Unlock a World of Free Content: Books, Music, Videos & More Await!

ᴇʟɪᴀꜱ ᴍᴇꜱᴇʀᴇᴛ

Description
Journalist-at-large
We recommend to visit

ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ

Last updated 3 days, 15 hours ago

ለማንኛውም አስተያየት እና ጥቆማ 👉 @Esat_tv_comment_bot

🇪🇹ኢሳት የኢትዮጵያ አይን እና ጆሮ🇪🇹

Last updated 6 days, 1 hour ago

Last updated 2 months ago

1 week, 4 days ago

አስተያየት እና ጥቆማ ለምታደርሱኝ፣

አካውንቶቼ ለተወሰኑ ሳምንታት ዝግ ሆነው ይቆያሉ፣ ሁሉንም መልእክቶቻችሁን ላልመለከት ስለምችል አቆዩልኝ።

መልካም ግዜ 👋👋

@EliasMeseret

1 week, 4 days ago

#Update የአለም ምግብ ፕሮግራም (WFP) በድሬዳዋ ነፃ የንግድ ቀጠና ዙርያ ባቀረብኩት መረጃ ላይ ያደረሰኝ መረጃ

በድሬዳዋ ነፃ የንግድ ቀጠና ውስጥ ከሚገኝ የምግብ ማከማቻ መጋዘን ውስጥ ለተራቡ ዜጎች ተብለው የሚወጡትን የምግብ አይነቶች እዛው የንግድ ቀጠና ውስጥ ፓኬጁ ላይ ባንዲራ በመጨመር እየታሸጉ እንደሆነ አንድ መረጃ አቅርቤ ነበር።

በዚህ ዙርያ የአለም ምግብ ፕሮግራም ይህን መረጃ አድርሶኛል:

"WFP procured 50,000 MT of wheat on behalf of the EDRMC from WFP’s Global Commodity Management Facility (GCMF) - WFP's regional storage facility for purchased commodities - for EDRMC’s humanitarian support to communities affected by drought, floods, and conflict in Ethiopia. The wheat purchased from WFP by EDRMC is being collected from WFP’s warehouses in Dire Dawa after it has been transferred from UN bags to those provided by the government, ready for distribution. WFP occasionally leverages its extensive procurement expertise and networks to provide food procurement services to partners allowing them to respond to food needs in a timely manner."

ለመረጃው የአለም ምግብ ፕሮግራምን እያመሰገንኩ በለጋሽ ድርጅቶች የሚገዙ የምግብ አይነቶችን 'በኢትዮጵያ የተመረተ' በሚል ማሸግያ ቀይሮ ማውጣት ለምን እንዳስፈለገ የሚመለከተው የመንግስት አካል አስተያየት ቢሰጥበት መልካም ነው እላለሁ። በቅርብ ወራት የእርዳታ ምግብ ምን ሲደረግ እንደነበር የሰማን/የምናውቅ እና እርዳታው ለተጠቃሚው ህዝብ እንዲደርስ የምንፈልግ ሁሉ ይህን መጠየቅ አለብን።

@EliasMeseret

1 week, 5 days ago

የዛሬ 50 አመት የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ከካናዳ፣ ከሳውዲ አረቢያ፣ ከቱርክ፣ ከአውስትራሊያ፣ ከጣልያን... ወዘተ ይበልጣል?

አንዳንድ 'ተቀፅላዎች' ይህን ስክሪንሾት በስፋት ሲያጋሩ እንደነበር ጥቆማዎች ደርሰውኝ ነበር፣ እንዲጣራም የጠየቁ አሉ። ነገሩ እንዲህ ነው፣

መረጃው በ Goldman Sachs የ 2022 ሪፖርት ላይ የተመሰረተ ሲሆን የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ እ.አ.አ በ 2075 ወይም የዛሬ 50 አመት 6.2 ትሪሊየን ዶላር የማደግ እድል እንዳለው ይጠቁማል። በዚህ መረጃ ላይ ታድያ እነ ከካናዳ፣ ሳውዲ አረቢያ፣ ቱርክ፣ አውስትራሊያ፣ ጣልያን ከኢትዮጵያ በታች የተቀመጡ ሲሆን ቻይና፣ ህንድ እና አሜሪካ ከ 1-3 ያለውን ቦታ ይዘዋል።

