ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።
@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna
#ኢትዮጵያ
Last updated 4 months, 1 week ago
Last updated 4 months ago
ይህ ስለ Manchester United መረጃዎችን የሚያገኙበት የ Telegram ቻናል ነው 🇪🇹
--------------------------------------------------------------
☞︎| ስለ ማንቸስተር ዩናይትድ ትኩስ መረጃዎች
☞| ቀጥታ ስርጭቶች ከየስታድየሞቹ
☞| የዝውውር ዜናዎች
☞| ስለ ማንችስተር ዩናይትድ ታሪኮች
📩 ለማስታወቂያ ስራ DM :- @Marcoabdu
Last updated 3 months ago
እንኳን ለኪዳነ ምሕረት በዓል በሰላም አደረሳችሁ አደረሰን።
አንቲ ውእቱ ተስፋሁ ለአዳም አመ ይሰደድ እምገነት።
ከገነት በተሰደደ ጊዜ የአዳም ተስፋው አንቺ ነሽ።
አምና በዜህ ሰዓት አዳም በስደቱ ምክንያት የደረሰበትን ኀዘንና የተጽናናበትን ተስፋውን እያሰብን በዓሉን አክብረን ነበር።
ዘንድሮ ግን በታሪክ የሰማንው ስደት በእኛ ላይ ደርሶ የእውቀት አምባችን፣ የጥበብ መፍለቂያችን፣ መማሪያችን፣ መኖሪያችን፣ ተስፋችን፣ ታሪካችን፣ ቅርሳችንና ማንነታችን የሆነሆው መታሰቢያ ቤት ፈርሶ ደሀ አደግና ቧጋች ሆንን።
ቤቷ ፈርሶ ማረፊያ እንደ አጣች ወፍ ከቦታ ቦታ እየተቅበዘበዝን ነው በዓሉን እያከበርን ያለንው።
ስደት እንዴት ክፉና መራራ ነው? የነበረንን ማጣትስ እንደምን ያለ የሰብእና ስበራት ነው?
ድንግል ሆይ!!! ለአባታችን አዳም የኀዘኑ መርሻ፣ የርስቱ ማስመለሻ ተስፋው እንደሆንሽው ኹሉ ለእኛም ተስፋ ኹኚልን፤
ርስታችንን እናስመልስ ዘንድ ኀይል ብርታት ሆነሽ ከፈጣሪያችን አማልደሽ ጠላቶቻችን አድክመሽ ወደ ጥንት ቦታችን እንድንመለስ እርጅን።
አሜን።
አምና በዜህ ወርና ዕለት አስብና አቅድ የነበረው፣
የቅዳሴ ተማሪዎቼ እንዴት በርትተውና ተግተው መማር እንዳለባቸው ነበር የማስበውና እየሰራሁ የነበረው እንጂ በዓመቱ በዜህ ወር የቆምሁበት መሬት ተንዶ የማድርበት ቤት ፈርሶ የማስተምርበት ክፍል አቧሯ ለብሶ ድሀ አደግ ተቅበዝባዥ እሆናለሁ ብዬ ፈጽሞ አላሰብሁም ነበር፤ ግን ሆነ።
ጊዜ ነው እንጂ ቁም ነገራም
የሰው ልጅነት አያኮራም።
እንደሚባለው።
ኹሉም የየራሱን ሲማር የሚሰማ ድምፅ ነው።
ሳይፈርስ ይኽ ነበር።
ምንም ዕንኳ ፍትሕን ማጣት አሳዛኝና አስከፊ ቢሆንም፤ ከጠላትህ ፍትሕን መለመን ግን የበለጠ ያማል።
ግን ምን ይደረግ?
