ᴇʟɪᴀꜱ ᴍᴇꜱᴇʀᴇᴛ

Description
Journalist-at-large
We recommend to visit

ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ

Last updated 4 months, 2 weeks ago

Last updated 4 months, 2 weeks ago

ይህ ስለ Manchester United መረጃዎችን የሚያገኙበት የ Telegram ቻናል ነው 🇪🇹
--------------------------------------------------------------
☞︎| ስለ ማንቸስተር ዩናይትድ ትኩስ መረጃዎች
☞| ቀጥታ ስርጭቶች ከየስታድየሞቹ
☞| የዝውውር ዜናዎች
☞| ስለ ማንችስተር ዩናይትድ ታሪኮች

📩 ለማስታወቂያ ስራ DM :- @Marcoabdu

Last updated 3 months, 1 week ago

hace 2 meses, 2 semanas
[#FakeNewsAlert](?q=%23FakeNewsAlert) አልጀዚራ እንደዚህ ብሎ አልዘገበም፣ የቀድሞው …

#FakeNewsAlert አልጀዚራ እንደዚህ ብሎ አልዘገበም፣ የቀድሞው ፕሬዝዳንት የአቶ ሙላቱ ተሾመን አስተያየት ግን ዛሬ አቅርቧል

ሊንክ: https://www.aljazeera.com/opinions/2025/2/17/to-avoid-another-conflict-in-the-horn-of-africa-now-is-the-time-to-act

- 'እርቅ' የተባለው ነገር ሲመጣ ኤርትራ ሀገሯ እንዳልገባ ከዛ ሁሉ ሚድያ ለይታ አገደችኝ፣

- የእኛው መንግስት ደግሞ ኤርትራን ጋብዞ የትግራይን ህዝብ ሲያስፈጅ እና ዜና ስሰራ 'ውሸት ነው፣ የኤርትራ ሀይል አልሀገባም፣ ሀገር ለማተራመስ የባንዳ ስራ ነው' ብሎ ፈረጀኝ

Now this!

@EliasMeseret

hace 2 meses, 2 semanas
እስከዛሬ የሚፅፉት እና የሚናገሩት ስለኢትዮጵያ መስሎኝ …

እስከዛሬ የሚፅፉት እና የሚናገሩት ስለኢትዮጵያ መስሎኝ የሰጠሁት አስተያየት ቆጨኝ

ለካ ስለሌላ ሀገር ነው 🤔

@EliasMeseret

hace 2 meses, 3 semanas
መቼም በአጥር ሾልካ ገብታ ወይም በፓራሹት …

መቼም በአጥር ሾልካ ገብታ ወይም በፓራሹት ወርዳ አይሆንም፣

ይህ እንደ አንድ ተራ ክስተት ብቻ ሊወሰድ አይገባም፣ አመራሩ ሳያውቅ እንዲህ አይነት ድርጊት በሀላል የሚፈፀም ከሆነ የኤርፖርቱ ግቢ ደህንነት ምን ያህል አስተማማኝ ነው የሚል ጥያቄንም ያጭራል።

@EliasMeseret

hace 4 meses, 1 semana
በሲዳማ ክልል በቦና ዙሪያ ወረዳ በደረሰ …

በሲዳማ ክልል በቦና ዙሪያ ወረዳ በደረሰ የትራፊክ አደጋ ህይወታቸውን ያጡ ወገኖቻችን ቁጥር 71 መድረሱ ታውቋል

እጅግ ያሳዝናል፣ ነፍስ ይማር!

@EliasMeseret

hace 4 meses, 1 semana
በአዲስ አበባ ከተማ የመንገድ ዳር አበባ …

በአዲስ አበባ ከተማ የመንገድ ዳር አበባ እና ሳር ለማጠጣት የሚውለው የመጠጥ ውሀ በመሆኑ ህዝቡ መቸገሩ ታወቀ

(መሠረት ሚድያ)- በአዲስ አበባ ከተማ በተለይ በቅርብ ግዜያት ከተሰሩ የኮሪደር ልማቶች ጋር ተያይዞ ለተተከሉ የመንገድ ዳር አትክልትና ሳር ለማጠጣት የሚውለው ውሀ ለነዋሪዎች መጠጥ ከሚያገለግል የውሀ መስመር በመሆኑ ህዝቡ ውሀ መቸገሩ ታወቀ።

