ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።
@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna
#ኢትዮጵያ
Last updated 2 months, 3 weeks ago
Last updated 2 months, 2 weeks ago
ይህ ስለ Manchester United መረጃዎችን የሚያገኙበት የ Telegram ቻናል ነው 🇪🇹
--------------------------------------------------------------
☞︎| ስለ ማንቸስተር ዩናይትድ ትኩስ መረጃዎች
☞| ቀጥታ ስርጭቶች ከየስታድየሞቹ
☞| የዝውውር ዜናዎች
☞| ስለ ማንችስተር ዩናይትድ ታሪኮች
📩 ለማስታወቂያ ስራ DM :- @Marcoabdu
Last updated 1 month, 1 week ago
የጥንቃቄ መረጃ‼
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
ከነገ ጀምሮ ከቡሬ እስከ አዲስ ቅዳም ባሉ ከተሞች ወጣቱን በማፈስ በግዴታ ወደመከላከያ ካምፕ እንደሚጭኑት ታውቋል ።
በመሆኑም ቡሬ ቲሊሊ ኮሶበርና አዲስ ቅዳም ያላችሁ ወጣቶች ብትችሉ ወደ አካባቢያቹህ ፋኖ ተቀላቀሉና ሰልጥኑ ካልቻላቹህም ወደ ፑልና ከረንቡላ ቤቶች አታዘጥዝጡ መልዕክታችን ነው።
የካቲት 07/2017ዓ.ም
ቢዛሞ ሚዲያ
መረጃ ጎጃም‼****
፨፨፨፨፨፨፨፨
በዛሬው ዕለት ጎጃም የጨረቃ ላይ አራት የመከላከያ አባላት ከነሙሉ ትጥቃቸው በአካባቢው የሚንቀሳቀሰውን የአማራ ፋኖ በጎጃም ቀኝ ጌታ ዮፍታሄ ንጉሴ የ6ኛ ክ/ጦር ኢንጂነር ክበር ተመስገን ብርጌድን ተቀላቅለዋል‼
ስቦ ማስከዳትና ስቦ መምታት ተጠናክሮ ይቀጥላል💪****
የካቲት 07/2017ዓ.ም
ቢዛሞ ሚዲያ
<<ከተላላኪ ባንዳ የፀዳ ትግል ለመፍጠርና ጠንካራ መሪ ለመባል>>
®የአማራ ህዝብ በአብይ አህመድ"የ666"ሰይጣናዊ ተግባር እየተሰራበት ያለው የጥፋት ሴራ ከባድ ከመሆኑ ባሻገር እጅግ አሳዛኝ ሆኖ ይስተዋላል፡ለዚህ ደግሞ ትልቁ መፍትሔ በክፍለ ጦሩ የተዋቀረ በሳል አመለካከት፣በብርጌዱ የተዘጋጀ ጠንካራ አካሄድ፣በሻለቃዎች የተደራጀ ብርቱ ጥምረት፣በፋኖ ሀይሎች የተሰራ ጠበብት የአቋም ምልከታ መሆኑን በመረዳትና በመገንዘብ፦
👉የፋኖ ሀይሉን ስለ አማራ ትግል ምንነት የግንዛቤ ት/ት መስጠት ያስፈልጋል፡
