ሎሬት ፀጋዬ ገብረመድህን እና ሌሎችም

Description
📓• ድርሰት ህይወት ነው ።

•|➮ የህይወት ትርጉም ያለው ማንበብ ውስጥ ነው።
•|➮ ማንበብ ውስጥ ራስን ማግኘት አለ
•|➮ ራስን ማግኘት ውስጥ ቤተሰብን ማግኘት አለ
•|➮ ቤተሰብ ውስጥ ሀገር
•|➮ ሀገር ውስጥ ፍቅርን
•|➮ ከሀገር ከቤተሰብ ከፍቅር ከፈጣሪ ከነዚህ በላይ ደሞ ምንም የለም !!

•══════════

📚•|For any promotion • Contact Admin @eyosiii
We recommend to visit

ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ

Last updated 2 months, 3 weeks ago

Last updated 2 months, 2 weeks ago

ይህ ስለ Manchester United መረጃዎችን የሚያገኙበት የ Telegram ቻናል ነው 🇪🇹
--------------------------------------------------------------
☞︎| ስለ ማንቸስተር ዩናይትድ ትኩስ መረጃዎች
☞| ቀጥታ ስርጭቶች ከየስታድየሞቹ
☞| የዝውውር ዜናዎች
☞| ስለ ማንችስተር ዩናይትድ ታሪኮች

📩 ለማስታወቂያ ስራ DM :- @Marcoabdu

Last updated 1 month, 1 week ago

2 weeks, 5 days ago

ዝምተኛ ልቦች

አምነው የወደዱ፣
ወደው የተካዱ፣
ተክደው የራዱ፣
ፍርሃት አንሸራቶ ቁልቁል የጣላቸው፣
የብቸኛ ልቦች የትነው መውደቂያቸው?
የትነው መድረካቸው?
ማነው አጃቢያቸው?
እንዴት ነው ምታቸው?
የተካዱ ልቦች አጋር የራቃቸው፣
የሚያቀነቅኑት ምንድን ነው ዜማቸው?
የተመረኮዙት እምነት ታጥፎባቸው፣
ድንገት የወደቁ ፍቅር ያዳጣቸው፣
ሚስጥር የሚያጋሩት ሰው የበረዳቸው፣
ብቸኝነት ሰርጎ ብቻ ያስቀራቸው፣
ዝምተኛ ልቦች ምን ይሆን ቋንቋቸው?
ከየት ነው ጥሪያቸው?
በየት ነው ጉዟቸው?
የት ነው መድረሻቸው?
እንደ ሰብአሰገል ጠቅሶ የሚመራቸው፣
የቃተቱ ልቦች የታል ኮከባቸው?
መቼም ከአምላክ ትንፋሽ ከውሃ ከአፈሩ፣
ከእምንት እና እውነት ከፍቅር ሲሰሩ፣
ዝምተኛ ልቦች ጥንቱን ሲፈጥሩ፣
ተገፍትረው ወድቀው፣
ደቀው እንዳይቀሩ፣
በተስፋ ጸንተው ነው ዘላለም ሊኖሩ

✍️✍️ አርቲስት ጌትነት እንየው

@lotet_tsegaye
@loret_tsegaye

1 month, 1 week ago
1 month, 1 week ago

አትገለን የለንም
የፃድቃኖች አርማ
አትቀጣን አንችል
ፍጡር ነን ደካማ
ብቻ....
ብቻ ይኼዉ አለን
እኛ ስናጨልም አንተ ስታበራ
መሃሪዉ ክርስቶስ.....
አንተ በኛ እፈር እኛ ባንተ እንኩራ

