ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።
@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna
#ኢትዮጵያ
Last updated 2 months, 3 weeks ago
Last updated 2 months, 2 weeks ago
ይህ ስለ Manchester United መረጃዎችን የሚያገኙበት የ Telegram ቻናል ነው 🇪🇹
--------------------------------------------------------------
☞︎| ስለ ማንቸስተር ዩናይትድ ትኩስ መረጃዎች
☞| ቀጥታ ስርጭቶች ከየስታድየሞቹ
☞| የዝውውር ዜናዎች
☞| ስለ ማንችስተር ዩናይትድ ታሪኮች
📩 ለማስታወቂያ ስራ DM :- @Marcoabdu
Last updated 1 month, 1 week ago
ፓርላማው በመጪው ማክሰኞ በሚያካሄደው አስቸኳይ ስብሰባ፤ የሀገራዊ የምክክር ኮሚሽንን የስራ ዘመን ያራዝማል ተብሎ ይጠበቃል
የሶስት አመት የስራ ዘመኑን እያገባደደ የሚገኘው የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን፤ አጠቃላይ የስራ አፈጻጸም ሪፖርቱን በመጪው ማክሰኞ በሚካሄድ አስቸኳይ የፓርላማ ስብሰባ ላይ ሊያቀርብ ነው።
በዚሁ ስብሰባ ላይ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽኑ “የስራ ዘመን ይራዘማል” ተብሎ እንደሚጠበቅ ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው ምንጮች ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናግረዋል።
በታህሳስ 2014 ዓ.ም የጸደቀው የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን ማቋቋሚያ አዋጅ፤ የኮሚሽኑ የስራ ዘመን ሶስት ዓመት እንደሆነ ይደነግጋል።
የኮሚሽኑ የስራ ዘመን የሚቆጠረው፤ በአዋጁ መሰረት የሚመረጡ ኮሚሽነሮች በፓርላማ ከተሾሙበት ጊዜ ጀምሮ እንደሆነ በድንጋጌው ላይ ሰፍሯል።
የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ለሀገራዊ ምክክር ኮሚሽኑ በዕጩነት የቀረቡ 11 ኮሚሽነሮችን ሹመት ያጸደቀው የካቲት 14፤ 2014 ዓ.ም. ነው።
ፓርላማው ለአንድ ወር እረፍት የተበተኑ አባላቱን ለመጪው ማክሰኞ አስቸኳይ ስብሰባ የጠራው፤ የኮሚሽኑ የስራ ዘመን ድፍን ሶስት ዓመት ከሚሞላበት ዕለት ሁለት ቀናት አስቀድሞ ነው።
የተወካዮች ምክር ቤት ባለፈው ረቡዕ ለአባላቱ ባሰራጨው የስብሰባ ጥሪ፤ ለኮሚሽኑ ጥያቄ ማቅረብ የሚፈልጉ አባላት እስከ ዛሬ ቅዳሜ የካቲት 8፤ 2017 ድረስ እንዲመዘገቡ አሳስቦ ነበር።
🔴 ዝርዝሩን ለማንበብ ➡️ https://ethiopiainsider.com/2025/15089/
ከመተሐራ ከተማ አቅራቢያ በሬክተር ስኬል 6.0 የተለካ የመሬት መንቀጥቀጥ ተከሰተ
ከመተሐራ ከተማ ስድስት ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በሚገኝ አካባቢ ላይ በሬክተር ስኬል 6.0 የደረሰ የመሬት መንቀጥቀጥ መከሰቱን የአሜሪካ የጂኦሎጂካል ሰርቬይ መስሪያ ቤት አስታወቀ። ዛሬ አርብ ምሽት 5ሰዓት ከ28 ደቂቃ ላይ የደረሰው ርዕደ መሬት፤ ባለፈው አንድ ወር ውስጥ ከተመዘገቡት ሁሉ በመጠን ከፍተኛው ነው።
የዛሬው የመሬት መንቀጥቀጥ ያስከተለው ንዝረት “በጣም ጠንካራ” ሆኖ የተሰማው በመተሐራ ከተማ ይሁን እንጂ መዲናይቱን አዲስ አበባን ጨምሮ በርካታ ከተሞችን ማዳረሱን የአሜሪካው የምርምር ተቋም ገልጿል። የርዕደ መሬቱ ንዝረት በአዋሽ ከተማ “መጠነኛ” እንደነበር ያመለከተው ተቋም፤ በአዳማ፣ ሞጆ፣ ቢሾፍቱ እና ደብረ ብርሃን ከተሞችም በተመሳሳይ መጠን መከሰቱን ጠቁሟል።