እውነታው ግን ወዲህ ነው፣

እንዲህ አይነት የኢኮኖሚ እድገት ትንበያዎች በአብዛኛው የወደፊት የማደግ አቅምን የሚያሳዩ ሲሆን በርካታ አሁናዊ እና የወደፊት እድሎችን እና መሰናክሎችን አያካትትም። በተጨማሪም ይህ አሀዝ በከፍተኛ ደረጃ የሚንተራሰው የህዝብ ብዛት ቁጥር ላይ ነው።

የኢትዮጵያ ህዝብ ብዛት በ2075 አካባቢ 281 ሚልዮን ይገመታል፣ ይህም ለከፍተኛ ምርታማነት እና የኢኮኖሚ እድገት መሰረት የመሆን እድል አለው። ሪፖርቱ የጠቀሰውም ይህን ነው።

ይሁንና ተቀፅላዎቹ ሊያቀርቡት እንደፈለጉት ይህ ብቻውን የሀብት ወይም እድገት መለኪያ እንዳልሆነ አለም ተግባብቷል። ትክክለኛ እድገት መለኪያው ፍትሀዊ የሀብት ክፍፍል፣ የኑሮ ደረጃ መሻሻል፣ እንደ ውሀ፣ መኖርያ ቤት እና ኤሌክትሪክ ላሉ አገልግሎቶች ያለ ተደራሽነት... ወዘተ መሆናቸውን ራሱ Goldman Sachs ይጠቅሳል።

- የጋሪ እና ፈረስ ትራንስፖርት እናመጣለን እየተባለ ወደ ቀደመው ክፍለ ዘመን ወደኋላ ለመሄድ እየተንደረደርን

- በአለም ትላልቅ የሚባሉ ግጭቶች፣ ጦርነቶች፣ መፈናቀሎች እና ስደቶች እያስተናገድን

- የህዝብ የመኖር፣ የቤት ባለቤትነት፣ የስራ እና ተንቀሳቅሶ የማምረት አቅም እየተፈተነ... ወዘተ ባለበት ወቅት ይህን ትንበያ ይዞ ከካናዳ እና አውስትራልያ ልንበልጥ ነው ማለት ማደንዘዣ እንጂ ምንም ሊሆን አይችልም።

ብቻ መልካሙን ለሀገራችን እንመኛለን።

@EliasMeseret

2 months, 1 week ago

#FactCheck እሁድ እለት በአድዋ ሙዚየም ምርቃት ወቅት የቀረበው የአፄ ምኒሊክ ንግግር እንደተባለው በ "ሆሎግራም" ቴክኖሎጂ የቀረበ አልነበረም 

በመጀመርያ የተወሰኑ ፅሁፎችን ለማንበብ ብንሞክር ለመረዳት የምንችለው ሆሎግራም ማለት ባለ ሶስት አውታር ምስል (three dimensional image) ሲሆን በረድፍ ከሚለቀቅ የብርሀን ምንጭ የሚፈጠር ምስል ነው። ይህ ብርሀን ከኮምፒውተር የሚለቀቅ ወይም ከአንድ ስፍራ የተለቀቀ ብርሀን ወደ አንድ አቅጣጫ በማንፀባረቅ የሚፈጠር ሊሆን ይችላል (ምስሉ ላይ የዝሆኑ ምስል ምሳሌ ይሆናል)። በዚህም ምክንያት የሆሎግራም ምስሎችን ካለ 3D መነፅር በአይን መመልከት ይቻላል።

የሆሎግራም ቴክኖሎጂ በመጀመርያ የተፈጠረው በዩሪ ዴኒስዩክ፣ ኤሜት ሌይት እና ጁሪስ ኡፓትኒክስ የዛሬ 62 አመት ነበር። ይሁንና ቴክኖሎጂው አሁን አሁን በስፋት ጥቅም ላይ እየዋለ ይገኛል።

ታድያ በአድዋ ሙዚየም ምርቃት ወቅት የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት በአፍሪካ ለመጀመሪያ ግዜ፣ በዓለም ደግሞ እጅግ ጥቂት ሀገራት ሊያሳኩ የቻሉትን የሆሎግራም ቴክኖሎጂ ተጠቅሞ የአፄ ምኒሊክ ንግግርን አቀረበ ተብሎ ተነግሮ ነበር።

