Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)

Description
ትክክለኛዉ የሁሌ አዲስ ሚዲያ ገፆች

Facebook : bit.ly/42rUuKj
WhatsApp : bit.ly/Huleadis_whatsapp
YouTube : bit.ly/3p7kj3N
Twitter : bit.ly/3NVMRrB
Telegram: bit.ly/Huleadis_tele

ለጥቆማ ና አስተያየት እንዲሁም ለማስታወቂያ ስራ ተከታዮን አድራሻ ይጠቀሙ
bit.ly/3VMy7x7
We recommend to visit

ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ

Last updated 2 months, 3 weeks ago

Last updated 2 months, 2 weeks ago

ይህ ስለ Manchester United መረጃዎችን የሚያገኙበት የ Telegram ቻናል ነው 🇪🇹
--------------------------------------------------------------
☞︎| ስለ ማንቸስተር ዩናይትድ ትኩስ መረጃዎች
☞| ቀጥታ ስርጭቶች ከየስታድየሞቹ
☞| የዝውውር ዜናዎች
☞| ስለ ማንችስተር ዩናይትድ ታሪኮች

📩 ለማስታወቂያ ስራ DM :- @Marcoabdu

Last updated 1 month, 1 week ago

1 month, 1 week ago

የሐኪሞች የስራ አጥነት ቁጥር እየጨመረ ከመምጣቱ በተጨማሪ በተለያዩ በሽታዎች ተይዘው የህይወት ዋጋ እየከፈሉ ነዉ ተባለ፡፡

በህክምና የተመረቁ ስራ አጥ የህክምና ባለሙያዎች ቁጥር እየጨመረ መሆኑን የኢትዮጵያ ህክምና ማህበር አስታዉቋል፡፡

ከዚህ በተጨማሪ ሕክምና የሚያስፈልጋቸው ሐኪሞች ተገቢውን ሕክምና በፍጥነት ባለማግኘታቸው የሕይወት ዋጋ እየከፈሉ ይገኛሉ ተብሏል፡፡

ማህበሩ ሀኪሞች ብዙ ጫናዎችን ተቋቁመው ስራ እየሰሩ ቢሆንም የሰሩበትን የትርፍ ሰዓት ክፍያ ሳይከፈላቸዉ የሚቆዩባቸዉ ክልሎች መኖራቸዉን አንስቷል፡፡

ክፍያ የሚጠይቁ ሐኪሞችም ለእስር የሚዳረጉበት ሁኔታዎች የታዩበት ዓመት ነበር ሲል ማህበሩ ገልጿል፡፡

እንደሕክምና ማህበር ከሚመለከታቸው የስራ ሃላፊዎች ጋር ምክክር ለማድረግ ቢሞከርም፤ አሁንም ከችግሩ ስፋት አንጻር ለብዙዎች ችግር ምላሽ መስጠት አልተቻለም ነዉ ያለዉ፡፡

ከዚህ ቀደም ከጣቢያችን ጋር ቆይታ ያደረጉት የኢትዮጵያ ህክምና ማህበር ፕሬዝዳንት ዶ/ር ተግባር ይግዛዉ ፤ በአገራችን ያሉ የሀኪሞች ቁጥር ወደ 17ሺህ ነዉ ያሉን ሲሆን፤ ከዚህ መሃል ወደ 40 በመቶ የሚሆነዉ ወይም 1ሶስተኛዉ ብቻ የማህበሩ አባል መሆኑን አንስተዋል፡፡

የሙያ ማህበር መቅጠር አይችልም ፤ማድረግ የሚችለዉ ጉዳዩን ማሳወቅ ነዉ ያሉት ዶ/ር ተግባር፤ከጤና ሚኒስቴርም ሆነ ከክልል ጤና ቢሮዎች ጋር በጉዳዩ ላይ መነጋገራቸዉን በወቅቱ አንስተዉ ነበር፡፡

