ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።
@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna
#ኢትዮጵያ
Last updated 2 months, 3 weeks ago
Last updated 2 months, 2 weeks ago
ይህ ስለ Manchester United መረጃዎችን የሚያገኙበት የ Telegram ቻናል ነው 🇪🇹
--------------------------------------------------------------
☞︎| ስለ ማንቸስተር ዩናይትድ ትኩስ መረጃዎች
☞| ቀጥታ ስርጭቶች ከየስታድየሞቹ
☞| የዝውውር ዜናዎች
☞| ስለ ማንችስተር ዩናይትድ ታሪኮች
📩 ለማስታወቂያ ስራ DM :- @Marcoabdu
Last updated 1 month, 2 weeks ago
| ኢትዮቴሌኮም ከተለያዩ አጋር ተቋማት ጋር ያዘጋጀው ከመገናኛ ቦሌ መንገድ የሚገኝ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች ቻርጅ ማድረጊያ ጣቢያን እያስመረቀ ይገኛል።
ዲጂታል ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ እየተጋ ያለው ተቋሙ ጣቢያዎቹም የእዚህ ጥረት አካል መሆናቸው ተገልጿል።
ኢትዮጵያ የአየር ንብረት ለውጥን ለመግታት እየሰራች ያለችውን ስራ የሚያግዝ ነው የተባለለት የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች ቻርጅ ማድረጊያ ጣቢያው እያደገ ለመጣው የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች ተጠቃሚነት አመቺ ሁኔታዎችን የሚፈጥር ነው።
ተጠቃሚዎች 24/7 አገልግሎቱን ማግኘት የሚችሉ ሲሆን አገልግሎቱን ካገኙ በኋላ ክፍያውን በቴሌ ብር አማካኝነት የሚከፍሉ ይሆናል። የአንድ ኪሎ ዋት ክፍያ አስር ብር ነው።
ሌሎች ተጨማሪ ሁለት ጣቢያዎች በግንባታ ላይ ሲሆኑ በቅርቡ ተጠናቀው ለአገልግሎት ክፍት እንደሚሆኑ ተጠቁሟል።
ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ያሰባሰበውን የሶስት ሚሊዮን ብር ድጋፍ አስረከበ
#Ethiopia | ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ የሩጫ ውድድሮችን ከማዘጋጀት በሻገር የውድድሮቹን ተወዳጅነት በመጠቀም ማህበራዊ ኃላፊነቱን በተለያየ መንገድ እየተወጣ ይገኛል። በተለይም ዓመታዊውን የ10ኪ.ሜ. ዓለም አቀፍ ውድድር በመጠቀም 'ሌሎችን ለመርዳት እሮጣለሁ' በሚል ለተለያዩ አገር በቀል የእርዳታ ድርጅቶች እና ድጋፍ ለሚሹ ወገኖች ሲያሰባስብ ቆይቷል።
በዘንድሮው የ2017 ሶፊ ማልት ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ዓለምአቀፍ 10ኪ.ሜ. ውድድር አማካኝነትም ሶስት (3) ሚሊዮን ብር በማሰባሰብ ለሶስት የተለያዩ ድርጅቶች ድጋፉን አበርክቷል፡፡
