ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ ነው። ሰውነትን አስቀድመው ግለሰብን፣ ህዝብና ሀገርን የሚያከብሩ፣ ሚዛናዊ አመለካከትን ያዳበሩ፣ ከጥላቻ አመለካከት የነፁ ኢትዮጵያውያን ቤት ነው።
ያግኙን +251913134524
Last updated 1 month, 2 weeks ago
ስለ መድፈኞቹ የሚወጡ መረጃዎች ለማግኘት የትም መሄድ አያስፈልግም
- የዝዉዉር ዜና
- የአሰልጣኞች አስተያየት
- የተጨዋቾች የህይወት ታሪክ
- ጨዋታዎችን በቀጥታ ስርጭት
ለማስታወቂያ ስራ --> @MKHI7
Last updated 1 month, 2 weeks ago
BoA Social media links
@ https://www.facebook.com/BoAeth
@ https://www.instagram.com/abyssinia_bank
@ https://www.linkedin.com/company/bankofabyssinia/
@ https://twitter.com/abyssiniabank
@BOA_ATM_bot
Last updated 3 weeks, 5 days ago
4 ማግባት
የሰው ልጅ ወንዱ ብዙ ሚስት ፈላጊ (polygamous) ነው። ይህ ታዲያ ተፈጥሯዊ (Biologic) ነው። አንዳንድ ወንዶች ቢያሽሞነሙኑትም ይህን የተፈጥሮ ክጃሎት እውነታ ሊቀይሩት አይችሉም። አላህ ታዲያ በሂክማው ይህን የወንድ ልጅ ፍላጎት (ማስተደርም ስለሚቸግረው) በእስልምና በ 4 ገድቦታል።
ወንድ ልጅ ጀነት ሲገባ ራሱ በብዙ ሁረል አይን ይሸለማል። ሴት ልጅ monogamous አንድ አግቢ ናት። ተፈጥሮዋ አንድ አፍቃሪ ነውና በጀነት ሽልማቷ ባሏ ነው። እንደወንዱ ለሴትም የደስታዋ ምንጭ በተፈጥሮዋ መነጽር እንጂ አሀዳዊ ይሁን አይባልም። ለ ዳልጋ አምበሳ ጥሩ ጨፌ አጭደህ ብታቀርብለት ትርጉም አልባ ነው። አምበሳ ስጋ እንጂ ሳር አይበለም። ዋናው ቁም ነገሩ ሁሉም በተፈጥሮው ልክ በጀነት ይደሰታል።
ብዙ ጊዜ በዚህ ጉዳይ አንዳንዶች ሲሸማቀቁ አንገት ሲደፉ እናያለን። እንግዲህ ካናገራችሁን ዘንድ 4 ሚስቶችን በእስልምና መፈቀዱን ስናስብ ፊጥራ ስለሆነ ኢማናችን ከፍ ይላል። አልሀምዱሊላህ እንላለን። አንዳንዶች በተመታ ሳይኮ ማስተዳደር ከቻለ ነው ሲሉንም እሱንማ ካልቻለ አንድም ሚስት አይፈቀድለትም ብለን ጸጥ እናደርጋለን።
ሌሎች ደግሞ ይመጡና የራሳቸውን phenotype ኤክስፕረስ አድርገው "የመጀመርያዋ ምን ጎድሏት" ይላሉ። በ men genotype ሲመለስ ከጎደላት ይሞላል። ሙሉ ከሆነች ደሞ በርካታ ኒእማን ማን ይጠላል ነው። አስፈቅዶ ከሆነ ይሁን የሚሉም ጨካኞችም አሉ። ይህ ስህተት ነው። አንድ ወንድ ሚስቱን የዚህ አይነት ሁኔታ ላይ ከ genetics profiሏ ውጭ ለምን ያስቸግራታል። የሱ ተፈጥሮ ጣጣን ራሱ ይወጣ።
እንደ ግል ምልከታየ ይህንን ጉዳይ ወንዶች ዞልመውታል። ትግበራው እንዲበላሽም ሴቶች አስተዋጽኦ አድርገዋል። አንድ ወንድ አንድ ሚስቱን በትክክል ማስተዳደር ካቃተው ግን መጨመሩ መፍትሄ አይመስለኝም።
ሂክማው የረቀቀ ጀሊል ተአዲን ስለፈቀደ አልሀምዱሊላህ። ይህንን ያጻፈኝ አንድ የጀነቲክስ ጥናት ሲደመድም እንዲህ ይላል።
The effective population size of females has been larger than that of males throughout human history.
የሲራ ትምህርቶችን ለመከታተል
ይህንን ቻናል ይቀላቀሉ።
「𑁍📲አዲስ አፕ | ተለቀቀ 𑁍」
╭┈⟢🎁የረመዷን ስጦታ
│
│❏መጃሊሱ ሸህሪ ረመዷን
│
│ሊሸይኺል ዑሰይሚን
╰─────────────────╯
╭🎙የደርሱ አቅራቢ:-
├─┈┈┈
│✑አቡ ዐብዲላህ ኢብኑ ኸይሩ
╰──────────────
╭⧿⧿⛉
├⎙አሁኑኑ ዳውንሎድ በማድረግ │ይጠቀሙ!