✍️✍️ Geni
#From our subscribers

@loret_tsegaye
@loret_tsegaye

4 months, 1 week ago
6 months, 2 weeks ago

የፍቅር ቀጠሮ

ጠበቅኩሽ እኔማ እዚያው ሥፍራ ቆሜ
በአክሱም ቁመና በላሊበላ ዕድሜ
እግሮቼን ተክዬ ቀኔን አስረዝሜ
በሔድሽበት መንገድ ልቤ እንደነጎደ
ስንት ነገር መጣ ስንት ነገር ሄደ
ስንት ጊዜስ ነጋ ስንቴ ጎህ ቀደደ
ስንቴ ዝናብ ጣለ ስንት ጊዜ አባራ
ትመጫለሽ ብዬ በቆምኩበት ሥፍራ
ስንቴ አድማሱን ማተርኩ ስንትና ስንት ዓመት
አንገቴን አስግጌ በራስ ዳሽን ቁመት
በአክሱም ቁመና በላሊበላ ዕድሜ
በቀጠርሽኝ ሥፍራ ስጠብቅሽ ቆሜ
ስንት ሳቅ አለፈ ስንትና ስንት ዕንባ
ስንቴስ ክረምት ሆነ ስንቴ ፀደይ ጠባ
ስንቱ ተገናኘ ስንቱ ሰው ተጋባ
ሽል ስንቴ ልጅ ሆነ ስንትስ ጊዜ አረጀ
ስንት ኮት ጨረሰ ስንት እንጀራ ፈጀ
ስንት ዓይነት ሞት አየሁ ስንት ዓይነት ፍፃሜ
በአክሱም ቁመና በላሊበላ ዕድሜ
በቆምኩበት ሥፍራ ስጠብቅሽ ቆሜ?
ስንት ውበት አለፈ ስንት ውበት ነጎደ
ስንት ትውልድ መጣ ስንት ትውልድ ሄደ
ስንት ዕውነት ከፍ አለ ስንት ዕውነት ወረደ
ስንት ዓለም ተሻረ ስንት ዓለም ነገሠ
ስንት ሀገር ተሰራ ስንት አገር ፈረሠ
ስንት ሺህ ዓመት ሸኘሁ ስንት ሺህ ተቀበልኩ
እዚያች ሥፍራ ቆሜ አንችን እየጠበቅኩ
እግሬን አስረዝሜ ቆየሁ ቆየሁና
በላሊበላ ዕድሜ በአክሱም ቁመና
ሳትመጪ ወደኔ ሳላገኝሽ ገና
ብዙ ነገር መጥቶ ብዙ ነገር ያልፋል
የራስ ዳሽን ራስ አንገቱን ይደፋል
አክሱምም ተንዶ እንደጨው ይረግፋል
ላሊበላም ወርዶ ቁልቁል ይነጠፋል
ሰማይና ምድርም ያልፋሉ ታያለሽ
እኔ ግን እዛው ነኝ አንች እስክትመለሽ…

✍️✍️ታገል ሰይፉ

@loret_tsegaye
@loret_tsegaye

6 months, 3 weeks ago

"ህልሜን አላቀልጥም"

ወታደርም ቢባል
ያው በቀቀናም ነው፣
ፍርሃት አለ ውስጡ፣
አሸናፊም ብትል
ይፈራል ነገውን
ፍርሃት አለው ነውጡ፣
ንጉሠ ነገሥትም
ፍርሃት አለ ቆጡ፣
አንበሳ ደቦሉም
ፍርሃት አለ ውስጡ፣
ማንኛውም ብትል
ጠልፎ የሚጥል ሰው
ፍርሃት አለ ውስጡ፣
"ብተወውስ" ብሎ
ይፈራል ታንቲራ፤
እኔ ግን የምልህ
ህልምህን አትፍራ፣
ድፈረው፣ ድፈረው
ወንጀለኛ አይልህም ፍርድ ቤቱ ደፍሮ
አቃቤ ህግ አይከስ፣
እንዲያውም ይፈራል-ይፈራል ወጥሮ
ህልምህን የምተው...
ወመኔ 'ሚዘራው
ገንዘብ ስላጣህ ነው?
ተስፋ ስላጣህ ነው?
ያዘው ግፋ ብሎ
ተስፋን የሚመግብ
ቤተሰብ ነው ያጣህ?
ወይስ ነው ከጀርባህ
ኦና ሆኖ ታየህ?
እኔ ግን የምልህ
እኔ የምመክርህ፣
እንዳትመለስ ነው
ከተስፋ ከእድልህ
እኔ የሚታየኝ
እኔ እንደሚሰማኝ፣
ችግርም ብትፈጥር
በራስህ ላይ ወጥር
ለውጥ አምጣ
ለውጥ አምጣ
ቀን አውጣ
ቀን አውጣ
ችግርና ፍዳህ የመኖርህ ትርጉም
ላብ ነህ ለዚህ ምድር
ወዝ ነህ ለዚህ ዓለም፡፡
ወዝና ጊዜየን በቁሜ ብቀማም
እንደ አሸን ተራግፈው
ጓደኞቼን ባጣም
ወደሁዋላ ስዞር
አንድም ሰው ባይመጣም
ተስፋዬን አልሸጥም
ህልሜን አላቀልጥም፡፡