እነዚህ ድጋፍ የተደረገላቸው ድርጅቶችም ፡- አዲስ ህይወት አይነ-ስውራን ማዕከል ፣ የአረጋውያን ድጋፍ እና እንክብካቤ ሰጪ የበጎ አድራጎት ድርጅቶች ህብረት እና ቪዥን ማየት የተሳናቸው ህፃናት ወላጆች በጎ አድራጎት ድርጅት ናቸው።
በዛሬው ዕለትም በቪዥን ማየት የተሳናቸው ህፃናት ወላጆች በጎ አድራጎት ድርጅት ማዕከል በመገኘት ለሶስቱም ድርጅቶች በአጠቃላይ የተሰበሰበውን የሶስት ሚሊዮን ብር አስረክቧል።
የኖቤል የኬሚስትሪ ዘርፍ ሽልማት ለሶስት ሳይንቲስቶች በጋራ ተበርክቶላቸዋል።
ለሶስቱ ሳይንቲስቶች ሽልማቱ የተበረከተላቸው ዘርፉ ይበልጥ ገቢራዊ ይሆን ዘንድ ለጣሉት መሰረት ነው ተብሏል።
ሽልማቱን አሜሪካውያኑ ሳይንቲስቶች ካሮሊን በርቶዚ እና ባሪ ሻርፕልስ ከዴንማርካዊው ሞርተን ሜልዳል ጋር የተጋሩት መሆኑን ኤኤፍፒ ዘግቧል።
@MyDataInfo
የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ እና የጤና ሳይንስ ኮሌጅ አካዳሚክ ኮሚሽን በጋራ ባካሄዱት ስብሰባ ተማሪ ቢንያም ኢሳያስ የሕክምና ትምህርቱን እንዲቀጥል ወስነዋል፡፡
የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ጠየና ሳይንስ ኮሌጅ ባወጣው መግለጫ እንዳስታወቀው÷ ተማሪ ቢኒያም ኢሳያስ እስካሁን የተቋረጡ ትምህርቶችን በማካካስ የሕክምና ትምህርቱን ካቆመበት እንዲቀጥል ተወስኗል፡፡
የተማሪ ቢንያም ኢሳያስን ትምህርት በተመለከተ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ጤና ሳይንስ ኮሌጅ እና የሕክምና ትምህርት ቤት ለተማሪው የትምህርት ሂደት ይረዳሉ ያሏቸውን አማራጮችን ቢያቀርቡም ÷ ተማሪ ቢንያም ብቸኛ ፍላጎቱ የሕክምና ትምህርትን መማር እንደሆነ ተገልጿል።
በዚሁም መሠረት የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ እና የጤና ሳይንስ ኮሌጅ አካዳሚክ ኮሚሽን በጋራ ባካሄዱት ስብሰባ ተማሪ ቢንያም ኢሳያስ የሕክምና ትምህርቱን እንዲቀጥል ተወስኗል።
እስካሁን የተቋረጡ ትምህርቶችንም በማካካስ ትምህርቱን ካቆመበት እንዲቀጥል ይደረጋል መባሉን የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ መረጃ ያመላክታል፡፡
ምንም እንኳን የትምህርት ሂደቱ ከባድ እና ውስብስብ ቢሆንም አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ፣ የጤና ሳይንስ ኮሌጅ እና የሕክምና ትምህርት ቤቱ የተማሪ ቢንያምን ትምህርት የተሳካ እንዲሆን የሚችሉትን ሁሉ ድጋፍ እንደሚያደርጉም ተመላክቷል፡፡
ወቅታዊ እና ትኩስ መረጃዎችን ለማግኘት ወደ 6624 Ok ብለው ይላኩ
@MyDataInfo
በአዲስ አበባ ሰሞኑን የወጣው የጋራ መኖሪያ ቤቶች ዕጣ ውደቅ ተደረገ!!