│
┝ለሌሎችም ሼር በማድረግ የአጅሩ │ተቋዳሽ ይሁኑ!
╰───────────
╭╼╺╼╺╼╺╼╺╼ ╺╼╺╼
┢⎘ ለመሰል ስራዎች ይቀላቀላሉን
┃
┡🖇http://t.me/Yusuf_App1
╰─╼╺╼╺╼╺╼╺╼╺╼╺╼
ነሺዳ + መንዙማ = ዘፈን
በየአመቱ ረመዷን ጠብቀው ይህን ኢስላማዊ የሚል ቅብ ቀብተው የሚለቁ አሉ ረመዳንን በመንዙማና በነሺዳ ሞቅ ሞቅ ለማድረግ ያስባሉ
የሚያስቀውና የሚያሳዝነው እነኚህ መንዙማ እና
ነሺዳ ከታዋቂ ዘፋኞች ሳይቀር ግጥም
እየሰረቁ ነው የሚሰሩት ግን አንሳሳት ሁላችንም ቆም ብለን ልናስብበት ይገባል መንዙማ በማዳመጥ
ወደ አላህ የምንቃረብ አይምሰለን
ፆመኛ ሆነን የሽርክ መንዙማ እየሰማን እንዴት
ወደ አላህ እንቃረባለን
ረመዷን ላይ መንዙማ ከረመዷን ውጪ ዘፈን??
ረሱል ሰለላሁአለዪሂ ወሰለም
የወደደ እኮ እነሱን ነው ሚከተለው።
ሱናቸውን ነው በአቅሙ ልክ እግር በእግር የሚከተለው እንጂ በሳቸው ስም እየነገድ ኪሱን እየሞላ ኡማውን ኢስላማዊ የሚል ስም ሰይሞ በዘፈን አያጠምም
አላህ ይምራን አላህ ከአውቆ አጥፊዎች አያድርገን
ሼር በማድረግ አሰራጩት
✍a.k
ቻናሉ ተቀላቀሉ👇👇
t.me/tdar_ina_islam
t.me/tdar_ina_islam
0ረብ ሃገር ያላችሁ ወገኖች !
~
1- ቤተሰቦቻችሁን እርዱ። መሆንም ያለበት ነው። ግን ድጋፋችሁ የሚጠቀሙበት እንጂ የሚጎዱበት እንዳይሆን ተጠንቀቁ። ለአጉል ሱሶች የሚጠፋ አይሁን።
2- ራሳችሁን አትርሱ። ተቀማጭ ይኑራችሁ። ዛሬ ሰው ተጨካክኗል። እድሜ ልካችሁን ስትልኩ ኖራችሁ በህመም የወደቃችሁ እለት የሚያነሳችሁ እንኳ ላይኖር ይችላል።
3- ብድር ስትሰጡ በሚገባ ተዋዋሉ። መካካድ በዝቷል። አማና የምታስቀምጡበትንም ለዩ።
4- በማይረቡ ሰበቦች የሚወጡ ወጭዎችን ቀንሱ።
5- ጥሩ ክፍያ አላገኘንም እያላችሁ ለወራት ያለ ስራ አትቀመጡ።
6- "አገባሻለሁ" ለሚሉ ጩልሌዎች የዘመናት ጥሪታችሁን አሟጣችሁ አትስጡ። ለትዳር ሲባል ገንዘብ መውጣቱ ችግር የለውም። ገንዘባችሁን እንጂ እናንተን በማይፈልጉ ሰዎች አትሸወዱ ማለቴ ነው።
=
የቴሌግራም ቻናል
https://t.me/IbnuMunewor
መልዕክተኛው ሰዐወ ተቀምጠው ንግግር ያደርጋሉ። ዙርያቸውን ከበው የተቀመጡ የመልዕክተኛው ሰዐወ ባልደረቦች በተመስጦ እና በስስት የመልዕክተኛውን ንግግር እያዳመጡ ነው። ፍፁም እርጋታ ፍፁም ስክነት ስፍራው ላይ ሰፍኗል።
ድንገት ከየት መጣ ያልተባለ አንድ አይሁድ ዘሎ ወደ መሀል በመግባት ነቢን ሰዐወ በሀይል አናቃቸው።
‹‹ሙሀመድ ሆይ! ገንዘቤን መልስልኝ፤ ድሮም ገንዘብ ተበድሮ መጥፋት የዘራችሁ ነው ›› ብሎ ጮኸባቸው።
ይህ ሰው በርግጥ ብድር ለነቢ ሰዐወ አብድሮ ነበር፤ ግና መክፈያ ግዜው አልደረሰም። ሰሀባው የነቢን መታነቅ ሲመለከት በጥድፍያ ሰይፉን መዘዘ፦‹‹ነቢ እባክዎን ይህን አንገት ልቀንጥሰው ይፍቀዱልኝ›› አለም።
ነቢ ሰዐወ ሰከኑ፣ ታገሱ፣ ንዴታቸውን ዋጡ፣ እንዲህም አሉ፦‹‹በስርዐት ብሩን እንዲጠይቀኝ ለርሱ ንገረው፤ ለኔ ደግሞ ብድሬን እንድመልስ ምከረኝ እንጂ አንገት መቁረጥን ምን አመጣው!››
