Tofik Bahiru

Description
We recommend to visit

ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ

Last updated 2 months, 3 weeks ago

Last updated 2 months, 2 weeks ago

ይህ ስለ Manchester United መረጃዎችን የሚያገኙበት የ Telegram ቻናል ነው 🇪🇹
--------------------------------------------------------------
☞︎| ስለ ማንቸስተር ዩናይትድ ትኩስ መረጃዎች
☞| ቀጥታ ስርጭቶች ከየስታድየሞቹ
☞| የዝውውር ዜናዎች
☞| ስለ ማንችስተር ዩናይትድ ታሪኮች

📩 ለማስታወቂያ ስራ DM :- @Marcoabdu

Last updated 1 month, 1 week ago

1 month ago

አላህ ካለ ከመጪው ማክሰኞ ጀምሮ እንጀምራለን። ደርሱ በሳምንት ሁለት ቀን [ማክሰኞና ሐሙስ] በድምፅ ቅጂ የሚለቀቅ ሲሆን ጥያቄዎችን የምናስተናግድበት መሰናዶዎችም ይኖሩናል።
ኪታብ አሰናዳችሁ?

1 month ago

ኢማም ሙስሊም [ረሒመሁላህ] ሶሒሕ በተሰኘው መጽሐፋቸው ላይ እንደዘገቡት የአላህ ነቢይ [ﷺ] እንዲህ ብለዋል: ‐
«አንዳንድ ሰዎች አላህ እስከሚያዘገያቸው ድረስ ሰርክ ከመዘግየት አይወገዱም።»
:
እነርሱ ከመልካም ሥራዎች ሲዘገዩ፣ መዋለልና ማመንታትን ጠባይ አድርገው ይዘው ሲዘናጉ አላህም ከእዝነቱ ያዘገያቸዋል።
ከትሩፋቱ ያዘገያቸዋል። ከንፁህ ምህረቱ፣ ከእገዛው፣ ከውዴታው፣ ከጀነቱ ያዘገያቸዋል። ጀነት ቢገቡም ከፍ ካለው ደረጃ ያዘገያቸዋል። ዝቅ ያደርጋቸዋል።
አመቱን ትተነው እንኳን ሸዕባን ላይ የዘገዩ መዘግየታቸውን እንዴት ያዩታል?!…
ሸዕባን ላይ መዘግየት ረመዳን ላይ መዘግየትም ያመጣል?!…
ረመዳን ላይ መዘግየት የሚያመጣው ክስረት ደግሞ የሚነገር አይደለም!
#በሊግና #ረመዳን

1 month ago

አዝካር አን‐ነወዊይ በፒዲኤፍ ይኸውላችሁ። ነገርግን በቤት ውስጥ አንድ ኮፒ መያዝና ማስታወሻ እየያዙ መከታተል መልካም ነው። አላህ ያግራልን!

4 months ago

ሰይዲና አቡሁረይራ [ረዲየላሁ ዐንሁ] የአላህ መልክተኛ [ﷺ] እንዲህ ማለታቸውን ዘግበዋል: ‐
«አላህ ጀነትን ከፈጠረ በኋላ ጂብሪልን [ዐለይሂ ሰላም] «ሂድና ተመልከታት!» አለው።

ጂብሪል ተመለከታትና እንዲህ አለ: ‐ «በልቅናህ እምላለሁ! ስለርሷ የሰማ ማንም ሰው ወደርሷ መግባቱ አይቀርም።»

ከዚያም አላህ ነፍስ በምትጠላው ነገር ከበባትና «ሂድና ተመልከታት» አለው። ሂዶ ተመለከታትና «በልቅናህ እምላለሁ! ማንም እርሷ ውስጥ አይደባም ብዬ ሰጋሁ!» አለ።

እሳትን የፈጠረ ጊዜም ጂብሪልን «ሂድና እያት» አለው። ሄዶ ተመለከታትና «በልቅናህ እምላለሁ! ስለርሷ የሰማ ማንም ሰው እርሷ ውስጥ አይገባም።» አለ።

ከዚያም አላህ ነፍስ በምትወዳቸው [እኩይ] ስሜቶች ከበባትና «ሂድና ተመልከታት» አለው።

ጂብሪልም ተመለከታትና እንዲህ አለ: ‐ «በልቅናህ እምላለሁ! ማንም ሰው እርሷ ውስጥ ከመግባት አይተርፍም ብዬ እሰጋለሁ።» አለ።»
ኢብኑ አቢዱንያ ዘግበውታል።

4 months, 1 week ago

ሙቀዲመቱ ባፈድል
? ክፍል ሠላሳ አንድ:‐ የዒድ ሶላት (ሶላቱል‐ዒደይን)
? ጥቅምት 24/ 2017 ዓ. ል.