ዘንድሮ 61ኛውን ዓመታዊ የሕክምና ጉባኤና ዓለም አቀፍ የጤና አዉደ ርእይ ከየካቲት 14 – 15/2017ዓ.ም ለማካሄድ ማቀዱንም ማህበሩ አስታዉቋል፡፡
በጉባዔዉ በሃገር ውስጥ እና በውጭ ሃገር የሚኖሩ የህክምና ባለሙያዎች ያላቸውን እውቀት፣ የምርምር ግኝቶችን እና የህክምና ልምዶችን በማቅረብ የዓመቱን መሪ ቃል መነሻ በማድረግ የፓናል ውይይቶች እንደሚካሄዱም ለማወቅ ችለናል፡፡

ማህበሩ ከተመሰረተበት 1940 ዓ.ም ጀምሮ በህክምና አገልግሎት አሰጣጥ ጥራት፣  ደህንነት እና በአጠቃላይ በህክምናው ዘርፍ አገልግሎት በመስጠት ላይ ይገኛል፡፡

#EthioFM

1 month, 1 week ago

ቀሲስ በላይ መኮንን በ5 ዓመት ጽኑ እስራትና በ10 ሺህ ብር የገንዘብ መቀጮ ተቀጡ

የፌደራል ከፍተኛ ፍ/ቤት ልደታ ምድብ 3ኛ የሙስና ጉዳዮች ወንጀል ችሎት በእነ ቀሲስ በላይ መኮንን መዝገብ ላይ የቀረቡ የግራ ቀኝ ማስረጃዎችን መርምሮ በዛሬው የችሎት ቀጠሮ በጽኑ እስራትና በገንዘብ መቀጮ እንዲቀጡ ወሰነ።

የፍትህ ሚኒስቴር የሙስና ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ዐቃቤ ሕግ በተከሳሾች ቀሲስ በላይ መኮንን፣ በግብርና ኢንቨስትመንት ላይ የተሰማራው እያሱ እንዳለ፣ በኮሚሽን ስራ ላይ የተሰማራው በረከት ሙላቱ እና አለምገና ሳሙኤል እንዲሁም የኒሞና ንግድ ስራ ኃላ/የተ/የግል ማህበር ስራ አስኪያጅ አበራ መርጋ በተባሉ ተከሳሾች ላይ በ1996 ዓ.ም የወጣውን የወንጀል ህግ ቁጥር 32 ንዑስ ቁጥር 1 (ሀ) እና የሙስና ወንጀሎች ለመደንገግ የወጣውን አዋጅ ቁጥር 881/2007 አንቀፅ 32 ንዑስ ቁጥር 2 እና ንዑስ ቁጥር 3 ስር የተመለከተውን ድንጋጌ እና በ1996 ዓ.ም የወጣውን የወንጀል ህግ ቁጥር 382 ንዑስ ቁጥር 1 ስር የተመለከተውን ድንጋጌ መተላለፋቸውን ጠቅሶ ዝርዝር ክስ አቅርቦባቸው ነበር።

በዚህም ተከሳሾቹ ከአፍሪካ ህብረት ምንም አይነት የክፍያ ትዕዛዝ ባልተሰጠበት ሁኔታ ላይ ተከሳሾች በተለያየ መጠን ክፍያ እንዲፈጸምላቸው የሚል አጠቃላይ የ6 ሚሊየን 50 ሺህ ዶላር ሀሰተኛ የክፍያ ሰነድ በአንደኛ ተከሳሽ አማካኝነት ለባንኩ መቅረቡ ተጠቅሶ በሁሉም ተከሳሾች ላይ ከባድ የማታለል ሙስና ወንጀል ክስ ማቅረቡ ይታወሳል።