የሁዲው ተናገረ፦‹‹በዝያ በዕውነት በላከህ ጌታ እምላለሁ፤ ብድሬን ልጠይቅህ አልመጣሁም። መክፈያ ግዜውም አልደረሰም። ብዙ ሰለልኩህ፣ ብዙ ፈተንኩህ ግና ያ በኦሪት ይወራለት የነበረው ነቢይ አንተ ሁነህ አገኘሁህ። ትዕግስተኛ ስለመሆንህ ኦሪት ነገረኝ። ዛሬ ልፈትንህ ሽቼ በአክባሪዎችህ ፊት አነቅኩህ ትዕግስትህን ተመለከትኩ።
እነሆ! የአላህ መልዕክተኛ መሆንህን እመሰክራለሁ። የነበረብህንም እዳ ለነዳያን ትመፀውተው ዘንድም ይቅር ብያለሁ ››
ሰለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም
እንኳን አደረሳችሁ
እንኳን አደረስህ/ሽ ብትባሉ እንኳ
እንኳን አብሮ አደረሰን ማለት አይቻልም አደለም እኛ ልንላቸው ይቅርና
እኛ እኮ አልሃምዱሊላህ
ሙስሊሞች ነን ምን አገባን ¿
ፈጣሪ አይወለድ ።
አይደለም ልደት ሊከበርለት ይቅርና
وَقَالُوا اتَّخَذَ الرَّحْمَـٰنُ وَلَدًا
«አልረሕማንም ልጅን ያዘ (ወለደ)» አሉ፡፡
لَّقَدْ جِئْتُمْ شَيْئًا إِدًّا
ከባድ መጥፎን ነገር በእርግጥ አመጣችሁ።
تَكَادُ السَّمَاوَاتُ يَتَفَطَّرْنَ مِنْهُ وَتَنشَقُّ الْأَرْضُ وَتَخِرُّ الْجِبَالُ هَدًّا
ከእርሱ (ከንግግራቸው) ሰማያት ሊቀደዱ፣ ምድርም ልትሰነጠቅ፣ ጋራዎችም ተንደው ሊወድቁ ይቃረባሉ፡፡
أَن دَعَوْا لِلرَّحْمَـٰنِ وَلَدًا
ለአልረሕማን ልጅ አልለው ስለአሉ፡፡
وَمَا يَنبَغِي لِلرَّحْمَـٰنِ أَن يَتَّخِذَ وَلَدًا
ለአልረሕማን ልጅን መያዝ አይገባውም፡
إِن كُلُّ مَن فِي السَّمَاوَاتِ وَالْأَرْضِ إِلَّا آتِي الرَّحْمَـٰنِ عَبْدًا
በሰማያትና በምድር ያለው ሁሉ (በትንሣኤ ቀን) ለአልራሕማን ባሪያ ኾነው የሚመጡ እንጂ ሌላ አይደሉም፡፡
(ሱርቱ መርየም፣ 88 - 93)
ቻናሉ ተቀላቀሉ ሼር አድርጉ👇
t.me/+kKY_gazIcRoyNWQ0
t.me/+kKY_gazIcRoyNWQ0
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ ነው። ሰውነትን አስቀድመው ግለሰብን፣ ህዝብና ሀገርን የሚያከብሩ፣ ሚዛናዊ አመለካከትን ያዳበሩ፣ ከጥላቻ አመለካከት የነፁ ኢትዮጵያውያን ቤት ነው።
ያግኙን +251913134524
Last updated 1 month, 2 weeks ago
ስለ መድፈኞቹ የሚወጡ መረጃዎች ለማግኘት የትም መሄድ አያስፈልግም
- የዝዉዉር ዜና
- የአሰልጣኞች አስተያየት
- የተጨዋቾች የህይወት ታሪክ
- ጨዋታዎችን በቀጥታ ስርጭት
ለማስታወቂያ ስራ --> @MKHI7
Last updated 1 month, 2 weeks ago
BoA Social media links
@ https://www.facebook.com/BoAeth
@ https://www.instagram.com/abyssinia_bank
@ https://www.linkedin.com/company/bankofabyssinia/
@ https://twitter.com/abyssiniabank
@BOA_ATM_bot
Last updated 3 weeks, 5 days ago