4 months, 1 week ago

በርካቶቻችን በቀልብ ድርቀት ፈተና ውስጥ ወድቀን በጭካኔ ህመም እየተሰቃየን ይሆናል።
አንዳንድ ሰዎች ግን ፈተናቸው ተቃራኒ ነው። በቀልብ ልስላሴና በቀልብ ቅጥነት ስር ወድቀው የሚሰቃዩ አሉ። የነርሱ ስቃይ ከባድ ነው!
:
መከረኛ በሆነው በዚህ ዓለም ውስጥ ቀልበ ቀጭን መሆን ከባድ ነው። የሰብዓዊው ፍጡር እንግልት በጠናበት በዚህ ዓለም እዚህም እዚያም ለሚወድቀው ነፍስ ማዘን መራር ነው። ፀሀይ ወጥታ እስከምትጠልቅ ስንት ዓይነት የሰዎችን ስቃይና ሰቆቃ እናያለን?
ቀልበ ቀጭኖች የሌሎችን ስቃይ እንደራሳቸው ስቃይ ይመለከታሉ። በሰው ሃሳብ ይብሰለሰላሉ። በጭንቀታቸው ይብሰከሰካሉ። በሰዎች ህመም ይታመማሉ። ከምላሳቸውና ከኪሳቸው እምባቸው ይቀድማል።
ሩኅሩኅ ናቸው። ለሰዎች መልካምን ይመኛሉ። በሰው ላይ በሚደርስ ክፉ ነገር ይጨነቃሉ። ሰዎች በእጦት ከተረበሹ እነርሱም ያላቸውን ሰጥተው በእጦት ከሚሰቃዩት ጋር ራሳቸውን ይቦድናሉ። የሚሰጡት ካጡም መለገስ ባለመቻላቸው በመቆጨት በለቅሶ ይመለሳሉ።
:
እነዚህ ሰዎች ጥቂቶች ናቸው። በህይወቴ ከሦስት የማይበልጡ ሰዎች ከነዚህ እንደሚመደቡ እመሰክርላቸዋለሁ። ምቾትን አያውቋትም። በእርግጥ በዓለሙ ስቃይ ይሰቃያሉ። ነገርግን ስቃያቸው ቢበረታም የጀነት ናቸው። እንደውም ያለ ሂሳብ ጀነት ከሚገቡት የበሯ ከፋቾች ናቸው! በክብር የሚገቡበት የግል በርም ሳይኖራቸው አይቀርም!
የአላህ መልክተኛ [ﷺ] እንዲህ ብለዋል: ‐ «ልባቸው እንደ ወፍ ልብ የሆኑ ሰዎች ጀነት ይገባሉ!»
በዚህ ሐዲስ ላይ «የወፍ ልብ ያላቸው» የተባሉት ሩኅሩኅ ሰዎች ናቸው ተብሏል በአንድ ተፍሲር።
አላህ ርኅራኄን ይስጠን!
https://t.me/fiqshafiyamh

6 months, 3 weeks ago

ሙስሊሞች የአላህ ነቢይን [] ለመጥራት ሲፈልጉ ሊከተሉት የሚገባን ስነስርዐት በማስመልከት በቀጥታ ከአላህ የተሰጡ ደንቦች አሉ። እነርሱም የሚከተሉት ናቸው: ‐

? ﴿يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا لَا تَرْفَعُوا أَصْوَاتَكُمْ فَوْقَ صَوْتِ النَّبِيِّ وَلا تَجْهَرُوا لَهُ بِالْقَوْلِ كَجَهْرِ بَعْضِكُمْ لِبَعْضٍ أَنْ تَحْبَطَ أَعْمَالُكُمْ وَأَنْتُمْ لَا تَشْعُرُونَ﴾.

«እናንተ ያመናችሁ ሆይ! ድምጾቻችሁን ከነቢዩ ድምጽ በላይ ከፍ አታድርጉ፡፡ ከፊላችሁም ለከፊሉ እንደሚጮህ በንግግር ለርሱ አትጩሁ፡፡ እናንተ የማታውቁ ስትኾኑ ሥራዎቻችሁ እንዳይበላሹ (ተከልከሉ)፡፡»

? ﴿إِنَّ الَّذِينَ يُنَادُونَكَ مِنْ وَرَاءِ الْحُجُرَاتِ أَكْثَرُهُمْ لَا يَعْقِلُونَ وَلَوْ أَنَّهُمْ صَبَرُوا حَتَّى تَخْرُجَ إِلَيْهِمْ لَكَانَ خَيْرًا لَهُمْ﴾.

