Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

Description
ትክክለኛዉ የሁሌ አዲስ ሚዲያ ገፆች

Facebook : bit.ly/42rUuKj
WhatsApp : bit.ly/Huleadis_whatsapp
YouTube : bit.ly/3p7kj3N
Twitter : bit.ly/3NVMRrB
Telegram: bit.ly/Huleadis_tele

ለጥቆማ ና አስተያየት እንዲሁም ለማስታወቂያ ስራ ተከታዮን አድራሻ ይጠቀሙ
bit.ly/3VMy7x7
Advertising
We recommend to visit

ለማንኛውም አስተያየት እና ጥቆማ 👉 @Esat_tv_comment_bot

🇪🇹ኢሳት የኢትዮጵያ አይን እና ጆሮ🇪🇹

Last updated 1 week, 1 day ago

በዚህ ቻናል ሀገራዊና አለምአቀፋዊ መረጃዎችን በፍጥነት ያገኛሉ❗
የውስጥ መስመር👉http://t.me/ayulaw

Last updated 2 months, 2 weeks ago

Last updated 1 month, 1 week ago

2 months ago

ዜና: “የፋኖ ወንድሞቻችን ወደ ጫካ የሄዱት የአማራ ሕዝብን ፍላጎት መነሻ አድርገው ነው” - #የአማራ ክልል የሰላም ካውንስል ሰብሳቢ

የአማራ ክልል የሰላም ካውንስል በክልሉ የሚንቀሳቀሱ #የፋኖ ታጣቂዎች ወደ አንድ አደረጃጀት በመሰባሰብ ለንግግር እንዲዘጋጁ ጥረት እየተደረገ መሆኑን አስታወቀ።

“የፋኖ ወንድሞቻችን ወደ ጫካ የሄዱት የአማራ ሕዝብን ፍላጎት መነሻ አድርገው ነው” ሲሉ የገለጹት የካውንስሉ ሰብሳቢ ያየህይራድ በለጠ አክለውም የአማራ ክልል ህዝብ በጫካ ያሉ ልጆቹ ወደ ንግግር እንዲመጡ ሊመክር እና ሊያበረታታ እንደሚገባም አሳስበዋል።

የሰላም ካውንስሉ የሰላም ጥሪ ከማቅረብ በተጨማሪ ሁለቱም ወገኖች ወደ ንግግር እና ድርድር መምጣት የሚችሉበትን አስቻይ ሁኔታዎችን እያመቻቹ መሆኑን የካውንስሉ ሰብሳቢ ያየህይራድ በለጠ ከኢቲቪ ጋር በነበራቸው ቆይታ አብራርተዋል።

የአማራ ክልል መንግስት በካውንስሉ የቀረበውን የሰላም ጥሪ ተቀብሎ ለድርድር ዝግጁ መሆኑን የገለጹት ሰብሳቢው፤ ህብረተሰቡ ለሰላም ንግግሩ ስኬት ድጋፉን አጠናክሮ እንዲቀጥል ጥሪ አቅርበዋል።

ከኢቲቪ ጋር ቆይታ ያደረጉት በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የፖለቲካል ሳይንስ መምህሩ ዮናስ አሽኔ (ዶ/ር) በበኩላቸውም ከድርድሩ በፊት ሁለቱም ወገኖች የተኩስ አቁም ስምምነትን ማድረግና ከጥላቻ ንግግር መታቀብ ይጠበቅባቸዋል ሲሉ አስረድተዋል።

መንግሥትም ሆነ ታጣቂዎች በሰላማዊ ንግግር ችግሮችን ለመፈታት በቁርጠኝነት ሊሰሩ እንደሚገባም ገልጸዋል።

የአማራ ክልል ሰላምን ለመመለስ እየተደረጉ ካሉ ጥረቶች መካከል ሰኔ 17 እና 18 ቀን 2016 ዓ.ም የተደረገው የሰላም ኮንፈረንስ አንዱ ሲሆን በኮንፈረንሱ ማጠቃለያ ላይ በመንግሥት እና ታጣቂዎች መካከል የሚደረገውን ድርድር እንዲያመቻች 15 አባላት ያሉት ካውንስል ተቋቁሞ ወደ ስራ መግባቱ ይታወቃል።