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሐምሌ 1 ቀን 2014 ያወጣው የ20/80 እና 40/60 የጋራ መኖሪያ ቤቶችን ዕጣ ውድቅ አደረገ፡፡
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ በዛሬው ዕለት በሰጡት መግለጫ ባሳለፍነው ሐምሌ 1 ቀን 2014 የወጣው የ20/80 እና 40/60 የጋራ መኖሪያ ቤቶች ዕጣ ውድቅ መደረጉን ተናግረዋል።
ወቅታዊ እና ትኩስ መረጃዎችን ለማግኘት ወደ 6624 Ok ብለው
@MyDataInfo
በዛሬው ዕለት የአሜሪካ የጦር መርከብ ከቻይና መንግስት ፈቃድ ውጪ በደቡብ ቻይና ባሕር በሚገኙ ደሴቶች አካባቢ መግባቱን የቻይና ጦር አስታወቀ፡፡
የቻይና ጦር የደቡብ ዕዝ ቃል አቀባይ ቲያን ጁንሊ በሠጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ÷ በቀጠናው የታየው የአሜሪካ ወታደራዊ እንቅስቃሴ የቻይናን ሉዓላዊነትና የሠላም ፍላጎት የሚጋፋ ነው ብለዋል፡፡
ቲያን ጁንሊ በቻይና ግዛት ውስጥ የተስተዋለው የአሜሪካ የባሕር ጦር እንቅስቃሴ የደቡብ ቻይናን ባሕር ሠላምና መረጋጋት የሚጎዳ፣ ዓለም አቀፍ ህግጋትን እና የዓለም አቀፋዊ ግንኙነቶችን ኅግ የጣሰ ነው ሲሉም በመግለጫቸው ተናግረዋል።
“አሜሪካ በደቡብ ቻይና ባሕር አካባቢ የፈጸመችው ጥሰት የደኅንነት ሥጋት ፈጣሪ እና የአካባቢውን ሠላም እና መረጋጋት አጥፊ መሆኗን ያረጋገጠ ተግባር ነውም” ብለዋል - ቃል አቀባዩ፡፡
የቻይና ጦር የሀገሪቷን ሉዓላዊነት፣ ደኅንነት ፣ ሠላም እና መረጋጋትን ለመጠበቅ ሁልጊዜም በተጠንቀቅ እንደሚገኝ ማስታወቁንም ሲ ጂ ቲ ኤን ዘግቧል፡፡
ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡- ወደ 6624 Ok ብለው ይላኩ
MyDataInfo
በተማሪ ቢኒያም ኢሳያስ ላይ ለደረሰዉ መጉላላት ኃላፊነቱን እንደሚወስድ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የጥቁር አንበሳ ስፔሻላይዝ ሆስፒታል አስታወቀ
በህክምና ትምህርቱን መቀጣል ባይችልም በሶስት የትምህርት ዓይነቶች መማር እንደሚችል ዉሳኔ ተላልፏል
በአዲስ አባባ ዩኒቨርሲቲ የጥቁር አንበሳ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል 5ኛ ዓመት የሕክምና ተማሪ የሆነው ቢኒያም ኢሳያስ በሕክምና ትምህርት ክፍሉ ትምህርቱን ሲከታተል የቆየ ቢሆንም ለመመረቅ 2 ዓመት የማይሞላ ጊዜ ሲቀረው ትምህርቱን እንዲቋርጥ መገደዱን ተማሪ ቢኒያም ኢሳያስ በተለይ ለብስራት ሬዲዮ መናገሩ ይታወሳል፡፡ይህ የሆነው ባለብኝ የአካል ጉዳት ምክንያት ነዉ የሚለዉ ተማሪ ቢኒያም አትችልም ተብሎ ትምህርቱን እንዲያቋርጥ እና ሌላ ትምህርት እንዲጀምር የሚል ዉሳኔ መተላለፉን አስረድቷል፡፡
ተማሪ ቢኒያም ኢሳያስ ያለበትን የአካል ጉዳት ተማሪዎች እና መምህራን ሊገናኙ በማይችሉበት የኮሮና ወቅት ላይ እና ተማሪ ቢኒያም ያለበት የአካል ጉዳት ሊታወቅ የቻለዉ ከህሙማን ጋር በተግባር በተገናኘበት አጋጣሚ መሆኑን በማንሳት ለተፈጠረዉ መጉላላት ሀላፊነቱን እንደሚወስድ በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የጤና ሳይንስ ኮሌጅ ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር አንዱአለም ደነቀ መናገራቸዉን ብስራት ሬዲዮ ሰምቷል፡