በዚህ መልኩ የቀረበውን ዝርዝር ክስ ከ1ኛ እስከ 3ኛ ተራ ቁጥር የተጠቀሱት ተከሳሾች ብቻ ችሎት ቀርበው የክስ ዝርዝሩ እንዲደርሳቸው የተደረገ ሲሆን 4ኛ እና 5ኛ ተከሳሾች በአድራሻቸው ባለመገኘታቸውና በተደጋጋሚ ቀጠሮ ባለመቅረባቸው ለጊዜው ክሳቸው እንዲቋረጥ ተደርጓል።

ከ1ኛ እስከ 3ኛ ተራ ቁጥር የተጠቀሱ ተከሳሾች ክሱ እንዲሻሻልላቸው ያቀረቡት የመጀመሪያ ደረጃ ክስ መቃወሚያ ነጥቦችን ፍርድ ቤቱ መርምሮ ወደፊት በማስረጃ የሚጣራ መሆኑን ገልጾ መቃወሚያቸውን አልተቀበለውም።

ከዚህም በኋላ ተከሳሾቹ በክሱ ላይ የተጠቀሰውን የወንጀል ድርጊት አለመፈጸማቸውን ጠቅሰው የዕምነት ክህደት ቃል መስጠታቸውን ተከትሎ ዐቃቤ ሕግ አጠቃላይ ሶስት ምስክሮችን አቅርቦ ምስክርነታቸውን አሰምቶ ነበር።

ፍርድ ቤቱ የምስክሮችን ቃል መርምሮ በክሱ ዝርዝር የተጠቀሰው የወንጀል ድርጊት መፈጸሙን በዐቃቤ ሕግ በማስረጃ ማረጋገጡን ጠቅሶ በአንደኛው ክስ ብቻ እንዲከላከሉ በሙሉ ድምጽ ብይን ሰጥቶ ነበር።

ሁለተኛውን ክስ በሚመለከት በሐሰተኛ ሰነድ የተፈጸመ ድርጊት መሆኑ በአንደኛውን ክስ ላይ መገለጹን ተከትሎ በሰበር ሰሚ ችሎት ትርጉም የተሰጠባቸው በተደራራቢነት የቀረቡና ተጠቃልለው ሊያስቀጡ የሚችሉ ድንጋጌዎች መኖራቸውን ፍርድ ቤቱ አብራርቶ ሁለተኛውን ክስ ውድቅ በማድረግ በአንደኛው ክስ ብቻ በከባድ አታላይነት ሙስና ወንጀል እንዲከላከሉ ብይን ሰጥቷል።

ሆኖም ተከሳሾቹ እንዲከላከሉ በሰጠው ብይን የዐቃቤ ሕግ ማስረጃን በተገቢው ማስተባበል አለመቻላቸው ተጠቅሷል።

በዚህም 1ኛ ተከሳሽ ቀሲስ በላይ መኮንን በሙሉ ድምጽ የጥፋተኝነት ፍርድ የተሰጠባቸው ሲሆን፤ 2ኛ እና 3ኛ ተከሳሾች በአንድ ዳኛ የሀሳብ ልዩነት በአብላጫ ድምጽ ጥፋተኛ ተብለዋል።

የሀሳብ ልዩነት ያቀረቡት አንደኛው ዳኛ 2ኛ እና 3ኛ ተከሳሾችን በሚመለከት የባንክ ሂሳባቸው በመገለጹ ብቻ የወንጀል ተግባሩ በስምምነት ተፈጽሟል ለማለት አያስችልም የሚል የሀሳብ ልዩነት እንዳላቸው ጠቅሰው ልዩነታቸውን አሳይተዋል።

ፍርድ ቤቱ የግራ ቀኝ የቅጣት አስተያየት መርምሮ ዐቃቤ ሕግ ወንጀሉ የተፈጸመው በትብብር መሆኑን ጠቅሶ ያቀረበውን የቅጣት ማክበጃ ይዟል።