👉በየቀጠናው ጠንካራና በሳል መሪ ከመፍጠር ባሻገር እርስ በእርሱ በስምምነት የተዋቀረ ሻለቃ መፍጠር ይገባል፡
👉በየቀጠናው የሚገኙ የፋኖ ሀይሎች ወታደራዊ ብቃትና ወታደራዊ ቁመና በመዘጋጀት ሁሌም በተጠንቀቅ መቆም እንዳለባቸው እለት እለት የአካሄድ ስምሪት ስልጠና መሰጠት አለበት፡
👉በእውነትና በሀቀኝነት ላይ የተመሰረተ ጠንካራ የፋኖ መረጃ ሰጭ በገጠርና በወረዳ ከተሞች ላይ ስውር መረጃና ደህንነት ማቋቋም ይገባል፡
👉ከውጊያ በፊት ከተላላኪ ቅጥረኛ ባንዳ የፀዳ ጥርነፋ ማዋቀር፤ከጠላት ሀይል ጋር የጥቅማጥቅም፣የዘመድ አዝማድ ትስስር ያደርጋሉ ተብለው የሚጠረጠሩ ሰርጎ ገቦችን በአይን ቁራኛ መከታተል ከውጊያ በኋላ ደግሞ የጦርነቱን አካሄድ፣ወታደራዊ አሰላለፉን በጠንካራና በደካማ ጎን ገምግሞ ደካማውን ማስተካከል ጠንካራውን ማስቀጠል የሚችል አቋም ማዘጋጀት፡
👉የጠላት ሀይል በሚንቀሳቀስባቸው አካባቢዎች ጠንካራና በጥበብ የተሞላ ስምሪት መንደፍ፡
👉ለትግሉ ይመጥናሉ ያሟላሉ የሚባሉ የአማራ ፋኖ ሀይሎችን በሀሳብና በስነ-ልቦና ድጋፍ የታገዘ ስራዊት ማነፅ፣በየቀጠናውም ጠንካራ ዋርድያ ማቋቋም ያስፈልጋል፡
👉ትግሉን ይጠልፋሉ፣ትግሉን በገንዘብ ይሸጣሉ፣ትግሉን በዘመድ አዝማድ በአጓጉል ሱስ ይለውጣሉ የሚባሉ ተጠርጣሪ ግለሰቦችን አጥብቆ መቆጣጠርና በእርግጠኝነት ሲያዙ እርምጃ መውሰድ ያስፈልጋል፡
👉ትግሉን እንደ መደበቂያነት ከመቆጠር ነፃ የወጣ፤ለእውነት የቆመ ጠንካራ ወታደራዊ አሰላለፍ ነፃ አውጭ ዘመን አሻጋሪ ስራዊት መገንባት ይገባል፡
👉ከክፍለ ጦር፣ከብርጌድ፣ከሻለቃዎች፣ከፋኖ ሀይሎችና ከህዝብ ጋር ስምምነት መፍጠር የሚችል በሳልና ጠንካራ ስራዊት ማቋቋምና ማደራጀት ያስፈልጋል፡
*👉*ግልባጭ፦ለክፍለ ጦር አመራሮች፣ለብርጌድ አመራሮች፣ለሻለቃ መሪዎች፣ለፋኖ መረጃና ደህንነት፣በክፍለ ጦሩ ውስጥ ለምትገኙ የፋኖ ሀይሎች፣ለውስጥ የአማራ ፋኖ የትግል ደጋፊዎች፣ለውስጥ የመረጃ ምንጮቻችን፣ለመረጃ አዘጋጁ፡:
የካቲት 07/2017 ዓ ም
ቢዛሞ ሚዲያ**
ሞቅ ሞቅ አድርጉት ግዙፉን የሀገሪቱን ማስልጠኛ ተቋምኮ ነው የተቆጣጠርነው???????????
ብርሸለቆ መኮድ ታሪክ ተሰርቷል????
ሰከላ‼️
በአሁኑ ሰዓት መከላከያ እየተንቀሳቀሰ ስለሆነ ጥንቃቄ አድርጉ።
አሁን አምቢሲ አካባቢ እየደረሱ ነው።
በአስገዳጅ ብሔራዊ ውትድርና ስም በሚደረግ ጭፍጨፋ እና በኢትዮጵያዊያን ወጣቶች ደም የሚፀና ስልጣን አይኖርም!!!
