"ይህ የቴሌግራም ቻናሌ ግንቦት1/2011ዓም የተከፈተ ነው። የእኔን የስልክ ወጪ ጨምሮ አገልግሎቴን መደገፍ የምትፈቅዱ ጓደኞቼ በ
👉🏿 https://donorbox.org/zemedemedia እና
👉🏿 https://www.paypal.com/paypalme/ZemedkunB በኩል ማገዝ ትችላላችሁ። በተረፈ ለቤተ ክርስቲያኔና ለኢትዮጵያ ሀገሬ የሚጠቅመውን ሁሉ አበረክት ዘንድ አብዝታችሁ ጸልዩልኝ።
Last updated 3 days, 14 hours ago
The first Telecom operator in Ethiopia https://t.me/EthiotelecomChatBot
Last updated 1 month ago
ለማንኛውም አስተያየት እና ጥቆማ 👉 @Esat_tv_comment_bot
🇪🇹ኢሳት የኢትዮጵያ አይን እና ጆሮ🇪🇹
Last updated 1 month ago
ተዘርፎ የተዘረፈው ወርቅ!
ጉዳዩ እንዲህ ነው: የሰሜኑ ጦርነት ከጀመረ በኋላ በርካታ የፀጥታ አካላት ከሹማምንት ጋር በመሆን የትግራይ ተወላጅ ቤቶችን እየፈተሹ በተለይ ወርቅ እና ብር ይዘርፉ ነበር።
እነዚህ ዜጎች ፍርድ ቤት እንዳይሄዱ እና ለማንም አቤት እንዳይሉ ማስፈራርያ ይነገራቸዋል፣ አለበለዛ በ "ጁንታ" ደጋፊነት አስከፊ ነገር እንደሚጠብቃቸው ስለሚነገራቸው ዝም ብለው ይቀመጣሉ።
ታድያ በዚህ መልኩ ከተዘረፈው ወርቅ ውስጥ እጅግ በርካታ መጠን ያለው ወርቅ የደረሳቸው አንዱ ከፍተኛ ሹም (የፍትህ አካል ከፍተኛ አመራር ነበሩ፣ የህዝብ ተወካይም ናቸው) ቤታቸው በሌባ ይሰበርና ወርቁ በሙሉ ይወሰዳል (በጥቆማ የተደረገ ይመስላል)።
ከዛማ እንዴት አርገው ያስመልሱ ወይም ለፖሊስ እንኳን ያመልክቱ!?
ይህ ሁሉ ወርቅ ከየት መጣ እንዳይባል እና እንዳይጠቆሩ ዝም... ጭጭ... ዋጥ አርገውት እንደቀሩ በቅርብ ጉዳዩን ከሚያውቁ ሁለት ሰዎች ከሰሞኑ ያገኘሁት መረጃ ይጠቁማል።
የሰው ወርቅ አያደምቅ ይልሀል ይሄ ነው።
በባህር በር ጉዳይ ላይ የተነሳውን ሀሳብ ተመርኩዞ የሰጠሁትን አስተያየት አንዳንዱ የተቃውሞ አድርጎ ስሎታል።
ግን አይደለም፣ የድጋፍም የተቃውሞም አይደለም፣ በግልፅ እንዳሰፈርኩት እንደ አንድ ተራ ግለሰብ የእኔ አቋም ዋጋ እምብዛም የለውም፣ ስለዚህ ይቆይ ብያለሁ።
እርግጠኛ ሆኜ መናገር የምችለው ግን ይፋ የተደረገበት ግዜ ትክክለኛ አይደለም፣ timing አመራረጥ ላይ ችግር አለ ብዬ ከነ ምክንያቱ በግልፅ አስፍሬያለሁ።
አሁንም ኢትዮጵያውያን ልብ ልንል የሚገባው ሌላው ጉዳይ የመንግስት ሚድያዎች እና አክቲቪስቶቻቸው እንደሚሉት "እንነጋገር ነው የተባለው... ስለ ጦርነት የተናገረ የለም" የሚለው የማለሳለስ አካሄድ ህዝብን አዘናግቶ ጦርነት መሀል ሊማግድ የሚችል አደገኛ ጉዳይ መሆኑን ነው... ልክ በ15 ቀን የሚያልቅ "የህግ ማስከበር ነው" ተብሎ በሁለት አመት በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎችን እንደፈጀው ጦርነት ማለት ነው።