በዚህም1ኛ ተከሳሽ ቀሲስ በላይ መኮንን ያቀረቡትን አራት የቅጣት ማቅለያ በመያዝ በዕርከን 21 መሰረት በ5 ዓመት ጽኑ እስራትና በ10 ሺህ ብር የገንዘብ መቀጮ እንዲቀጡ ወስኗል።

2ኛ እና 3ኛ ተከሳሾችን በሚመለከት ደግሞ እያንዳንዳቸው አራት፣ አራት የቅጣት ማቅለያ አስተያየት በመያዝ በዕርከን 17 መሰረት በ3 ዓመት ከ3 ወር ጽኑ እስራትና በ3 ሺህ ብር የገንዘብ መቀጮ እንዲቀጡ ወስኗል።

በፍርድ ቤቱ በተከሳሾች ላይ የተወሰነውን የጽኑ እስራት ውሳኔን የአዲስ አበባ ማረሚያ ቤት እጃቸው ከተያዘ ጀምሮ ታሳቢ በማድረግ እንዲያስፈጽም ታዟል።

በታሪክ አዱኛ

1 month, 1 week ago

በጌታቸው ረዳ ላይ የሚደረገው የመፈንቅለ መንግስት ሙከራ ልንለው እንችል ይሆን ?

በዛሬው እለት የታጠቁ ግለሰቦች መቐለ ኤፍኤም 104.4 ሬድዮን ለመቆጣጠር ሙከራ አርገው ነበር ተባለ

በትግራይ ክልል ባለስልጣናት መሀል እየተካረረ የመጣውን ውዝግብ ተከትሎ በዛሬው እለት የታጠቁ ግለሰቦች የመቐለ ኤፍኤም 104.4 ሬድዮን ለመቆጣጠር ሙከራ አርገው እንደነበር ታውቋል።

ሙከራው የተካሄደው በዶ/ር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል በሚመራው ቡድን አባላት መሆኑን ምንጮቻችን ጠቅሰው ሙከራው ግን ያልተሳካ ነበር ብለውታል።

"ታጣቂዎቹን ወደ ሬድዮ ጣቢያው ይዞ የገባው በእነ ዶ/ር ደብረፅዮን የተሾመ ዘመንፈስ ቅዱስ ፍስሃ የተባለ ግለሰብ ነው" ያሉት ምንጫችን ድርጊቱ ሲከሽፍ የኤፍኤም ሬድዮ ጣቢያውን ማህተም ይዘው ሲወጡ በፖሊስ ቁጥጥር ስር መዋላቸውን ጠቁመዋል።

ምን ያህል ታጣቂዎች ወደ ሬድዮ ጣብያው እንደገቡ እንዲሁም አላማቸው ምን እንደነበር እስካሁን የተገለፀ ነገር የለም።

Via (መሠረት ሚድያ)-

3 months, 4 weeks ago

ዶናልድ ትራምፕ ለቢሊየነሩ ኤለን መስክ ሹመት ሰጡ

ተመራጩ የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ቢሊየነሩን ኤለን መስክ አዲስ ባቋቋሙት የመንግስት መስሪያ ቤቶች አፈጻጸም ዲፓርትመንት (ዲኦጂኢ) መሪ አድርገው ሾመዋቸዋል።

አዲስ የተመሰረተው ይህ ተቋም ከመንግስት መዋቅር ውጪ ሲሆን ተግባሩም በዋናነት የመንግሰት መስሪያ ቤቶችን አፈጻጸም መፈተሽና መዋቅራዊ ማስተካከያ ምክረ ሃሳብ ማቅረብ መሆኑ ተገልጿል።

የባዮ ቴክኖሎጂ ስራ ፈጠራ ባለሙያ ቪቪክ ራማስዋሚ አዲስ የተቋቋመውን መስሪያ ቤት ከኤለን መስክ ጋር በጋራ እንደሚመሩት አናዶሉ ዘግቧል።