የተለያዩ ድጋፎች ለተማሪዉ እየተደረገለት ውሳኔው ከ7 ወር በፊት የጽሁፍ የተሰጠው ቢሆንም ሊቀበል አልቻለም ብለዋል ። የኢትዮጵያ አካል ጉዳተኞች ብሄራዊ ማህበር ደብዳቤ በመላክ ትምህርት ቤቱ ገለልተኛ እንዲሆን ተደርጎ ኮሚቴዎች ተዋቅረው ውሳኔ ሊተላለፍ ችሏል። ተማሪው የህክምና ትምህርት ቤት ከገባበት ጀምሮ ጉዳዩ እስከተከሰተበት ድረስ ያለውን ሁኔታ የሚያጣራ ኮሚቴ ስራውን እንዲሰራ እንዲሁም በሙያው ላይ ሁለት እጅ እንዴት ያስፈልጋል የሚል ወርክሾፕ መካሄዱን ዶ/ር አንዱአለም ደነቀ ተናግረዋል፡፡
ኮሚቴ ያቀረበዉን ምክረ ሃሳብ መነሻ በማድረግ ውሳኔ መተላለፉንም ገልጸዋል:: ትምህርት ቤቱም እነዚህም ምክረ ሃሳቦች እና አለም አቀፍ የህክምና ስምምነቶችን እንዲሁም በ2018 የወጣውን ካሪኩለም በማጣቀስ ባሳለፈዉ ዉሳኔ ተማሪዉ በነርሲንግ ፣በሚድዋይፍ ፣በዴንታል፣ ሜድስን እና መስል ትምህርቶች ላይ ተቀባይነት የማያገኝ ሲሆን በክሊኒካል ፋርማሲ ፣ በራዲዮሎጂ እንዲሁም በላብራቶሪ መቀጠል እንዲችል ውሳኔ ተላልፏል።
በተጨማሪም ተማሪው እስከዛሬ በተማረው ብቻ ዩንቨርስቲው ባችለር ኦፍ ባዮ ሜድኪል ሳይንስ ዲግሪ ሊሰጠው በዝግጅት ላይ ሲሆን ተማሪ ቢኒያም ከተስማማ በቀጣዩ አመት መስከረም ላይ ማስተርስ ኦፍ ፐብሊክ ህልዝ መማር እንዲችል ይደረጋል ሲሉ ዶ/ር አንዱአለም ተናግረዋል ።
የሴቶች እና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር የጥቁር አንበሳ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የህክምና ትምህርት ከፍል በተማሪ ቢኒያም ኢሳያስ ላይ በደረሰዉ መጉላላት ክስ እመሰርታለዉ ማለቱን በሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የአካልጉዳተኞች ጉዳይ ዳይሬክተር አቶ አሳልፈው አህመዲን መናገራቸዉ ይታወሳል፡፡
ለበለጠ መረጃ ወደ 6624Ok ብለው ይላኩ
@MyDataInfo
የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ ሀገር አቀፍ የማስተዋወቂያ መድረክ እየተካሄደ ነው
የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር ያዘጋጀው የተለያዩ በኤሌክትሪክ የሚሰሩ ተሽከርካሪዎችን የማስተዋወቂያ መድረክ በወዳጅነት አደባባይ እየተካሄደ ነው።
በስነ-ስርአቱ ላይ በኤሌክትሪክ የሚሰሩ የተለያዩ ሞዴል ተሽከርካሪዎች ለእይታ ቀርበዋል።
ለበለጠ መረጃ ወደ 6624 Ok ብለው ይላኩ
@myDataInfo
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።
@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna
#ኢትዮጵያ
Last updated 2 months, 3 weeks ago
Last updated 2 months, 2 weeks ago
ይህ ስለ Manchester United መረጃዎችን የሚያገኙበት የ Telegram ቻናል ነው 🇪🇹
--------------------------------------------------------------
☞︎| ስለ ማንቸስተር ዩናይትድ ትኩስ መረጃዎች
☞| ቀጥታ ስርጭቶች ከየስታድየሞቹ
☞| የዝውውር ዜናዎች
☞| ስለ ማንችስተር ዩናይትድ ታሪኮች
📩 ለማስታወቂያ ስራ DM :- @Marcoabdu
Last updated 1 month, 2 weeks ago