አፋጎ (AFG)
`````````````
የውድቀት አፋፍ ላይ የሚገኘው የብልጽግናው አገዛዝ በአማራ ክልል በተለያዩ አካባቢዎች በከተሞች የሚገኙ የቀን ሰራተኞችን፣ የትምህርት ገበታ ላይ የተቀመጡ ህጻናትን፣ አስተማሪዎቻቸውንና የመንግስት ሰራተኞችን የፋኖ ደጋፊ ናችሁ በሚል ሰበብ በገፍ እያፈሰ የተሀድሶ ስልጠና በሚል ያዘጋጀውን ማደናገሪያ በመጠቀም አስገድዶ ወደ ማጎሪያ ካምፖች ሲያግዝ የቆያቸውን ወጣቶች ወደ ወታደራዊ ማሰልጠኛ ተቋማት በማጓጓዝ ላይ ነው።
ከአማራ ክልል እያፈሰ ወደ አልታወቀ ቦታ የሚወስዳቸውን ወጣቶች በርሃብ፣ በበሽታና በድብደባ አለፍ ሲልም ሰበብ እየፈጠረ በመረሸን እንደሚያጠፋቸው የታወቀ ነው። ለዚህም በአማራው ህዝብ ላይ ይፋዊ ጦርነት ከጀመረበት ጊዜ አንስቶ በጀግናው የአማራ ፋኖ ሃይል በተደመሰሰ ቁጥር በመኖሪያ ቤታቸው፣ በአደባባይ ቦታዎችና በቤተ እምነቶች የሚማሩ የአብነት ተማሪዎችን፣ ህፃናትና አረጋውያንን አማራ በመሆናቸው ብቻ በጅምላ ሲረሽን መክረሙ በቂ ማሳያ ነው። ሰሞነኛው የአብይ አህመድ አፈሳም የጀርመኑ ናዚ በአይሁዳውያን ላይ ሲፈፅመው እንደነበረው የኦሺዊትዝ የእገታ ማዕከል የሚታይ አማራን ወጣት አልባ ህዝብ በማድረግ ለማጥፋት የሚደረግ አፈሳና እመቃ በመሆኑ የተለመደ የውትድርና አፈሳ ነው ብሎ መዘናጋት በራስ ላይ ሞት እንደማወጅ ያለ ነው።
ኢትዮጵያዊያን ወጣቶችን ሁሉ የስልጣን ማስጥበቂያ ዕቃዎች እንደሆኑ አድርጎ የሚቆጥረው ይህ አገዛዝ ይህንን የአፈሳ ተግባሩን እንደ አማራ ክልሉ ሁሉ በተለያዩ የኢትዮጵያ አካባቢዎች ያለምንም ሃፍረት በማናለብኝነት እያከናወነ ይገኛል። ይህ የአገዛዙ ተግባር የሃገሪቱን አምራች ዜጎች በጅምላ በመጨፍጨፍና ወደ ወታደራዊ ካምፕ በማጋዝ እርስ በእርስ በማጫረስ ወጣት አልባ ሃገር ለመፍጠር አረመኒያዊ ተግባር እየፈፀመ መሆኑን በግልፅ ያሳየበት ነው።
ከኦሮሚያ አካባቢ የሚያፍሳቸውን ወጣቶች በዘረኝነትና በፀረ አማራነት እየቀሰቀሰ "የኦሮሞ መንግስት ነው፤ መንግስታችሁን ከመውደቅ አድኑት" እያለ አገሪቱን ወደ ባሰ የእርስ በርስ ጦርነት ለማስገባት ቆርጦ መነሳቱንና የወጣቶችን አዕምሮ እየበረዘ በማታለል ማሰለፍ ያልቻለው ብልፅግና በግድ እና በሽብር የሃሰት የግድያ ፈጠራዎችን አቀናብሮ ቪዲዮ በማሳየት፣ በካድሬዎቹ በኩል የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችን በግድ ሰልፍ በማስወጣት ሽብርና ግርግር በመፍጠር የኦሮሞን ህዝብ ጭምር እረፍት እየነሳ ይገኛል።
ስለሆነም-