ሹመቱን አስመልክቶ ዶናልድ ትራምፕ “ሁለቱ ሰዎች በኔ አስተዳደር ዘመን የተንዛዛ የመንግስት ቢሮክራሲን የማፈራረስ፣ የበዛ ቁጥጥርን እና ለብክነት የሚያጋልጡ ወጭዎችን መቀነስ እንዲሁም የፌደራል ኤጀንሲዎችን እንደገና በማሻሻል መንገድ ይከፍታሉ” ብለዋል።

ትራምፕ አዲሱን ተቋም የዚህ ዘመን “የማንሃታን ፕሮጀክት” በማለት አሜሪካ አቶሚክ ቦንብ ለመስራት ከተጠቀመችበት የፕሮጀክት ስም ጋር አነጻፅረውታል።

አማካሪው ተቋም በፌደራል መስሪያ ቤቶች የአፈጻጸም ድክመቶችን በመፍታት እና ፈጠራ የታከለበት የመንግስታዊ አሰራርን በማስተዋወቅ ጥረቱ ከነጩ ቤተ መንግስትና ከከበጀትና አስተዳደር ቢሮ ጋር በትብብር ይሰራል ተብሏል።

ኤለን መስክ አዲሱ መስሪያ ቤት በመንግስት አሰራር ስርዓትና በገንዘብ ብክነት ውስጥ በተሳተፉ በርካታ ሰዎች ዘንድ አስደንጋጭ መልዕክት ያስተላልፋል ብለዋል።

ይህ አዲሱ ተቋም አሜሪካ ለዓመታዊ ወጭዋ ከመደበችው 6 ነጥብ 5 ትሪሊዮን ዶላር ላይ የሚባክነውንና በሙስና የሚጭበረበረውን ሀብት እንደሚያስቆመው ትራምፕ ተናግረዋል።

ተቋሙ ተልዕኮውን አሜሪካ የተመሰረተችበትን 250ኛ የልደት በዓሏን በምታከብርበት በፈረንጆቹ ሐምሌ 4/2026 እንደሚያበቃም ተጠቅሷል።

3 months, 4 weeks ago

‘’መንግስት በሚወጡ የትምህርት ፖሊሲዎች ዙርያ ግብዓቶችን እንዳቀርብ ይጠይቀኝና፤ ያቀረብኳቸው ግብዓቶች ግን በቅጡ ሳያያቸው ውድቅ ያደርጋቸዋል’’ ሲል የኢትዮጵያ የግል ከፍተኛ የትምህርት እና የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ማህበር ተናገረ፡፡

ማህበሩ በተለያዩ ጊዜያት በትምህርት ሚኒስቴር እና በትምህርትና ስልጠና ባለስልጣን በኩል በሚወጡ ፖሊሲዎችና መመሪያዎች ላይ ያለውን አተያይ እና የመፍትሄ ሀሳቦች ጥናት አድርጎ እንደሚያቀርብ ተናግሯል፡፡

‘’ነገር ግን እነዚህን በመንግስት ተጠይቆም ሆነ በራሱ ተነሳሽነት የሚያቀርባቸው ግብዓቶችና የመፍትሄ ሀሳቦች በአግባቡ እንኳ ታይተው አያውቁም’’ ሲል ማህበሩ ዓመታዊ ጉባኤውን ባካሄደበት ወቅት ሲናገር ሰምተናል፡፡

የማህበሩ ፕሬዚደንት አረጋ ይረዳው(ዶ/ር) በተለያዩ ጊዜያት በሚወጡ የትምህርት ፖሊሲዎች ዙሪያ ዘርፉን አይተን እና ጥናት አድርገን ለፓርላማ አቅርበን፤ ፓርላማውም ከተቀበለን በኋላ ምንም ታሳቢ ሳያደርጋቸው ወደ ጎን ትቷቸዋል ብለዋል፡፡

