ር ነገሪ በዚህ ንግግራቸው እንደጠቀሱት "በየመንግሥት መሥሪያ ቤቱ ያለው የሠራተኛ ቁጥር በጣም በርካታ ነው። ሀገሪቷ ከምትሸከመውና አገልግሎቱ ከሚፈልገው በላይ የበዛ ነው። ከአደረጃጀት አንጻር ሲታይም በአንድ መሥሪያ ቤት ውስጥ መዋቅሩ የሚሸከመው ብዙ የሰው ኃይልን ነው፤ በተሸከመ ቁጥር ደግሞ የሚያገኘው ጥቅም አናሳ ነው" ብለው ነበር።
ሀላፊው አክለውም "የመንግሥት ሠራተኞች የብዛታቸውን ያህል የሚሠሩት አገልግሎት የሚያረካ አይደለም፣ የተወሰኑ ይሠራሉ፤ ሌሎቹ ግን የተወሰኑ ሠራተኞች በሠሩት ትከሻ ላይ ተንጠላጥለው ይኖራሉ" በማለት የሰራተኛ ቅነሳ መኖሩን በተዘዋዋሪ መንገድ ጠቁመው ነበር።
የዳኝነት ክፍያን እስከ 500 ፐርሰንት የሚጨምረው ህግ ዛሬ ፀደቀ
የፌዴራል ፍርድ ቤቶች የዳኝነት ክፍያን ለመወሰን የወጣው ረቂቅ ደንብ በዛሬው እለት በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የፀደቀ ሲሆን መሠረት ሚድያ የተመለከተው ይህ የክፍያ ወሰን እስከ 500 ፐርሰንት ጭማሪ ተገልጋዮች ላይ ይጥላል።
ደንቡን ማሻሻል ያስፈለገው የፌዴራል ፍርድ ቤቶች ከዚህ ቀደም የሚጠቀሙበት የዳኝነት ገንዘብ አከፋፈል ለ72 ዓመታት ማሻሻያ ሳይደረግበት የቆየ መሆኑ የተገለፀ ቢሆንም እስከ 500 ፐርሰንት ጭማሪ ማድረጉ በተለይ አሁን ላይ ካለው የኑሮ ውድነት ጋር ተያይዞ ለብዙዎች አስገራሚ ሆኗል።
መሠረት ሚድያ የተመለከተው እና በቅርቡ በነጋሪት ጋዜጣ ታትሞ እንደሚወጣ የሚጠበቀው ዛሬ የፀደቀው የዳኝነት ክፍያ ከዚህ በፊት ለሁለት ሚልዮን ብር የክስ ገንዘብ መጠን ይከፈለው የነበረው 23,000 ብር ወደ 82,000 ብር ጨምሯል።
ይህ የተጋነነ ክፍያ ሰዎች ፍትህ ለማግኘት ወደ ፍትህ ተቋማት እንዳይሄዱ እንቅፋት ሊሆን እንደሚችል ከወዲሁ እየተጠቆመ ይገኛል።
መሠረት ሚዲያ
@Yenetube @Fikerassefa
የከተማ መሬቶች በሶስት ዓመት ጊዜ ውስጥ ሙሉ በሙሉ በሊዝ የመሬት ስርዓት ውስጥ መካተት እንዳለባቸው ተጠቆመ
በኢትዮጵያ ከተሞች ያሉ መሬቶች በሶስት ዓመት ጊዜ ውስጥ ሙሉ በሙሉ በሊዝ የመሬት ስርዓት ውስጥ መካተት እንዳለባቸው ተሻሻሎ በቀረበው የከተማ መሬትን በሊዝ ለመያዝ በቀረበው ረቂቅ አዋጅ ላይ ተጠቆመ።
በዛሬው ዕለት በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የከተማ፣ መሰረት ልማት እና ትራንስፖርት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የከተማ መሬት ይዞታ እና መሬት ነክ ንብረት ለመመዝገብ እና የከተማ መሬትን በሊዝ ለመያዝ ተሻሽሎ የቀረቡ ረቂቅ አዋጆች ላይ ከባለድርሻ አካላት ጋር እየተወያየ ይገኛል።
በተሻሻለው አዋጅ ውስጥም የከተማ መሬት ሊዝን በተመለከተ ከኅዳር 18/2004 በኋላ ያለፈቃድ የተያዙም ሆነ ፈቃድ ባላገኙ መሬት ላይ ያሉ ግንባታዎችን ጭምር በማፍረስ መንግስት የመሬት ይዞታዎቹን እንደሚረከብ ተመላክቷል።
እንዲሁም በኢትዮጵያ ውስጥ ያሉ ከተሞች በሶስት ዓመት ጊዜ ውስጥ ሙሉ በሙሉ በሊዝ የመሬት ስርዓት ውስጥ መካተት እንዳለባቸው በተሻሻለው በረቂቅ አዋጅ ላይ መካተቱን ለሚመለከታቸው አካላት ተብራርቷል።
ቻይና ኢኮኖሚዋን ለማነቃቃት መግቢያ ቪዛ የማያስፈልጋቸው ሀገሮችን ቁጥር ልታሳድግ ነው!