✍️✍️ ይስማዕከ ወርቁ

@loret_tsegaye
@loret_tsegaye

7 months ago

ሞት አያምም

እኖር ብዬ ብታረድም
ለመኖር ስል ብሰደድም
እኖር ብዬ ብዋረድም
ዘጠኜ ሞቴን ብሞተው…
አንዴ እንደመኖር አይከብድም!
መኖር ከመምት አይልቅም
ሞት እንደሕይወት አይጨንቅም፡፡

የሞተ ‹‹እሞታለሁ›› ሲል…
በጭራሽ አያውቅም ፈርቶ፡፡
ያልኖረ አያውቅም ሞቶ።
መኖር እንጂ የሚያስፈራኝ
መኖር እንጂ የሚያስገፋኝ
መኖር እንጂ የገደለኝ
መኖር እንጂ የበደለኝ
ሞት አያምም ካቆሰለኝ
ምት አያምም ከገደለኝ!

✍️✍️ በላይ በቀለ ወያ

@loret_tsegaye
@loret_tsegaye

7 months, 1 week ago

ፈተሽ እንጋባ

የሰርጌ ቀን መሃላ፣ ሃጥያት ገለመሌ
ኩነኔ ነው ይሄ፣ አመልህ አመሌ
ጡር አለው ምናምን፣ እንዲያ አትበይኝ
ይልቅ ከወደድሽኝ፣ ፈተሽ ተከተይኝ።
"
ደሞ መሃላ ላልሽው
ሳትፈሪ መልሽው
በውነት' ለማገልገል'፣ ለአንዲት አላማ
ምሎ ተገዝቶ፣ በሃገር ፓርላማ
የአምስት መቶ ሰው፣ ማላ ተርከፍክፎ
ሃገር ከተሸጠ፣ ከተሰጠ ታልፎ
ስለ መሃላ ፈርተሽ፣ ለምን መክሰራችን
ሃገር በሸጠ ፊት፣ ፅድቅ ነው ስራችን
ሁሉም በየዘርፉ፣ በመሃላ ከታጨ
ኩነኔ ደርሶበት፣ ፂም እንኳን ካላጨ
የዚህ ሁሉ ምዑር፣ መሃላ ከጠፋ
የምን ኩነኔ ነው፣ ነይ ፈተሽ እንጥፋ።

✍️✍️እንግዳዬሁ ዘሪቱ

#From our subscribers

@loret_tsegaye
@loret_tsegaye

7 months, 3 weeks ago

ስርቆሽ

አልመለስ ያለ ትውልድ
አዳኝ መርከቧን ንቆ
በጥፋት ውሃ ሰጠመ
በዝሙት ሃጥያት ወድቆ
ኀላም ውሃው እንደጠፈፈ
ምድርን 'ሀ' ብሎ ሲያቀና
ኖህ በኩራት እንደቆመ
ፍጥረቱን ሰበሰበና
በቅደም ተከተላቸው
በጥምረት እንዳሳፈረ
ከመርከቡ ሊያወርዳቸው
አንድ በአንድ እየቆጠረ
አጋር የሌለው ፍጥረት
መጀመሪያ ያልነበረ
አንድ እንስሳ ትርፍ ቀረ
ለካስ የዝሙት መንፈስ
ከአህያ ጋር ተሳፍሮ
ሚስቱን እየደበቀ
ከፈረስ ፍቅር ጀምሮ
ከማይሆን ተኝቶ ኖሮ
ከመርከቡ እንደወረደ
መሃን በቅሎን ወለደ!

እንግዲህ ከኖህ ጀምሮ
ዘመን ዘመንን አያደሰ
የጥፋት ውሃም የለ
ዝሙትም እዚህ ደረሰ፡፡

✍️✍️ ሜሮን ጌትነት

@loret_tsegaye
@loret_tsegaye

8 months, 3 weeks ago

ተማሪ ነህ ?

We recommend to visit

ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ

Last updated 2 months, 3 weeks ago

Last updated 2 months, 2 weeks ago

ይህ ስለ Manchester United መረጃዎችን የሚያገኙበት የ Telegram ቻናል ነው 🇪🇹
--------------------------------------------------------------
☞︎| ስለ ማንቸስተር ዩናይትድ ትኩስ መረጃዎች
☞| ቀጥታ ስርጭቶች ከየስታድየሞቹ
☞| የዝውውር ዜናዎች
☞| ስለ ማንችስተር ዩናይትድ ታሪኮች

📩 ለማስታወቂያ ስራ DM :- @Marcoabdu

Last updated 1 month, 1 week ago