2 months ago

የ6ኛው ግራንድ አፍሪካን ረን በመጪዉ ጥቅምት በዋሽንግተን ዲሲ ሊካሄድ ነው

የዝግጅቱ ዕድለኛ ተሳታፊ የ2024 ቶዮታ ኮሮላ ያገኛል::

ደራርቱ ቱሉና 2 የዓለም ሪከርድ ባለቤት አትሌቶች በዚህ ዝግጅት ላይ በክብር እንግድነት ይሳተፋሉ።

ዋሽንግተን ዲሲ (ሐምሌ 5/2016) ፤ 6ኛው ግራንድ አፍሪካን ረን በፈረንጆቹ አቆጣጠር በመጪዉ ኦክቶበር 12/ 2024 ወይም ጥቅምት 2/ 2017 ዓ.ም. በዋሽንግተን ዲሲ ሊካሄድ መሆኑን ዛሬ በተሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ተገለፀ።

'አብሮነት መሻል ነው' በሚል መሪ ቃል የሚካሄደው ይህ ዝግጅት፤ ኢትዮጵያዊያንን ብሎም አፍሪካዊያንን ማሰባሰብ፤ የመጀመሪያው ትውልድ ልጆችን ከባህላቸው ጋር የበለጠ ማቀራረብ፣ እና ለተለያዩ በጎ ስራዎች ገቢ ማሰባሰብን ዓላማው አድርጎ የሚከናወን ነው። በዚሀ ዝግጅት፥ በሺህ የሚቆጠሩ የዲያስፖራው ማሀበረሰብ አባላት የሚሳተፉበት መሆኑ ተገልፆ፣ በዝግጅቱ ለመሳተፍ ምዝገባው በአዘጋጆቹ ዌብሳይት www.africanrun.com ላይ መጀመሩ ታውቋል።

የዝግጅቱ ቀዳሚ ኣጋር የሆነው አሌክሳንድሪያ ቶዮታ ለተሳታፊዎች የመኪና ሽልማት ማዘጋጀቱም ተገልፆል። "ሁሉም አሸናፊ ነው" በሚል መርሀ በተዘጋጀው በዚህ ሽልማት የዝግጅቱ ተሳታፊዎች አንደኛም ሆነ መጨረሻ ሆነው ርቀቱን ቢያጠናቅቁም ሁሉም ተሳታፊ መኪናውን የማሸነፍ እኩል ዕድል እንደሚኖረው ታውቋል። በዝግጅቱ ቀን የሩጫው ማጠቃለያ ላይ የሎተሪ ዕጣ የማውጣት ስነ ስርዓት ተከናውኖ የመኪናው አሸናፊ በይፋ ለታዳሚዎች የሚገለጽ መሆኑ ተመልክቷል።

በዘንድሮው ዝግጅት በክብር እንግድነት ተሳታፊዎችን ለማበረታታት ረዳት ኮሚሽነር ደራርቱ ቱሉ፣ በሴቶች የማራቶን የዓለም ሪከርድ ባለቤት አትሌት ትግስት አሰፋ፣ እና በሴቶች የ5ሺ የዓለም ሪከርድ ባለቤት አትሌት ጉዳፍ ፀጋዬ በዝግጅቱ ላይ እንደሚገኙ ገልፀዋል። አትሌት ደራርቱ ቱሉ ከመጀመሪያው ጀመሮ ዝግጅቱን በመደገፍ እና በማበረታታት ያገዘች መሆኗን ጠቁማ፣ "አገራችንን በዓለም መድረክ በመልካም ገፅታ እንድንታዋወቅ ያደረገው የአትሌቲክስ ስፖርት በዉጭ ለሚገኙ ወገኖቻችን የመሰባሰቢያ መድረክ ሆኖ ማገልገሉ ዝግጅቱን ልዩ ያደረገዋል" ብላለች።