‘’የምናቀርባቸው ግብዓቶች ታሳቢም ሆነ ተግባራዊ የማይደረጉ ከሆነ የኛ ድካም ትርፉ ምንድነው?’’ ሲሉም ጠይቀዋል፡፡

በተጨማሪም በትምህርት ሚኒስቴር እና በትምህርትና ስልጠና ባለስልጣን በኩል ተናቦ የመስራት ክፍተት እንደሚያዩም አስረድረዋል፡፡

በማህበሩ የቀረበው ቅሬታን በተመለከተ ሸገር ራዲዮ በህዝብ ተወካዎች ምክር ቤት የሰው ሀብት፣ ስራ ስምሪት፣ ድልድል እና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አባል የሆኑት ታደሰ በዛ (ዶ/ር)ን ጠይቋል፡፡

ዶ/ር ታደሰ ‘’መንግስት ከዚህ በፊት ትኩረት ያደርግ የነበረው በራሱ የሚተዳደሩት የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ላይ ነበረ፤ አሁን ግን የግሉንም በማካተት አዲስ ማዕቀፍ ተዘጋጅቶ የክትትልና የቁጥጥር ስራ እየተሰራ ነው’’ ብለዋል፡፡

የግል የከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ለሀገር የሚያበረክቱት አስተዋጽኦ ትልቅ ነው፤ መንግስትም ይህንንይረዳል ብለዋል የቋሚ ኮሚቴው አባል፡፡

በሚወጡ የትምህርት ፖሊሲዎችና መመሪያዎች የግሎቹ ታሳቢ እንደሚደረጉ አስረድተዋል፡፡

Sheger Fm

3 months, 4 weeks ago

መንግሥት ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ያቀረበው አዲሱ የባንክ ሥራ አዋጅ፣ በባንክ ሥራ ላይ ለመሠማራት የሚፈልጉ ትውልደ ኢትዮጵያዊያን ከአገር ውስጥ ወይም ከውጭ አገር ኢንቨስተርነት አንዱን ብቻ እንዲመርጡ እንደሚያስገድድ ተገልጧል።

ኢትዮጵያ ውስጥ አክሲዮን የገዙ ትውልደ ኢትዮጵያዊ የኾኑ የውጭ አገር ዜጎች ግን እንደ አገር ውስጥ ኢንቨስተር የመቆጠር መብት እንዳላቸው ረቂቅ አዋጁ መደንገጉን ኢትዮጵያ ኢንሳይደር ዘግቧል። እንደ ውጭ ዜጋ መቆጠር የሚፈልጉ ትውልደ ኢትዮጵያዊያን፣ ለውጭ ዜጎች የተደነገጉ ድንጋጌዎች ተፈጻሚ ይኾኑባቸዋል ተብሏል።

ረቂቅ አዋጁ የውጭ ዜጎች ባንድ ባንክ ውስጥ መያዝ የሚችሉትን የአክስዮን መጠን፣ ከባንኩ የተፈረመ ካፒታል ውስጥ ከ49 በመቶ እንዳይበልጥ ገደብ እንደጣሉ ዘገባው ጠቅሷል።

4 months ago

ሰበር .. ቤተመንግሥት የተደበቀው 400 ኪ/ግ ወርቅ ሚስጥር ? | ነገስታቶችን ያስወቀሰዉ ጉዳይ | እዉነታዉ ምን... https://youtube.com/watch?v=auBVBrJWu_g&si=eA85_REy6galxjCP

4 months ago
በኢኳቶሪያል ጊኒ ከታዋቂ ሴቶች ጋር ሲፈፅም …

በኢኳቶሪያል ጊኒ ከታዋቂ ሴቶች ጋር ሲፈፅም የነበረውን ወሲብ፤ በቪዲዮ ካሴቶች ያከማቸው ባለስልጣን

የኢኳቶሪያል ጊኒ የፋይናንስ ምርመራ ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር ባልታሳር ኢንጎንጋ ከታዋቂ ሴቶች እና የባለስልጣናት ዘመዶች ጋር ከቢሮ እና በተለያዩ ቦታዎች ወሲብ ሲፈፅም የሚያሳዩ ቪዲዎች አከማችቶ ተገኝቷል።