በመተሐራ እና አዋሽ ከተሞች አቅራቢያ ያሉ አካባቢዎች ባለፉት ወራት የመሬት መንቀጥቀጥ በተደጋጋሚ ሲከስትባቸው የቆዩ ናቸው። በአካባቢዎቹ በመስከረም እና ጥቅምት ወራት ሲከሰት የነበረው የመሬት መንቀጥቀጥ በህዳር ወር ጋብ ያለ ቢመስልም፤ በታህሳስ እና ጥር ወራት በቀን ለበርካታ ጊዜያት ጭምር ሲመዘገብ ቆይቷል።
በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚከሰቱ የመሬት መንቀጥቀጦችን የሚመዘግበው “ቮልካኖ ዲስከቨሪ”፤ ባለፉት ሶስት ወራት ብቻ መጠናቸው በሬክተር ስኬል 4.0 እና ከዚያ በላይ የሆኑ 173 ርዕደ መሬቶች በኢትዮጵያ መከሰታቸውን አስታውቋል። እስከ ዛሬ ምሽቱ ክስተት ድረስ በመጠኑ ከፍተኛ የነበረው የመሬት መንቀጥቀጥ፤ ታህሳስ 26 ለሊት የተከሰተው እና በሬክተር ስኬል 5.8 የተለካው ርዕደ መሬት ነበር። (ኢትዮጵያ ኢንሳይደር)
[በዚህ ዘገባ ላይ ተጨማሪ መረጃ ታክሎበታል]
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ህወሓትን ለሶስት ወራት ከማንኛውም ፖለቲካዊ እንቅስቃሴ አገደ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ፤ ህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) ለሶስት ወራት “በምንም አይነት” ፖለቲካዊ እንቅስቃሴ እንዳይሳተፍ አገደ። በዚህ ጊዜ ውስጥ ህወሓት ጠቅላላ ጉባኤ ለማካሄድ የሚያስችል “የእርምት እርምጃ” ካልወሰደ፤ የፓርቲው ምዘገባ በቀጥታ እንደሚሰረዝ ቦርዱ አስታውቋል።
ብሔራዊው ምርጫ ቦርድ ይህን ያስታወቀው፤ ህወሓትን በተመለከተ ዛሬ ሐሙስ የካቲት 6፤ 2017 ባወጣው መግለጫ ነው። ቦርዱ ለህወሓት ህጋዊ ሰውነት ማረጋገጫ የምስክር ወረቀት “በልዩ ሁኔታ” መስጠቱን የገለጸው፤ በነሐሴ 2016 ዓ.ም. መጀመሪያ ላይ ነበር።
ይህ እርምጃ በጥር 2013 ዓ.ም. በምርጫ ቦርድ አማካኝነት ከፓርቲነት የተሰረዘው ህወሓትን፤ ወደ “ህጋዊ ሰውነት” የመለሰ እንደሆነ በወቅቱ ተገልጾ ነበር። ቦርዱ ህወሓትን ከፓርቲነት ሰርዞ የነበረው፤ “ኃይልን መሠረት ባደረገ የአመጻ ተግባር ላይ መሳተፉን” እንዳረጋገጠ በመጥቀስ ነበር።
ለህወሓት ህጋዊ ሰውነት ማጣት በምክንያትነት ተጠቅሶ የነበረው የሰሜን ኢትዮጵያው ጦርነት፤ በደቡብ አፍሪካ ፕሪቶሪያ በተካሄደ የግጭት ማቆም ስምምነት በጥቅምት 2015 ዓ.ም. መቋጨቱ ይታወሳል።
ስምምነቱን ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር የተፈራረመው ህወሓት፤ ህጋዊ ሰውነቱ እንዲመለስ ለቦርዱ ያቀረበው ጥያቄ “በህግ የተደገፈ አይደለም” በሚል ውድቅ ተደርጎ ነበር።
🔴 ለዝርዝሩ:- https://ethiopiainsider.com/2025/15059/
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።
@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna
#ኢትዮጵያ
Last updated 2 months, 3 weeks ago
Last updated 2 months, 2 weeks ago
ይህ ስለ Manchester United መረጃዎችን የሚያገኙበት የ Telegram ቻናል ነው 🇪🇹
--------------------------------------------------------------
☞︎| ስለ ማንቸስተር ዩናይትድ ትኩስ መረጃዎች
☞| ቀጥታ ስርጭቶች ከየስታድየሞቹ
☞| የዝውውር ዜናዎች
☞| ስለ ማንችስተር ዩናይትድ ታሪኮች
📩 ለማስታወቂያ ስራ DM :- @Marcoabdu
Last updated 1 month, 1 week ago