የዲፕሎማቲክ ምንጮች እንደሚነግሩን ከሆነ በጎረቤት ሀገራት ዘንድ "confusion, tension and unease" የፈጠረ ንግግር እንደሆነ፣ በተጨማሪም የወደብ ጉዳዩ አሁን ሊፈታ ባይችል በልጅ፣ ልጆቻችን ይፈታል መባሉ ከዚህ በኋላ የሚመጣው ትውልድ ጭምር እስከመጨረሻው በጥርጣሬ እንዲተያይ እና በቀጠናው አስተማማኝ እና ቋሚ ሰላም እንዳይፈጠር ምክንያት ሊሆን እንደሚችል ያስረዳሉ።
እስካሁን ኤርትራ፣ ጅቡቲ እና ሶማልያ ለጉዳዩ negative መልስ ሰጥተዋል፣ ከ OSINT ምንጮች የሚገኙ መረጃዎች ደግሞ በኤርትራ በኩል የጦር እንቅስቃሴ እንዳለ ያሳያሉ።
ይህ በእንዲህ እንዳለ ይህ የኢትዮጵያ ሀሳብ በቴሌቭዥን መስኮት ይፋ ከመደረጉ በፊት ለኤርትራ መንግስት በውስጥ ቀርቦ "a resounding no!" የተባለ መልስ በመመለሱ ጉዳዩ ለህዝብ ይፋ እንደተደረገ የደረሰኝ መረጃ ይጠቁማል።
እነዚህ እንደ ማሳያ ያነሳኋቸው ነጥቦች የሚያመላክቱት ጉዳዩ ጥልቅ የሆነ ጂኦፖለቲካዊ ውጤት ያለው እንደሆነ፣ ሊያስከትል የሚችለውን ከፍተኛ ፖለቲካዊ፣ ወታደራዊ፣ ዲፕሎማሲያዊ እና ኢኮኖሚያዊ ጫና ለመቋቋም ውስጣዊ ጥንካሬ እና አንድነት እንደሚያስፈልግ ያሳያሉ።
በመጨረሻም፣ እንደፈረደብን ከዚህ በኋላ ደግሞ የተለየ ሀሳብ ያለውን "የኤርትራ ተላላኪ፣ የታሪካዊ ጠላቶቻችን ተባባሪ፣ የሻዕቢያ ደጋፊ...ወዘተ" ስሞችን ወይም እንደ ጁንታ እና ጃውሳ የሚወጣ አዲስ ስም በስፋት እንደምናይ ይታየኛል። Mark my word!
ሰላም ለሀገራችን፣ ሰላም ለሰው ዘር በሙሉ!
አሁን አሁን እየተለመደ የመጣ ነገር ቢኖር መንግስት ሊሄድባቸው ያሰበባቸውን መንገዶች ቀድሞ ለአክቲቪስቶች ማሾለክ እና በግልፅ ሊናገራቸው የማይፈልጋቸውን ነጥቦች በእነሱ በኩል ማስተላለፍ ነው።
ይህን ለማለት ያነሳሳኝ በቅርቡ ጠ/ሚሩ ስለ ባህር በር ጉዳይ ባደረጉት ገለፃ ዙርያ እነዚህ አክቲቪስቶች እያነሷቸው ያሉ አስገራሚ ነጥቦች ናቸው። ለምሳሌ ባለፉት ጥቂት ቀናት ከሰማኋቸው መሀል የተወሰኑት እነዚህ ይገኙበታል:
- ኤርትራ ከፈለገች አሸዋውን ትብላው፣ እኛ የዘይላ ወደብን እንጂ አሰብን እና ምፅዋን አላልንም
- የኤርትራ ወደቦች ካስፈለጉንም በፀባይ ጠይቀን እምቢ ካሉ በፈለጉት መልኩ መቀበል እንችላለን
- ጅቡቲን የምታክል ሀገር ወደብ ኖሯት እኛ የለንም ማለት ውርደት ነው፣ በወታደር ከቦ ማስጨነቅ ነው
ታድያ እነዚህ ነጥቦችን ሲያነሱ እና ሲጥሉ የሚውሉት አብዛኞቹ ታማኝ ሎሌ አክቲቪስቶች ናቸው፣ በብሄራዊ ቴሎቭዥን ቀርበው ሴራ ሲተነትኑ የሚውሉም አሉ።
የዲፕሎማሲ ስራውን በከፊል ለአክቲቪስት አስረክቦ በእንደዚህ አይነት አካሄድ የት እንደምንደርስ እንጃ፣ ምክንያቱም የኢትዮጵያ ህዝብም ሆነ በቅርበት ሀገሪቱን የሚከታተል ሁሉ ይህን ያለተለመደ አካሄድ በደንብ ተረድቶታል፣ ከመንግስት በተዋረድ "እንደዚህ በሉ..." ተብለው እንደሆነ ተገንዝቧል።
የሀገር ጉዳይ ነውና ይታሰብበት!