አያይዛም፣ ዝግጅቱ ማሀበረሰባችን የተለየ ቦታ የሚሰጠውን የአትሌቲክስ ስፖርት በመጠቀም አብሮነትን ማጎልበት ያስችላል ስትል ገልፃለች።

የማራቶን ሪከርድ ባለቤቷ አትሌት ትግስት አሰፋ በበኩሏ ዝግጅቱ ላይ ተገኝታ ተሳታፊዎችን እንደምታበረታታ 169፣ ወገኖቻችን ተሰባስበው በአንድነት የሚያሳልፉባቸው መድረኮች ሁሉ የአብሮነታችን መገለጫዎች ናቸው ስትል ገልፃለች፡፡ የ5ሺ ሪከርድ ባለቤቷ አትሌት ጉዳፍ ፀጋዬ እንዲሁ ወገኖቿን በቦታው በመገኘት እንደምታበረታታ ገልፃ፣ አገራቸውን ወከለው በኦሎምፒክ መድረክ ለሚሳተፉ አትሌቶች ሁሉ መልካም ምኞቷን አስተላልፋለች፡፡

2 months ago

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አጠቃላይ ተቀማጭ ገንዘብ 1.17 ትሪሊዮን መሻገሩን አስታወቀ ‼️‼️

መንግስታዊ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በበጀት ዓመቱ 135.4 ቢሊዮን አጠቃላይ ገቢ ማግኘቱን በመግለፅ የተቀማጭ ገንዘብ መጠኑ  ከ ብር 1.17 ትሪሊዮን መሻገሩን አስታዉቋል።

ባንኩ ከታክስ በፊት 25.6 ቢሊዮን ትርፍ ማስመዝገቡን እና ይህም በባንኩ ታሪክ ከፍተኛው ሆኖ መቀመጡን ገልጿል።

በበጀት ዓመቱ 218 ቢሊዮን ብር  በላይ የብድር አገልግሎት ማቅረብን፤ 91% ወይም ብር 198 ቢሊዮን የሚበልጠው ለግሉ ሴክተር የተለቀቀ ብድር  መሆኑን በማሳወቅ የብድሮች ክምችት በዓመቱ ማጠቃለያ 2.6% ደርሷል ብሏል።

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በ2023/24 በጀት ዓመት የሥራ አፈጻጸም በተመለከተ ባቀረበው ሪፖርት
በበጀት ዓመቱ በቁጥር ከ1.56 ቢሊዮን የሚበልጥ ግብይት፤ ወይም በገንዘብ ከብር 31.6 ትሪሊዮን በላይ የገንዘብ ዝውውር መፈፀሙን በመግለፅ ከ1.19 ቢሊዮን ወይም 72% የሚሆነው ግብይት በዲጂታል የክፍያ አማራጮች የተከናወነ ነዉ ማለቱ ካፒታል ከተቋሙ ያገኘዉ መረጃ ያመለክታል ።

2 months, 1 week ago
Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ …
2 months, 1 week ago
ቶምቦላ ሎተሪ 2016 ዓ/ም ዕጣ ዛሬ …

ቶምቦላ ሎተሪ 2016 ዓ/ም ዕጣ ዛሬ ሰኔ 28 ቀን 2016 ዓ.ም በብሔራዊ ሎተሪ አስተዳደር በዕድል አዳራሽ የወጣ ሲሆን የወጡት የዕጣ ቁጥሮች ከላይ ተያይዘዋል

2 months, 1 week ago

በኢትዮጵያ በህገ ወጥ መንገድ የሚኖሩ ከ10 ሺ በላይ ስደተኞች መመዝገባቸውን ጠቅላይ ሚኒስተር ዐቢይ ገለጹ!