ሰሞነኛው አፈሳ አስገዳጅ ብሄራዊ ውትድርና ሳይሆን አማራን በአንድ ላይ ማመቅና ሲስተማቲክ በሆነ መልኩ በተለያዩ ስልቶች ወጣት አልባ ለማድረግ ያለመ መሆኑን ተረድቶ መላው የአማራ ህዝብ የአገዛዙን ህገ ወጥ ድርጊት ተቃውሞ እንዲቆም፣ በተለይ ወጣቱ ጨርቄን ማቄን ሳይል በየአካባቢው በሚገኘው የፋኖ አደረጃጀት ውስጥ በመካተት ራሱንና ህዝቡን ከጥፋት እንዲያድን ጥሪ እናቀርባለን።
የደርግ ዘመን ብሄራዊ ውትድርና ማንኛውም ዕድሜና ጤናው የሚፈቅድለት ዜጋ አገሩን በውትድርና የማገልገል ግዴታ አለበት በሚል በአዋጅ የተደገፈ ነበር። ይሁንና ከመብት አኳያ ያለ ግለሰቦች ይሁንታ የሚፈፀም ትክክል ያልሆነ ተግባር ቢሆንም በይፋ የታወቀና ሌላ የተለየ ሥጋት የሚፈጥር አልነበረም። የደርግ ብሄራዊ ውትድርና ተቀባይነት ስላልነበረው ውጤት ማምጣት አልቻለም። ይልቁንም ውድቀቱን እንዳፋጠነው የቅርብ ታሪካችን ነው። "በፊት የበቀለውን ጀሮ በኋላ የበቀለው ቀንድ በለጠው" እንዲሉ የብልፅግናው አገዛዝ ከደርግ ዘመን በከፋ ሁኔታ ወጣቶችን በጅምላ እያፈሱ ወደ ወታደራዊ ካምፖች እያስገባ ነው። ድርጊቱም የኢትዮጵያን ዳር ድንበር ለመጠበቅ ሳይሆን ኢትዮጵያውያንን እርስ በእርስ ለማጫረስ ያለመ በመሆኑ ሁሉም ኢትዮጵያውያን ይህንን የአገዛዙን ሴራ ተረድቶ በጋራ በመቆም ድርጊቱን እንዲያወግዝ ጥሪ እናቀርባለን።
በኦሮሚያና በደቡብ የሀገራችን አካባቢዎች የምትገኘ ኢትዮጵያውያን አፈሳው አብይ አህመድን ስልጣኑን ለማስጠበቅ የሚፈፅመው አረመኒያዊ ተግባር እንጅ ጠንካራ የመከላከያ ኃይል በመፍጠር የኢትዮጵያን ዳር ድንበር ለማስጠበቅ በማሰብ አለመሆኑን ተገንዝባችሁ በአማራ ህዝብ ላይ ለከፈተው ጦርነት ተባባሪ እንዳትሆኑ፣ ልጆቻችሁንም እንዳታስጨርሱ ይልቁንም ከአማራ ህዝብ ጎን እንድትቆሙ ጥሪ እናቀርባለን።
ዓለምአቀፉ ማህበረሰብና የሰብአዊ መብት ድርጅቶች ይህን ይፋ የሆነ ህገ ወጥ ድርጊት እንዲያወግዝና ከህዝባችን ጎን እንዲቆም ጥሪ እናቀርባለን።
ፎቶው:- በዘመቻ መቶ ተራሮች እጅ የሰጡ ምርኮኞችን ለአንድ ዓለም አቀፍ ጋዜጠኛ ስናስጎበኝ የተወሰደ ነው።
አስረስ ማረ ዳምጤ
የግልባጭ ትርጉም‼****
በጦር እያመሰ ሰላም ነው ማለቱ፣
ድህነት ገብቶብን እድገት ነው ማለቱ ፣
ይህ ነው ማይገናኝ ትርጉም መምታታቱ።
ደመወዝን በስልት ቀንሶ በግማሽ ፣
ጨመርኩልሽ ይላል ህዝቤ ሆይ ሲያሞኝሽ ፣
ገነባሁሽ ይላል ሀገሬ ሲያፈርስሽ።
የሰው ቤቱ ፈርሶ ወጥቶ ጎዳና፣
የግልባጭ ትርጉም ይህ ነው ብልፅግና።
ቤት ፈርሶ መዝናኛ ሆድ ተርቦ ውበት፣
ይህ ነው ብልፅግና ይህ ነው የሀገር እድገት።
ሰው ከሰውነቱ ከክብሩ ተዋርዶ፣
በቀለም ዘርፍ ስንጥቅ በብሔር ተቀዶ፣
ፍቅር ተሸርሽሮ አንድነት ተንዶ፣
ይህ ነው ...