ቻይና የቱሪዝም እና የንግድ ተጓዦችን ቁጥር በማሳደግ የተቀዛቀዘውን ኢኮኖሚዋን ለማነቃቃት ለዘጠኝ ተጨማሪ ሀገራት ዜጎች ካለቪዛ እንዲገቡ ልትፈቅድ መሆኗን አስታወቀች፡፡የቻይና ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ሊን ጂያን ዛሬ ዓርብ እንዳስታወቁት እአአ ከህዳር 30 ጀምሮ ከቡልጋሪያ፣ ሮማኒያ፣ ማልታ፣ ክሮኤሺያ፣ ሞንቴኔግሮ፣ ሰሜን መቄዶኒያ፣ ኢስቶኒያ፣ ላቲቪያ እና ጃፓን ተጓዦች ለሠላሳ ቀናት ቆይታ ያለ ቪዛ ሊገቡ ይችላሉ።
ይህ ካለፈው ዓመት ጀምሮ ያለቪዛ መግባት የተፈቀደላቸውን ሀገራት ቁጥር ወደ 38 ያሳድገዋል።ከዚህ ቀደም ከቪዛ ነጻ ፈቃድ የነበራቸው ሦስት ሀገራት ብቻ ሲሆኑ የእነሱም ፈቃድ በኮቪድ-19 ወረርሽኝ ወቅት ተሰርዞ እንደነበረ ይታወሳል፡፡የጃፓን ከቪዛ ነጻ ሀገራቱ ውስጥ መጨመር፣ ቻይና በታይዋን ጉዳይ ከቶኪዮ በተደረጉ ጠንከር ያሉ ንግግሮች የተነሳ ሻክሮ የነበረውን ግንኙነት ለማሻሻል እየፈለገች መሆኗን ሊጠቁም እንደሚችል ተነግሯል፡፡
ጃፓን ከወረርሽኙ በፊት ከቪዛ ነፃ ከሚገቡት ሶስት ሀገራት አንዷ ነበረች፡፡ የጃፓን የካቢኔ ፀሃፊ ዮሺማሳ ሃያሺ እንደገና እንዲጀመር መንግሥታቸው በተደጋጋሚ ሲወተውት እንደነበረ ገልጸዋል፡፡ቻይና ከቪዛ ነፃ የመግባት ሂደትን በየደረጃው በማስፋፋት የአውሮፓ ሀገራትን ጨምራ በቅርቡ የተማሪዎችና እና የምሁራን ጉብኝቶችን በማሻሻል የህዝብ ለህዝብ ልውውጥ ላይ ትኩረት አድርጋለች።
ታይላንድ እና ሌሎች ሀገራት ቱሪዝምን ለማበረታታት ለቻይና ተጓዦች ከቪዛ ነጻ ፖሊሲዎችን ተግባራዊ አድርገዋል፡፡በዚህ ዓመት ከሀምሌ እስከ መስከረም በነበሩት ሦስት ወራት 8.2 ሚሊዮን የውጭ ዜጎች ቻይና የገቡ ሲሆን 4፡9 ሚሊዮን የሚሆኑት ከቪዛ ነጻ ተጠቃሚዎች መሆናቸውን የአሶሴይትድ ፕሬስ ዘገባው አመልክቷል፡፡
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።
@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna
#ኢትዮጵያ
Last updated 2 months, 3 weeks ago
Last updated 2 months, 2 weeks ago
ይህ ስለ Manchester United መረጃዎችን የሚያገኙበት የ Telegram ቻናል ነው 🇪🇹
--------------------------------------------------------------
☞︎| ስለ ማንቸስተር ዩናይትድ ትኩስ መረጃዎች
☞| ቀጥታ ስርጭቶች ከየስታድየሞቹ
☞| የዝውውር ዜናዎች
☞| ስለ ማንችስተር ዩናይትድ ታሪኮች
📩 ለማስታወቂያ ስራ DM :- @Marcoabdu
Last updated 1 month, 1 week ago