ተጨማሪ ያንብቡ: https://t.me/meseretmedia/736

Via @MeseretMedia
@EliasMeseret

hace 4 meses, 2 semanas
የተባበሩት መንግስታት ድርጅትን ጨምሮ መንግስት ራሱ …

የተባበሩት መንግስታት ድርጅትን ጨምሮ መንግስት ራሱ በምንጭነት የሚጠቅሳቸው ተቋማት ደግሞ ከ120 ሚልዮን ህዝባችን ውስጥ 86 ሚልዮኑ በድህነት ውስጥ እንደሚገኝ እየነገሩን ነው

የህዝቡን ምሬት፣ እሮሮ እና ስቃይ ደግሞ እለት ከእለት በግልፅ እያየነው ነው። ኢኮኖሚያችንን ፕላን የሚያረጉልን ደግሞ ስሌታቸው ስክሪንሾቱ ላይ ያለውን እያሳያቸው ነው።

ችግር ሲያጋጥም ጭንቅላትን ብቻ ለይቶ አሸዋ ውስጥ መቅበር ማለት ይህ ነው። 

@EliasMeseret

hace 4 meses, 2 semanas

Journalism is not just about speaking to those in power; it is about speaking truth to power ✊️

#Journalism

@EliasMeseret

hace 4 meses, 2 semanas
Thank you, America!

Thank you, America!

የእነዛ በርሀብ የተጎዱ ምስኪን ህፃናት ምስል ከአእምሮ አይጠፋም።

https://t.me/meseretmedia/731

hace 4 meses, 2 semanas
ᴇʟɪᴀꜱ ᴍᴇꜱᴇʀᴇᴛ
hace 7 meses, 1 semana

የሰሞኑን የብር መዳከምን (የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያውን) ተከትሎ ገበያ ላይ ያልጨመረ ነገር የለም ቢባል ማጋነን አይሆንም

ይህ አልበቃ ብሎ የመንግስት ተቋማት ህዝብ ላይ እልህ እየተወጡ ይመስል ተራ በተራ እስከ 700 ፐርሰንት ጭማሪ ያረጉ አሉ።

ኢሚግሬሽን፣ ንግድ ባንክ፣ ኤሌክትሪክ፣ ውሀ፣ ቴሌ፣ አየር መንገድ፣ የመኪና ቦሎ እና መንጃ ፈቃድ፣ የትራፊክ ቅጣት... ከሰሞኑ ደግሞ የዳኝነት ክፍያ እንኳን ጭማሪ ይደረግበታል። የኔ ጥያቄ:

አንደኛ፣ ጭማሪ ሲደረግ ነባራዊ የህዝብን አቅም እና ችግር ማገናዘብ የለበትም ወይ?

ሁለተኛ፣ በሌላው አለም እንደምናየው progressive የሆነ የ10%፣ የ20%... ወዘተ እያለ ጭማሪ ይደረጋል እንጂ ሲፈልግ የ150%፣ ሲያሻው የ700% ጭማሪ ማድረግ ማለት ነው?

ሶስተኛ ደግሞ አንድ ሰሞን ሲወራ የነበረውን ጥቂት የሆነ የደሞዝ ጭማሪ እንኳን ተግባራዊ ሳያደርጉ ህዝብ ላይ ሸክም መጫን ለምን ተፈልጎ ይሆን?

እውነት ይሄ ነገር አንድ ወዳጄ እንዳለኝ "መንግስት ከህዝብ ጋር እልህ ተጋብቶ እየቀጣው ነው" ያለው እውነት ይሆን እንዴ?

ዝመት ሲባል ዘምቶ ለሚቆም፣ ደግፍ ሲባል በሚሊዮኖች ወጥቶ ለሚሰለፍ፣ ሀገርህ ተደፈረ ሲባል "ኢትዮጵያን!" ብሎ ለሚዘምት ግን ይህ አይገባውም።

@EliasMeseret

We recommend to visit

ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ

Last updated 4 months, 2 weeks ago

Last updated 4 months, 2 weeks ago

ይህ ስለ Manchester United መረጃዎችን የሚያገኙበት የ Telegram ቻናል ነው 🇪🇹
--------------------------------------------------------------
☞︎| ስለ ማንቸስተር ዩናይትድ ትኩስ መረጃዎች
☞| ቀጥታ ስርጭቶች ከየስታድየሞቹ
☞| የዝውውር ዜናዎች
☞| ስለ ማንችስተር ዩናይትድ ታሪኮች

📩 ለማስታወቂያ ስራ DM :- @Marcoabdu

Last updated 3 months, 1 week ago