ለልጅ፣ ልጆቼ የማወርሳቸው ትልቁ ነገር ህዝቤ በእርስ በርስ ጦርነት ሲጫረስ "ግፋ በለው፣ ቁረጠው፣ ፍለጠው፣ ግደለው..." ሳልል በሙያዬ ማድረግ የምችለውን እስከ መጨረሻው ድረስ መረጃን ለህዝብ እና ለአለም አቀፍ ማህበረሰብ ማድረስ ብቻ መስራቴ የሰጥኝን ሰብአዊነት ነው።
ይህን ማድረጌ ብዙ ነገር አስከትሎብኛል (ወደፊት እገልፀው ይሆናል) ነገር ግን ይህ እኔ ላይ የደረሰው ብዙ ሺህ መቶ ሌሎች ዜጎች ጦርነቱ ያስከተለባቸው ጉዳት እና ወዳጅ፣ ዘመድ ማጣት እጅጉን ይበልጣልና አላማርርም።
"ስልጣኔን ተነጠቅኩ" ያለ እና "ስልጣኔን ሊወስዱብኝ ነው" ብሎ የተነሳ አካል ምድሪቱን በደም አጨቅይቷል፣ አሁንም ውጊያ እና ተኩስ እዚህ እዚያም አለ። በዚህ ሁሉ መሀል ማረጋገጥ የቻልኩትን ያህል መረጃ ለህዝብ ማቅረብ እቀጥላለሁ።
አብራችሁኝ ለነበራችሁ ሁሉ ምስጋናዬ የላቀ ነው።
መልካም ምሽት።
#የካድሬነገር ይህን ታውቁ ኖሯል?
"ማህበራዊ ሚድያ ላይ ተፅእኖ መፍጠር እና ቅቡልነትን ማሳደግ" በሚል ፕሮግራም 300 ካድሬዎች የዛሬ አመት ተኩል ገደማ ስልጠና ተሰጥቷቸው ነበር፣ ስራቸው ደግሞ እስከ 10,000 የሚደርሱ ሌሎች ካድሬዎችን አሰልጥነው ማህበራዊ ሚድያ ላይ ማሰማራት ነው።
አላማውስ?
የአመራሩን ገፅታን ሊያሳድጉ የሚችሉ መረጃዎችን ማህበራዊ ሚድያ ላይ ማሰራጨት፣ የሚቃወሙትን በአስተያየት ማውገዝ፣ በአመራሮች በቀጥታ በሚተላለፉ ስርጭቶች ላይ ጭምር በመግባት የድጋፍ አስተያየቶችን በተለያዩ ቋንቋዎች መፃፍ... ወዘተ።
እነዚህ ናቸው እንግዲህ ፌስቡክ Live ስርጭቶች ላይ ገብተው ሲፃፅፉ እና ሌላውን ሲሳደቡ የሚውሉት። ካድሬ ቢንጫጫ ለቀይ ወጥ እና አልጫ ያለው ትዝ አለኝ።
*Someone just asked me... አሁን እነሱም ቢሮ ለመግባት ታክሲ ይጋፋሉ?
በሙዝ ልጣጭ ማስኬድ ነበር እንጂ!
#Update በጃፓን የኤርትራ አምባሳደር የሆኑት እስጢፋኖስ በትዊተር ገፃቸው ትናንት ምሽት በኢትዮጵያ ለቀረበው ሀሳብ ምላሽ የሚመስል ይህን ፅሁፍ አስፍረዋል:
"ግንቦት 1998 (እአአ) የኢትዮጵያ ፓርላማ በኤርትራ ላይ ጦርነት አወጀ... ከዛ በኋላ ኤርትራን የባህር በር አልባ ለማድረግ ሁሉንም አይነት አሰቃቂ ድርጊት ፈፀመ። ድርጊቱ ግን አልተሳካም! ይህን የማያውቅ ማን ነው?"
*የዚህ የ1998 ጦርነት መነሻ ኤርትራ ኢትዮጵያን በመውረሯ እንጂ ኤርትራን ወደብ አልባ ለማድረግ እንዳልነበር ቢታወቅም የአምባሳደሩ አባባል ግን በኤርትራውያን ዘንድ የትናንቱ ንግግር የፈጠረውን ስሜት በከፊል የሚያሳይ ይመስላል።
የኢሉይድ ኪፕቾጌ የአለም የማራቶን ሪከርድ በሌላ ኬንያዊ ተሰብሯል!