«እነዚያ ከክፍሎቹ ውጭ ኾነው የሚጠሩህ አብዛኞቻቸው አያውቁም፡፡ ወደእነርሱም እስክትወጣ ድረስ እነርሱ በታገሱ ኖሮ ለእነርሱ በላጭ በኾነ ነበር፡፡ አላህም እጅግ መሓሪ አዛኝ ነው፡፡»

? ﴿يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا لَا تَقُولُوا رَاعِنَا وَقُولُوا انْظُرْنَا وَاسْمَعُوا﴾.

«እናንተ ያመናችሁ ሆይ! (ለነቢዩ) ራዒና አትበሉ፡፡ ተመለከትን በሉም፡፡ ስሙም፤ ለከሓዲዎችም አሳማሚ ቅጣት አላቸው፡፡»

? ﴿یَـٰۤأَیُّهَا ٱلَّذِینَ ءَامَنُوۤا۟ إِذَا نَـٰجَیۡتُمُ ٱلرَّسُولَ فَقَدِّمُوا۟ بَیۡنَ یَدَیۡ نَجۡوَىٰكُمۡ صَدَقَةࣰۚ ذَ ٰ⁠لِكَ خَیۡرࣱ لَّكُمۡ وَأَطۡهَرُۚ فَإِن لَّمۡ تَجِدُوا۟ فَإِنَّ ٱللَّهَ غَفُورࣱ رَّحِیمٌ﴾.

«እናንተ ያመናችሁ ሆይ! መልክተኛውን በተወያያችሁ ጊዜ ከመወያየታችሁ በፊት ምጽዋትን አስቀድሙ፡፡ ይህ ለእናንተ መልካም ነው፡፡ አጥሪም ነው፡፡ ባታገኙም አላህ መሓሪ አዛኝ ነው፡፡»

? ﴿لَّا تَجۡعَلُوا۟ دُعَاۤءَ ٱلرَّسُولِ بَیۡنَكُمۡ كَدُعَاۤءِ بَعۡضِكُم بَعۡضࣰاۚ﴾.

«በመካከላችሁ የመልክተኛውን ጥሪ ከፊላችሁ ከፊሉን እንደ መጥራት አታድርጉት፡፡»

#ሶሉ #ዐለነቢ

6 months, 3 weeks ago

ተወዳጃችን [] እንዲህ ይላሉ: –
«ሰኞና ሐሙስ ቀን የጀነት ደጃፎች ይከፈታሉ። እናም አላህ በእርሱ ላይ ምንም የማያጋራ ሰውን በሙሉ ምህረት ይሰጣል፤ በእርሱና በወንድሙ መካከል ቂም የቋጠረ ሰው ሲቀር። አላህም: ‐ 'እነዚህን እስከሚታረቁ ድረስ አቆይዋቸው' ይላል።»
ሙስሊም ዘግበውታል።
:
አስፈሪ ነው። ነገርግን ዐፍዉ በመባባል አደጋውን መሻገር ይቻላል!

6 months, 3 weeks ago

ሱፍያን ኢብኑ ዑየይና [ረዐ] እንዲህ ብለዋል: —
«አምስቱን ሶላቶች የሰገደ ሰው በእርግጥ አላህን አመሰገነ። ከሶላት በኋላ ለወላጆቹ ዱዓ ያደረገ ሰው በእርግጥ አመሰገናቸው።»
ተፍሲር አል‐ቁርጡቢ
t.me/fiqshafiyamh

6 months, 3 weeks ago

ጠቢቡ ሰይዲና ሉቅማን ልጃቸውን ሲመክሩ እንዲህ አሉ: ‐

«ልጄ ሆይ!…
ክፉ በክፉ ይጠፋል የሚልህን ሰው አትስማ።
የሚለው እውነት ከሆነ እስኪ ሁለት እሳቶችን ያንድድና አንዱን በሌላው ያጥፋ!
እሳትን ውሃ እንደሚያጠፋው ክፋትንም መልካምነት ብቻ ያጠፋዋል!»
t.me/fiqshafiyamh

We recommend to visit

ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ

Last updated 2 months, 3 weeks ago

Last updated 2 months, 2 weeks ago

ይህ ስለ Manchester United መረጃዎችን የሚያገኙበት የ Telegram ቻናል ነው 🇪🇹
--------------------------------------------------------------
☞︎| ስለ ማንቸስተር ዩናይትድ ትኩስ መረጃዎች
☞| ቀጥታ ስርጭቶች ከየስታድየሞቹ
☞| የዝውውር ዜናዎች
☞| ስለ ማንችስተር ዩናይትድ ታሪኮች

📩 ለማስታወቂያ ስራ DM :- @Marcoabdu

Last updated 1 month, 1 week ago