እያለው የሌለው ሕዝብ እንዲህ ነው።
የቱንም ያኽል ብዙ ብትሆን በአግባቡ ተደራጅተህ መብትህን ማስከበር ካልቻልህ የጥቂቶች መዘባበቻ ትሆናለህ።
ልክ እንደእኛ።
ኹሉም ነገር ተፈጸመ።
ዛሬ ታኅሣሥ 22 ቀን 2017 ዓ.ም የ92 ዓመተ ምሕረቱ አንጋፋው የዳግማዊ ምኒልክ መታሰቢያ መንፈሳዊ ትምህርት ቤት በዕለተ ሠሉስ በሦስት ሰዓት ማፍረስ ተጀመረ።
በውስጡ ያሉት ካህናት፣ አዳሪ ተማሪዎች፣ ጡረተኞች፣ መምህራንና ልዩ ልዩ በገዳሙ ውስጥ ነዋሪ የሆንን ኹሉ አንዳችም ማረፊያ ሳይሰጠን ነው ገዳሙ እየፈረሰ ያለው።
እኔም አዘጋጅቼ የነበረውን አስፈላጊ የሆኑ መጻሕፍቶቼን ብቻ ይዤ ለዐርባ ዓመት የኖርሁበትን፣ የተማርሁበትንና ያስተማርሁበትን ቦታ ለአፍራሹ ቡድን ትቼ ወደ ዘመድ ቤት ተጠጋሁ።
ይኽን አንጋፋና እድሜ ጠገብ፣ የመንፈሳዊ ትምህርት ኹሉ ማእከል የሆነ ተቋቋም እነሆ ሲፈርስ ዐይኖቼ አዩ።
ምን ማድረግ እችላለሁ?
ነገም ሌላ ቀን ነው።
ዛሬ ታኅሣሥ 17 ቀን 2017 ዓ.ም ነው፤ እንደ ሌላው ቀን ቢሆን ኖሮ በዚህ ሰዓት ጉባኤ ዘርግተን ትምህርት ላይ ነበር።
አሁን ግን ጉባኤ አጥፈን ትምህርት ዘግተን የዘጠና ዓመቱን አንጋፋ የዳግማዊ ምኒልክ መታሰቢያ መንፈሳዊ ትምህርት ቤታችን በልማት ሰበብ እንዲፈርስ ስለተወሰነብን እቃችንን እያዘጋጀን እንገኛለን።
ለማን አቤት ይባላል?
ጉባኤ አጥፎ፣ ማስተማርን ትቶ፣ ተፈናቃይ መሆን ምንኛ ያማል?
ስሳ ወይም ሰባ ሚሊየን አማኝ ሕዝበ ክርስቲያን ያላት ቤተ ክርስቲያን በመቶ የሚቆጠሩ አባቶች ጳጳሳት ያላት ቤተ ክርስቲያን እንዴት ለምን? ብሎ የሚጠይቅ አባት አጣች?
አሳዛኝ ነው።
ለማኛውም ዕቃዬን ላዘጋጅ።
ይኽ የአንቀጸ ቅዳሴ መጽሐፍ የአንቀጹን ዜማ ታርሞና ተስተካክሎ ከመያዙ በላይ የቅዳሴ ስረዮችን የዜማና የንባብ ጠባይ ጠንቅቆ የያዘ በመሆኑ ለመማር፣ለማስተማርና በጥልቀት ለማወቅ በእጅጉ ይረዳል፤
ስለዜህ መጽሐፉ ሊኖርዎ ይገባል።
ከዜህ ቀደም በዜህ መልኩ ታትሞ አያውቅምና፤
መጽሐፉን ከፈለጉ 0911691953 ብለው ይደውሉ።
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።
@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna
#ኢትዮጵያ
Last updated 4 months, 1 week ago
Last updated 4 months ago
ይህ ስለ Manchester United መረጃዎችን የሚያገኙበት የ Telegram ቻናል ነው 🇪🇹
--------------------------------------------------------------
☞︎| ስለ ማንቸስተር ዩናይትድ ትኩስ መረጃዎች
☞| ቀጥታ ስርጭቶች ከየስታድየሞቹ
☞| የዝውውር ዜናዎች
☞| ስለ ማንችስተር ዩናይትድ ታሪኮች
📩 ለማስታወቂያ ስራ DM :- @Marcoabdu
Last updated 3 months ago