ይህን መረጃ በወቅቱ ስሰማ 'እስቲ ይሁን' በማለት አልፌው ነበር፣ ነገር ግን ዛሬ ጠዋት እንደገና አዲስ ሚድያ ኔትዎርክ (AMN) በዚህ ዙርያ በሰራው አንድ ዘገባው "ዳግማዊ አፄ ምኒልክ በዓድዋ ድል መታሰቢያ አዳራሽ  ያቀረቡት ንግግር  በተለመደው እስክሪን ላይ በቪዲዮ ካሜራ ተቀርፆ የተዘጋጀ ሳይሆን ሆሎግራም በሚባል የወደፊቱ ዓለም ቴክኖሎጂ  መድረክ ላይ ልክ በአካል እንደሚታይ ሰው  ሆኖ  የቀረበ ነው" ብሏል።

እውነት ነው፣ ትክክለኛ ሆሎግራም የሚሰራው በብርሀን ልቀት አማካኝነት ነው። እሁድ መድረክ ላይ በአካል የቀረበው፣ ሲተርክም ድምፁ የሚሰማው ግን አርቲስት ተስፋዬ ገብረሀና ነው።

ምስሉ ላይ እንደምትመለከቱት መድረክ ላይ የቆመው አርቲስቱ ጥላው ይታያል፣ ወደ መድረክ ሲመጣ እና ሲመለስ ኮቴው ይሰማል፣ እርሱ መሆኑንም ከእራሱ አረጋግጫለሁ። በእለቱ የሆነው አፄ ምኒሊክን መስሎ የቀረበውን የተስፋዬን ምስል በፕሮጀክተር ስክሪን ላይ ማሳየት ነበር።

በመጨረሻም፣ ቴክኖሎጂው በአፍሪካ እስካሁን እንደ ደቡብ አፍሪካ፣ ታንዛንያ፣ ናይጄርያ፣ ግብፅ፣ ኬንያ በመሳሰሉ ሀገራት ጥቅም ላይ ውሏል።

በነገራችን ላይ የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ሆሎግራም ሰራሁ አላለም፣ በመድረኩ ተባለ እንጂ። በተቋሙ በርካታ ጎበዝ ልጆች እንዳሉ ሰምቻለሁ፣ ግን እንዲህ ያልሰሩትን እንደሰሩ፣ የሰሩትን እንዳልሰሩ ማቅረቡ ትክክል አይመስለኝም።

መልካም ቀን።

@EliasMeseret

2 months, 1 week ago
ᴇʟɪᴀꜱ ᴍᴇꜱᴇʀᴇᴛ
2 months, 1 week ago

የኢንደስትሪ ሚኒስትሩ ከሰሞኑ የተሸለሙት የ African Governance Award ሽልማት ምንድን ነው?

አሁን አሁን እየተለመደ የመጣ ነገር ቢኖር የመንግስትም ሆነ የግል ድርጅቶች "ሽልማት አገኘን፣ ምርጡ ተብለን ተሰየምን፣ ፋና ወጊ ተብሎ ተነገረልን..." የሚል ዜና መስማት ነው። እርግጥ ነው ትክክለኛ አለም አቀፍ እውቅና የሚያገኙ እንደ የኢትዮጵያ አየር መንገድ አይነት ተቋማት አሉ፣ ግን ሌላ ጨዋታም አለ።

ታድያ ለእንዲህ አይነት ዜና ያለውን ከፍተኛ ጥማት የተረዱት በተለይ ናይጄርያውያን እና ጋናውያን ጋዜጠኞች ተፍ ተፍ እያሉ ይገኛሉ፣ ሽልማቶችን በገፍ ያከፋፍላሉ። ከዛም ለሚድያቸው የሚሆን ለማስታወቂያ በሚል ዳጎስ ያለ ክፍያ ይቀበላሉ፣ የሽልማት ስነ-ስርዐት አዘጋጅተው አንደኛ-ሁለተኛ-ሶስተኛ ደረጃ ስፖንሰር ብለው ከፋፍለው ገቢያቸውን ያጦፋሉ።

ለዚህ ማሳያ የሚሆነው ጋናዊው ጋዜጠኛ አዩሬ አታፎሪ ሰሞኑን በግሉ ያዘጋጀው የ African Governance Award ነው። በሽልማቱ ላይ የኢንደስትሪ ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አለበል በኢንደስትሪው ዘርፍ ሽልማት አግኝተዋል። እንደ ኬንያ፣ ሴራሌዎን እና ደቡብ ሱዳን ካሉ ሀገራት የተውጣጡ ግለሰቦች እና የመንግስት ሀላፊዎች ሽልማታቸውን ሞሪሺየስ ላይ ተቀብለዋል። የእኛ ሀገር ሚድያዎች "በአፍሪካ ደረጃ የተሰጠ ሽልማት" እያሉ ሲዘግቡት እያየሁ ነበር።