የግልባጭ ትርጉም ደስታ መሳይ መርዶ።
ታሪክን አጥፍቶ ትርክትን ፈጣሪ ፣
የእድገት መንገድ ብሎ ተንኮልን ቀማሪ፣
በፊደላት ፋንታ ብሔር አስቆጣሪ፣
ይህ ነው...
የግልባጭ ትርጉም የመርዶ ዱብዳ ደስታ ብሎ አብሳሪ።
ወደ ጥልቁ ስንወርድ በላያችን ጭነን የዘመናት መርገም ፣
ሀገር እድገት ላይነች ፈጥረናል ይለናል ፍፁማዊ ሰላም።
ከአለም ፍጥረታት የሰው ልጅ ክብሩ አንሶ ፣
በመደመር ስሌት ሰውን በመሳሪያ በመግደል ተቀንሶ፣
የመዋኛ ገንዳ መዝናኛ ይለናል መቃብርን ምሶ።
ሀገር ስትመራ ፊደላት ባለዬ በእኔ አውቃለሁኝ ባይ ፣
ህዝብ ሲስተዳደር በአሸባሪ ቡድን በንፁሀን ገዳይ ፣
አያገባችሁም አታውቁም ስንባል በሀገራችን ጉዳይ።
ገነት መሳይ ሲኦል ሲገነባ ሲሰራ ገሀነም፣
ታድያ ይሄ እኮ ነው ፍፁም ማይገናኝ የግልባጭ ትርጉም።
አስቼኳይ መረጃ‼****
አመሻሹን ጨለማን ተገን በማድረግ ብዛት ያለው የአገዛዙ ጥምር ጦር ከአድስ ቅዳም ከተማ ወደ ፋግታ አቅጣጫ መንቀሳቀሱን የአይን እማኞች አረጋግጠውልናል። ፋግታዎች የኤፍሬም አጥናፉ ፍሬዎች ጥንቃቄ አይለያቹህ ስንል እናሳስባለን‼
መረጃ‼️
ከባህርዳር የተነሳ አራዊት ሠራዊት በጥዋቱ 12:43amወደ ጎንደር ? አቅጣጫ ወጧል 1ዙ 23 ሌሎች በካሱኔ የተጫኑ ናቸው በ 5መኪና ፍጥነት አላቸው እስኪ share አድርጉት እንደ ተለመደው በስልክም አድርሱ‼️
#የአማራ ድምፅ ሚዲያ
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።
@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna
#ኢትዮጵያ
Last updated 2 months, 3 weeks ago
Last updated 2 months, 2 weeks ago
ይህ ስለ Manchester United መረጃዎችን የሚያገኙበት የ Telegram ቻናል ነው 🇪🇹
--------------------------------------------------------------
☞︎| ስለ ማንቸስተር ዩናይትድ ትኩስ መረጃዎች
☞| ቀጥታ ስርጭቶች ከየስታድየሞቹ
☞| የዝውውር ዜናዎች
☞| ስለ ማንችስተር ዩናይትድ ታሪኮች
📩 ለማስታወቂያ ስራ DM :- @Marcoabdu
Last updated 1 month, 1 week ago