ኬልቪን ኪፕቱም ዛሬ በተካሄደው የቺካጎ ማራቶን 2:00:35 በመግባት በአለም ኦፊሴላዊ የማራቶን ውድድር ከ 2:01 በታች የገባ የመጀመርያው ሰው ሆኗል።
አትሌቱ ማራቶን ሲሮጥ ይህ ሶስተኛው ሲሆን (እነሱንም ባለፈው አስር ወራት ውስጥ ብቻ) ምናልባት ሪከርድ ለመስበር ይቀላል በሚባለው የበርሊን ማራቶን ከ2 ሰአት በታች የሚገባ የመጀመሪያው አትሌት ሊሆን እንደሚችል ተገምቷል።
በሴቶች ውድድር ለኔዘርላንድስ የምትሮጠው ሲፋን ሀሰን የስፍራውን ሪከርድ በማሻሻል አሸንፋለች።
A new distance running great in the making!
Image: World Athletics
በዚህ የኢትዮጵያ አየር መንገድ አርማ በሌለው አውሮፕላን ዙርያ እየተሰራጨ ያለ ሀሰተኛ መረጃ!
ይህ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ንብረት የሆነ ቦምባርዲየር (Q-400) አውሮፕላን ምስልን በማያያዝ "የኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላማ በብቸኝነት እስከአሁን ሳይደፈር፣ ሳይነካ የቆየው በአንድ ለእናቱ በኢትዮጵያ አየር መንገድ አውሮጵላኖች ላይ ነበር" የሚል ፅሁፍ ማህበራዊ ሚድያ ላይ ተጋርቶ ተመልክተናል።
ይህ ፅሁፍ አክሎ "አሁን ግን ከውስጥ በሚወጡ መረጃዎች መሠረት ጽንፈኛ ኦሮሞዎቹ የኢትዮጵያን ሰንደቅ ዓላማ በክልላችን በሚያርፍ አውሮጵላን ላይ ማየት አንፈልግም በማለታቸው ምክንያት የተነሣ በሃገር ውስጥ በረራ በሥራ ላይ ያሉትን ሎምባርዲ q400 ከተሰኙ የኢትዮጵያ አየር መንገድ አውሮጵላን ላይ አረንጓዴ ቢጫ ቀይ ቀለማቱን ማጥፋት መጀመራቸው ተመልክቷል" ይላል።
ይህ መረጃ ሀሰተኛ ሲሆን እውነታው እንደሚከተለው ነው።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ይህ ቦምባርዲየር አውሮፕላን ላይ ብቻ ሳይሆን (ምናልባት እንደኔ አጋጥሟችሁ ከሆነ) እንደ ቦይንግ ያሉ ሞዴሎቹ አንዳንድ ግዜ ምንም አርማ (በባለሙያዎቹ አጠራር livery) ሳይኖራቸው ወይም አየር መንገዱ አባል የሆነበትን Star Alliance አርማ ብቻ ይዞ አገልግሎት ይሰጣል።
ለምን?
የ Star Alliance አርማን አልፎ አልፎ አውሮፕላኖቹ ላይ ማኖር የአባልነት ቅድመ ሁኔታ ሲሆን በምስሉ ላይ እንደሚታየው ምንም አርማ ሳይኖራቸው የሚታዩት ደግሞ አየር መንገዱ በሽርክና አብሯቸው የሚሰሩ እንደ Asky Airlines, Malawi Airlines, Tchadia, Zambia Airlines... ወዘተ ያሉ አየር መንገዶች አውሮፕላኖቹን ተጠቅመው ሲመልሱ የኢትዮጵያ አየር መንገድ አርማ እስኪቀባ ድረስ እንዲህ በሙሉ ነጭ ሆነው ሊታዩ ይችላሉ።
በዚህ ዙርያ የአየር መንገዱን ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ መስፍን ጣሰውን ያነጋገርኩ ሲሆን "ይህ [ማህበራዊ ሚድያ ላይ የተሰራጨው መረጃ] ፍፁም ውሸት ነው፣ ማንም የኢትዮጵያ አየር መንገድን አርማ ከአውሮፕላኖቻችን እንድናነሳ አልጠየቀንም" ብለው ምላሽ ሰጥተውኛል።
በምስሉ ላይ የሚታየው አውሮፕላንም አየር መንገዱ አብሮት ከሚሰራ ሌላ የአፍሪካ አየር መንገድ የተመለሰ እንደሆነና ሂደቱን ጠብቆ በቅርቡ አርማው እንደሚቀባ አስረድተውኛል።
ይህ የምዝገባ ኮዱ ET- AUS የሆነ አውሮፕላን የዛሬ አምስት አመት ከካናዳው አምራች ለኢትዮጵያ አየር መንገድ የተላለፈ ሲሆን በአብዛኛው የሀገር ውስጥ በረራዎችን ያከናውናል።
የቤት ካርታ ለማውጣት 1.5 ሚልዮን ብር ጉቦ!
በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ "የማህበራት ማደራጃ" ሚባል ቢሮ አለ፣ ይህ ቢሮ በክፍለ ከተማው ስር ያሉ የማህበር ቤቶችን ይቆጣጠራል።
እና ላለፋት 3 እና 4 አመታት ኦዲት እያረግን ነው ብለው አገልግሎት አንሰጥም ብለው ቆይተዋል። በነዚህ ጊዜያት ታዲያ ጉቦ እየተቀበሉ በውስጥ አገልግሎት ይሰጣሉ፣ አብዛኛው ህዝብ ግን ገንዘብ መክፈል ስለማይችል እየተሰቃየ ይገኛል።
በደረሰኝ መረጃ መሰረት ኦዲቱ ካለቀ ቆይቷል፣ ነገር ግን የሚያስከፍሉት ብር እዳይቀርባቸው የብዙ ሺህ ቤቶች ዶክመንት ቆልፈው ቁጭ አርገዋል። ህዝብ ሲጠይቃቸው "እንጀምራለን" እያሉ አመት ሊሞላቸው ነው። አሁን ላይ ካርታ ለማውጣት እንኳን ጉቦ እስከ 1.5 ሚልዮን ብር እየጠየቁ ነው። ተገልጋይ ግብር ልክፈል ሲል ደሞ ኦዲት ካላለፈ አናስከፍልም ነው መልሳቸው።
እርምት ለማድረግ የሚፈልግ የመስተዳድሩ አካል ካለ መረጃው ይኸው።
ፌስቡክ ላይ የማውቀው ሰው ነው፣ በአንድ ወቅት እንደውም ሄጄበት በነበረ ውጭ ሀገር ተገናኝተን ልጋብዝህ ብሎኝ ነበር።
ታድያ ትናንት "አንድ ውድድር ላይ እየተሳተፍኩ ስለሆነ ድምፅ ስጠኝ" ብሎ ይህን ሊንክ ላከልኝ፣ እኔም ምን ችግር ብዬ ስከፍተው የፌስቡክ username እና password የሚጠይቅ አድራሻውም appzmil.com የሚል ድረ-ገፅ ነበር።
ስለዚህ አላማው ልክ ይህንን መረጃ እንዳስገባሁ አካውንቱን መውሰድ/መጥለፍ ነበር፣ ነገር ግን ሰውየው ያላወቀው ነገር ቢኖር ይህን አውቆ ለህዝብም ማሳወቅ ስራዬ እንደሆነ ነው።
ራሱ ተጠልፎ ይሆን ብዬም አሰብኩ፣ ብቻ እንዲህ አይነት የማጭበርበርያ መልእክቶች ሲደርሷችሁ ጥንቃቄ አድርጉ፣ በተለይ username/password የሚጠይቁ።
"ይህ የቴሌግራም ቻናሌ ግንቦት1/2011ዓም የተከፈተ ነው። የእኔን የስልክ ወጪ ጨምሮ አገልግሎቴን መደገፍ የምትፈቅዱ ጓደኞቼ በ
👉🏿 https://donorbox.org/zemedemedia እና
👉🏿 https://www.paypal.com/paypalme/ZemedkunB በኩል ማገዝ ትችላላችሁ። በተረፈ ለቤተ ክርስቲያኔና ለኢትዮጵያ ሀገሬ የሚጠቅመውን ሁሉ አበረክት ዘንድ አብዝታችሁ ጸልዩልኝ።
Last updated 3 days, 14 hours ago
The first Telecom operator in Ethiopia https://t.me/EthiotelecomChatBot
Last updated 1 month ago
ለማንኛውም አስተያየት እና ጥቆማ 👉 @Esat_tv_comment_bot
🇪🇹ኢሳት የኢትዮጵያ አይን እና ጆሮ🇪🇹
Last updated 1 month ago