ወንድሜ አዩሬ ሽልማት ለመስጠት ክፍያ አይጠይቅም፣ ግን ሽልማት የሚያገኙ ግለሰቦች በድርጅታቸው በኩል "The Business Executive" የተባለው መፅሄቱ ላይ ማስታወቂያ እንዲያስነግሩ ያረጋል፣ የሽልማት ስነ ስርዐቱንም በራሳቸው ተሸላሚዎች ወጪ (sponsorship) ይዘጋዋል።

ሌላው የሚገርመው ድረ-ገፁ (አቀራረቡ ድረ-ገፅ ብሎ ለመጥራት የሚከብድ ቢሆንም) ላይ ማን እንዳሸነፈ፣ ማን እጩ እንደነበር... ወዘተ መረጃ የለውም። ያለው መረጃ ለሽልማት ራሳችሁን ወይም ድርጅቶችን ጠቁሙ፣ ማስታወቂያም አምጡ አይነት ነው: https://afga.thebusinessexecutive.net/index.php

በነገራችን ላይ ዘንድሮ የሽልማቱ አንዱ ተቀባይ KEMA የተባለ የኬንያ መድሀኒት አስመጪ ድርጅት ሲሆን ለወባ መከላከያ በወጣ ጨረታ 3.7 ቢልዮን የኬንያ ሽልንግ መዝብሮ ተገኝቶ በቅርቡ በሀገሪቱ ሚድያዎች የተጋለጠ ነው።

ምናልባትም እንዲህ አይነት ሽልማቶች ችግሮችን መሸፋፈን ለሚፈልጉም ጥሩ ማደንዘዣ ሳይሆን አይቀርም። የእኛኑ በቅርብ ግዜ ከስራ ውጪ የሆኑ ከ460 በላይ የኢንደስትሪ ተቋማትን ታሳቢ ካረግን ጉዳዩ ይጠራል።

የሽልማቱን ፎቶዎች አያይዣለሁ፣ ፎቶዎቹም ትንሽ ይናገራሉ።

@EliasMeseret

2 months, 2 weeks ago

#ትኩረት ሌላ አለም ላይ እንዲህ አይነት የከፋ አደጋ ሲያጋጥም የመንግስት የአደጋ መከላከል አካላት፣ አስፈላጊ ከሆነም የጦር ሰራዊት አባላት በምድር እና በአየር ተረባርበው ህይወት ለማትረፍ ይጥራሉ፣ የሰው ህይወት የረከሰበት እኛ ሀገር የአደጋው መረጃ በአብዛኞቹ የመንግስት ሚድያዎች ለህዝብ አልደረሰም (ስፖኪዮ የሰረቀ ልጅ ተያዘ የዛሬ ዋና ዜናቸው ነበር)።

የዛሬ 14 አመት ቺሊ ውስጥ የማዕድን ማውጫ የተደረመሰባቸው 33 ሰራተኞች ከ69 ቀናት ትግል በኋላ ህይወታቸው የተረፈበት አጋጣሚን አስቤ ይህን የእኛን ስሰማ አዘንኩ። መረጃው ከታች ይገኛል ⬇️

በደቡብ ወሎ ውስጥ በማዕድን ስራ ላይ ተሰማርተው የነበሩ በቁጥር እስከ 30 የሚሆኑ ዜጎች ባለፈው ሀሙስ ዋሻ ተደርምሶባቸው ያሉበት ሁኔታ አልታወቀም።

በደላንታ ወረዳ ውስጥ በህጋዊ መንገድ ኦፓል በማውጣት ላይ የነበሩ እነዚህ ሰዎችን ለማውጣት የሚደረገው ጥረት በአካባቢው ማህበረሰብ እስከዛሬ ቢቀጥልም ውጤት አለመገኘቱ ታውቋል።

ትናንት እሁድ ቢቢሲ ያነጋገራቸው የወረዳው አስተዳዳሪ አቶ አያሌው በሪሁን ባለፉት ቀናት ከአምስት መቶ በላይ ሰዎች በነፍስ አድን ሥራው ላይ እገዛ ለማድረግ ወደ ሥፍራው ቢያቀኑም ወደ ዋሻው ለማምራት የሚያስችለው መንገድ ጠባብ እና በአንድ ጊዜ ከአስር ሰዎች በላይ ማስገባት ባለመቻሉ ጥረታቸው አዝጋሚ መሆኑን ተናግረዋል።