ቪዲዮው የሀገሪቱን ፕሬዝዳንት እህት ጨምሮ የታዋቂ ሰዎችን የወሲብ ህይወት የሚያሳይ ነው የተባለ ሲሆን ከ400 በላይ የወሲብ ካሴቶችን በባለስልጣኑ ቢሮ እና መኖሪያ ተገኝቷል ተብሏል።

ድርጊቱ የተጋለጠው የ54 አመቱ ኢንጎንጋ በተጠረጠረበት የማጭበርበር ወንጀሎች ላይ ተመስርቶ በተደረገ ፍተሻ ነው።

በዚህም ባለስልጣኑ በቤቱ እና በቢሮው ውስጥ ወሲባዊ ግንኙነቶችን በቢሮው እና በተለያዩ ቦታዎች ሲፈፅም የሚያሳዩ ቪዲዮዎች በማህበራዊ ትስስር ገጾች ተሰራጭተዋል።

በቪዲዮ ቅጂው ከታዩት ውስጥ የፕሬዝዳንት ቴዎዶሮ ኦቢያንግ ንጉማ ምባሶጎ ​​እህት፤ የከፍተኛ ባለስልጣናት የትዳር አጋሮች ጨምሮ የቅርብ የቤተሰብ አባላት እና ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት ዘመዶች እንደሚገኙ አፍሪካ ኒውስ ዘግቧል።

ሮይተርስ በበኩሉ በቪዲዎቹ ላይ የሚታዩትን ባለስልጣናት እና ትክክልኝነት ማረጋገጥ እንዳልቻለ ገልጿል።

የቪዲዮ ቅጂዎቹ በማህበራዊ ትስስር ገጾች ከወጡ በኃላ ከፍተኛ የህዝብ ቁጣ በመቀስቀስ የብዙሃን መገናኛዎችን ቀልብ ስቧል።

የአገሪቱ ምክትል ፕሬዝደንት ቴዎዶሮ ኦቢያንግ ማንጉ ማንኛውም ሰራተኛ በስራ ቦታ የወሲብ ድርጊት ሲፈጽም ከተገኙ “የሥነ ምግባር ደንቡን በመጣስ” እንደሚታገድ ገልፀዋል።

እኚህን መሰል ድርጊቶች ለመከላከልም የክትትል ካሜራዎችን በፍርድ ቤት እና በሚኒስቴር መስሪያ ቤቶች እንዲገጠሙ አዘዋል።

4 months, 1 week ago

የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአፍሪካ በአይነቱ የመጀመሪያው ነው የተባለውን ኤይርባስ A350-1000 የተሰኘውን አዲስ አውሮፕላን ተረክቧል፡፡

አየር መንገዱ በፈረንሳይ ቱሉስ በተከናወነው ስነስርዓት ከአውሮፕላን አምራቹ ኤርባስ ኩባንያ የተረከበውን የመጀመሪያውን አውሮፕላን ዛሬ በአዲስ አበባ ቦሌ ዓለማቀፍ አየር ፣ማረፊያ አስተዋውቋል፡፡

አቪየሽን ሳንስ ፊሮንተርስ ከኤርባስ ጋር በመሆን ለኢትዮጵያ አየርመንገዶች ፋውንዴሽን የተበረከተውን በ100 ሺህ ዩሮ የሚገመት የህክምና ቁሳቁስ ተሸክሞ በአየርመንገዱ ባለስልጣናት ከሰዓቱን አዲስ አበባ የደረሰው አውሮፕላኑ ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት እና ዲፕሎማቶች በተገኙበት በደማቅ ስነስርዓት አቀባበል ተደርጎለታል፡፡