በኢትዮጵያ በህገ ወጥ መንገድ የሚኖሩ ከ10 ሺ በላይ ስደተኞች መመዝገባቸውን ጠቅላይ ሚኒስተር ዐቢይ ገለጹ።የኢምግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት የውጭ ስደተኞች እንዲመወገቡ ባወጣው ማስታወቂያ መሰረት፣ በኢትዮጵያ በህወጥ መንገድ የሚኖሩ 10467 ስደተኞችን መመዝገቡን ጠቅላይ ሚኒስተር ዐበይ በትዊተር ገጻቸው ገልጸዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ቅሬታ የሚነሳበት ይህ የአገልግሎት መስሪያ ቤት በርካታ ማሻሻያዎችን አድርጓል ብለዋል።መስሪያ ቤቱ ከፓስፖርት አሰጣጥ አገልግሎት ጋር በተገናኘ በርካታ ቅሬታ የሚቀርብቀት ሲሆን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ጥር 2015 ዓ.ም ሶስት ከፍተኛ ኃላፊዎች ከኃላፊነት መነሳታቸው ይታወሳል።ጠቅላይ ሚንስትር ከኃላፊነት ያነሱት የአገልግሎቱን በዋና ዳይሬክተርነት ሲመሩ የነበሩትን አቶ ብሩህተስፋ ሙልጌታን፣ በምክትል ዳይሬክተርነት ሲያገለግሉ የነበሩትን ፍራኦል ጣፋ እና ታምሩ ግንበቶንን ነው።

ይህን ተከትሎ ወይዘሮ ሰላማዊት ዳዊት ከሐምሌ 12 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ ተቋሙን በዋና ዳይሬክተርነት እየመሩ ነው።በቅርቡ የፌደራል ዋና ኦዲተር በህዝብ ተወካዮች ባቀረበው ሪፖርት የኢምግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት መስሪያ ቤት ያለአግባብ በግለሰቦች ስም በተከፈተ አካውንት 17 ሚሊዮን ብር መሰብሰቡን መግለጹ ይታወሳል።

"የተከማቹ ቅሬታዎች መቶ በመቶ ተፈተዋል" ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐበይ አገልግሎቱ በቀን ይሰጥ የነበረውን የፓስፖርት መጠን ከ900 ወደ 1700 ከፍ አድርጓል ብለዋል።ጠቅላይ ሚኒስትሩ እንደገለጹት ከተመዘገቡት ህገ ወጥ ስደተኞች ውስጥ 18ሺ የሚሆኑት ቅጣት ከፍለዋል።በኢ ቪዛ ጨምሮ በ88 ሀገራት የቪዛ አገልግሎት በመክፈት ለ819,278 ሰዎች የቪዛ አገልግሎት መሰጠቱንም ጠቅላይ ሚኒስትሩ አክለው ገልጸዋል።

በቅርቡ ዜጎች ከሀገር እንዳይወጡ ገደብ ከሚጥለው ፍርድ ቤት በተጨማሪ ለኢምግሬሽን ሰራተኞች የሚሰጥ ረቂቅ አዋጅ ለተወካዮች ምክር ቤት ቀርቧል። ይህ ረቂቅ አዋጁ አስፈጻሚው አካል የፍርድ ቤቶችን ስልጣን እንዲሻማ ያደርገዋል የሚል ትችል ቀርቦበታል።

Via Al ain

4 months, 3 weeks ago
በእስር ላይ ከሆነች 2ኛ ሳምንቷን የያዘችው …

በእስር ላይ ከሆነች 2ኛ ሳምንቷን የያዘችው አርቲስት አዲስ ዓለም ጌታነህ በምርመራ ላይ ከ2 ዓመት በፊት ጎንደር ላይ ስለነበራት ቆይታ መጠየቋ ተሰማ።