ስምንቱ የማኅበሩ አባላት በናዳው ተይዘው እንደሚገኙ የገለጸው ወርቅ ዋሻ የከበሩ ማዕድናት አምራቾች ማኅበር ሊቀመንበር ተስፋዬ አጋዥ በበኩሉ እስካሁን በተደረገው ጥረት 150 ሜትር ርዝማኔ ወዳለው ዋሻ ዘልቆ ለመግባት መቆፈር የተቻለው 33 ሜትር ገደማ ብቻ መሆኑን ለሚድያው ተናግረዋል።

ይህ አደጋ ከተከሰተ በኋላ በመንግሥት በኩል የተቀበሩትን ሰዎች ያሉበትን ሁኔታ ለማወቅም ሆነ ከዋሻው ለማውጣት የተደረገላቸው ድጋፍ እንደሌለም ገልጿል።

Photo: File

@EliasMeseret

2 months, 2 weeks ago

የቤተሰብ አባላቱ ለጉብኝት ከውጭ ወደ ሀገር ቤት ይገባሉ።

ትንሽ እንዝናና ብለው ከአዲስ አበባ ወጣ እንዳሉ እገታ ይፈፀምባቸዋል።

10 ሚልየን ብር ክፈሉ ተባሉ፣ ከፈሉ፣ ጥቂት ሰው ተለቀቀ።

የመክፈል አቅም አላቸው ብለው ሳይጠረጥሩ ያልቀሩት አጋቾች ተጨማሪ 10 ሚልዮን አምጡ ይሏቸዋል፣ አሁንም ይህ ብር ይከፈላል፣ ጥቂት ሰዎች ይለቀቃሉ።

ለሶስተኛ ግዜ ሲጠየቅ ግን ያላቸውን ንብረት ሸጠው እና ተበድረው የጨረሱት ሰዎቹ "ያለንን በሙሉ ሰጠን፣ ምንም የለንም" ይላሉ።

አሁን ድረስ ቀሪው የቤተሰቡ አባላት በእገታ ላይ ይገኛሉ፣ አጋቾቹም ስልክ መመለስ አቁመው ጭንቅ ላይ ይገኛሉ።

እንዲህ አይነት ወንጀሎች የማይነገርበት፣ እንደ ሿሿ ያለ ተራ ወንጀል ግን በየቀኑ የሚለፈፍበት ግዜ ላይ መድረሳችን ብዙዎችን እያሳዘነ እና እያስገረመ ይገኛል።

(ገና እገታ ላይ ያሉ የቤተሱ አባላት ስላሉ ዝርዝር መረጃውን ትቼዋለሁ)

2 months, 2 weeks ago

#NewsFlash በኢትዮጵያ የስራ አስፈፃሚውን በጠ/ሚር ከሚመራ (parliamentarian) ወደ ፕሬዝደንታዊ (presidential) ስርዐት የመለወጥ ሂደት መጀመሩ ተሰምቷል።

ጠ/ሚር አብይ አህመድ ወደ ስልጣን የመጡ ሰሞን በስፋት ይነሳ የነበረው ይህ የፕሬዝደንታዊ ስርዐትን የመዘርጋት ሂደት አሁን ከታሰበው የህገ መንግስት ማሻሻያ ጋር አያይዞ በስፋት ስለተሄደበት በቅርብ ግዜያት ለህዝብ ይፋ እንደሚደረግ የደረሰኝ መረጃ ይጠቁማል።

በፓርላመንታዊ ስርዐት ዜጎች የመረጧቸው የህዝብ ተወካዮች ጠ/ሚሩን ሲመርጡ በፕሬዘደንታዊ ስርዐት ደግሞ ዜጎች በቀጥታ ፕሬዝደንት የሚሆነውን ይመርጣሉ።

@EliasMeseret

5 months, 4 weeks ago

ይህ ቻናል ከ4- 6 ሳምንታት ዝግ ሆኖ ይቆያል፣ ስለዚህ ጥቆማዎች እና መረጃዎች የማይስተናገዱ ይሆናል።

"የሆነ ነገር ሊከሰት ነው መሰለኝ ሊጠፋ ነው" የሚሉ ኮመንቶችን ለማንበብ ተዘጋጅቻለሁ 😊

ቸር እንሰንብት 🙏

@EliasMeseret

We recommend to visit

ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ

Last updated 3 days, 15 hours ago

ለማንኛውም አስተያየት እና ጥቆማ 👉 @Esat_tv_comment_bot

🇪🇹ኢሳት የኢትዮጵያ አይን እና ጆሮ🇪🇹

Last updated 6 days, 1 hour ago

Last updated 2 months ago