በአውሮፕላኑ አቀባበል ስነስርዓት ወቅት ንግግር ያደረጉት የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ስራ አስፈጻሚ መስፍን ጣሰው ዛሬ አየር መንገዱ የተቀበለው ኤይርባስ A350-1000 አውሮፕላን አየር መንገዱ ካዘዘው አራት አውሮፕላኖች አንዱ ነው፡፡

4 months, 1 week ago

በኢትዮጵያ እየተከሰተ ያለው የመሬት መንቀጥቀጥ ለ10 ሺህ ገደማ ሰዎች የእሳተ ገሞራ ፍንዳታ ስጋት እንደሆነ ተጠቆመ

'Gelology Hub' በሚል የሚታወቀው እሳተ ገሞራዎችን እና የመሬት እንቅስቃሴዎችን በተመለከተ ትንታኔ የሚያቀርበው ድርጅት እንዳለው በአለም ዙርያ ትኩረት የተነፈገው ይህ አደገኛ ክስተት የእሳተ ገሞራ ፍንዳታን ሊያስከትል የመቻል እድሉ ከፍተኛ ነው።

በኢትዮጵያ እየተካሄዱ ያሉ ግጭቶች እና ጦርነቶች ይህ ተፈጥሮአዊ አደገኛ ክስተት ብዙ ትኩረት እንዳያገኝ አድርጎታል የሚለው Geology Hub ይህን መረጃ ለህዝብ ማድረስ የፈለገው የሰው ህይወት ለማትረፍ ነው ብሏል።

ከመስከረም ወር ጀምሮ ከፍተኛ የሆነ የቀለጠ አለት ክምችት እየታየ መሆኑን ገልጾ እስካሁን ከአደጋው አካባቢ 700 ገደማ ሰዎች እንዲነሱ መደረጉን ገልጿል።

በዚህ አደገኛ ስፍራ የሚገኙ 10 ሺህ ገደማ ሰዎች በአስቸኳይ ከስፍራው እንዲነሱ መደረግ እንዳለባቸው የሚገልፀው Gelology Hub ይህን ጉዳይ በዋሽንግተን ዲሲ ለሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ እና ለአሜሪካው የጂኦሎጂካል ሰርቬይ ማሳወቁን ጨምሮ ጠቅሷል።

21 ኪ/ሜ ርዝመት ያለው ይህ የእሳተ ገሞራ ግፊት በመካከለኛ ኢትዮጵያ አዋሽ አካባቢ እንቅስቃሴው እንደቀጠለ የታወቀ ሲሆን ከዚህ ጋር ተያይዞ ከዚህ በፊት በአካባቢው ያልነበሩ አዳዲስ ሙቅ ውሀዎች መፍለቅ መጀመራቸውም ታውቋል።

ለአራተኛ ግዜ በአዋሽ ፈንታሌ እስከ 4 ነጥብ 7 ሬክተር ስኬል የተመዘገበ የተለያየ ደረጃ ያለው የመሬት መንቀጥቀጥ መከሰቱን ሠመራ ዩኒቨርሲቲ አስታውቆ ነበር።

መሠረት ሚዲያ

We recommend to visit

ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ

Last updated 2 months, 3 weeks ago

Last updated 2 months, 2 weeks ago

ይህ ስለ Manchester United መረጃዎችን የሚያገኙበት የ Telegram ቻናል ነው 🇪🇹
--------------------------------------------------------------
☞︎| ስለ ማንቸስተር ዩናይትድ ትኩስ መረጃዎች
☞| ቀጥታ ስርጭቶች ከየስታድየሞቹ
☞| የዝውውር ዜናዎች
☞| ስለ ማንችስተር ዩናይትድ ታሪኮች

📩 ለማስታወቂያ ስራ DM :- @Marcoabdu

Last updated 1 month, 1 week ago