"ከናሁሰናይ ጋር የፍቅር ግንኙነት አላት" በሚል ከዱባይ እንደተመለሰች ወደ አዲስ አበባ ፖሊስ ታስራ የገባችው አርቲስቷ፤ "በአሁኑ ሰዓት ላይ ከናሁሰናይ ጋር ግንኙነት የለኝም፤ እንደውም እኔ ቪክትም ነኝ" የሚል ማብራሪያ ለፖሊስ እንደሰጠች የነገሩን የፖሊስ ምንጮች፤ መርማሪዎች ምርመራ ሲያደርጉባት የሚጠይቋት ጥያቄ ግን ከ2 ዓመት በፊት ከናሁሰናይ ጋር ጎንደር ላይ ሲተዋወቁ ምን እንደተፈጠረ፣ እንዴት እንደተዋወቁ እንደሆነና ተያያዥ የሆኑ ጉዳዮች እንደሆነ ነግረውናል።

እስካሁን ክስ ያልተመሰረተባት አዲስ ዓለም የምታውቀው ነገር እንደሌለ፤ ለጥምቀት በዓላት ጎንደር እንደምትሄድ ለመርማሪዎች ተናግራለች ሲሉ ምንጮቹ አስታውቀዋል።

አርቲስቷ እስካሁን ፍርድ ቤት አልቀረበችም። አብራትም አንዲት ጓደኛዋ በእስር ላይ እንደምትገኝም ሰምተናል። ( ዘሃበሻ )

አዳዲስ መረጃዎች እንዲደርስዎ Join አድርገው👇በሚፈልጉት አማራጭ ይከታተሉ

በቅንነት ለሌሎች እንዲደርስ ሼር ያድርጉልን🙏

Facebook : bit.ly/42rUuKj
YouTube : bit.ly/3p7kj3N
Twitter : bit.ly/3NVMRrB
Telegram: bit.ly/Huleadis_tele

4 months, 3 weeks ago
Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ …
4 months, 3 weeks ago
አንድ ሰንጋ 650 ሽህ ብር ተጠርቷል።ሌላው …

አንድ ሰንጋ 650 ሽህ ብር ተጠርቷል።ሌላው 550 ሽህ ጥሪ ተሰምቷል።

በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን እነዋሬ ከተማ አስተዳደር በአመት አንድ ጊዜ የሚውለው የሆሳዕና ገበያ ዘንድሮም የተለየ ነገር ታይቶበታል።
ይህ በምስሉ ላይ የሚታየው ሰንጋ 650 ሽህ ብር ተጠርቷል ።የሰንጋው ባለቤት ወጣት ሚጥዬ ታደለ ይባላል። በእነዋሪ ከተማ አስተዳደር ነዋሪ ነው።650 ሽህ ብር የተጠራው የጅሩ ሰንጋ ገና አልተሸጠም።

ሌላው በዚሁ ገበያ የሞረትና ጅሩ ወረዳ የማንጉዶ ቀበሌ ነዋሪ የሆኑት አቶ አበበ በፍቃዱ ለ1 አመት ያክል እንደ ልጄ ስንከባከበው ነበር ያሉትን ሰንጋ በ550 ሽህ ብር ሲሉ ጠርተዋል ሲል የከተማ አስተዳደሩ ሚዲያ አስነብቧል። የሁለቱም ሽያጭ ገና አልተፈፀመም ።

አዳዲስ መረጃዎች እንዲደርስዎ Join አድርገው👇በሚፈልጉት አማራጭ ይከታተሉ

በቅንነት ለሌሎች እንዲደርስ ሼር ያድርጉልን🙏

Facebook : bit.ly/42rUuKj
YouTube : bit.ly/3p7kj3N
Twitter : bit.ly/3NVMRrB
Telegram: bit.ly/Huleadis_tele

4 months, 4 weeks ago
Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ …
We recommend to visit

ለማንኛውም አስተያየት እና ጥቆማ 👉 @Esat_tv_comment_bot

🇪🇹ኢሳት የኢትዮጵያ አይን እና ጆሮ🇪🇹

Last updated 1 week, 1 day ago

በዚህ ቻናል ሀገራዊና አለምአቀፋዊ መረጃዎችን በፍጥነት ያገኛሉ❗
የውስጥ መስመር👉http://t.me/ayulaw

Last updated 2 months, 2 weeks ago

Last updated 1 month, 1 week ago