ቶኔቶር ሀገረ እግዚአብሔር

Description
ኢትዮጵያ በጥንት ግብጻውያን ቋንቋ ቶኔቶር፣ጵንጥ፣የኩሽ ሀገረ እየተባለች ትጠራለች።ቶኔቶር ሀገረ እግዚአብሔር ማለት ነው።በሌሎች ሀገሮች ስነ ጽሑፍ ኢትዮጵያና አቢሲኒያ በማለት ተገልጻለች።በቻናሉ መንፈሳዊ ትምህርቶች ወደ እናንተ ይደርሳሉ። እግዚአብሔር አምላካችን ቅድስት ሀገር ኢትዮጵያን ከነጣቂው ተኩላ ይጠብቅልን።ድንግል ሆይ የአስራት ሀገርሽን ኢትዮጵያን ጠብቂያት።
ለሌሎችም ያጋሩ ? @tonetore
We recommend to visit

The first Telecom operator in Africa https://t.me/EthiotelecomChatBot

Last updated 2 Monate, 1 Woche her

◉ Welcome to the 433 Films

Best Place To Find All Movies..

🤞For Promo - @Abusheymc

☕️Buy ads: https://telega.io/c/Films_433

Last updated 11 Monate her

"ይህ የቴሌግራም ቻናሌ ግንቦት1/2011ዓም የተከፈተ ነው። የእኔን የስልክ ወጪ ጨምሮ አገልግሎቴን መደገፍ የምትፈቅዱ ጓደኞቼ በ
👉🏿 https://donorbox.org/zemedemedia እና
👉🏿 https://www.paypal.com/paypalme/ZemedkunB በኩል ማገዝ ትችላላችሁ። በተረፈ ለቤተ ክርስቲያኔና ለኢትዮጵያ ሀገሬ የሚጠቅመውን ሁሉ አበረክት ዘንድ አብዝታችሁ ጸልዩልኝ።

Last updated 2 Wochen, 6 Tage her

11 months, 3 weeks ago

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!

የተወደዳችሁ እና የተከበራችሁ የእግዚአብሔር ቤተሰቦች!

በእግዚአብሔር ፍጹም ሰላም እንደምን ሰነበታችሁ?

እኔ በቅዱሳኑ ጸሎት እና ቅድስና የባሕርይ ገንዘቡ በሆነው በእግዚአብሔር ቸርነት ይኸው ዛሬን ደርሻለሁ።

ዛሬ መድረስ ከሱቅ የሚገዛ የሸቀጥ ዕቃ አይደለም።

ዛሬ መድረስ ከመንግሥት መሥሪያ ቤት በስጦታ መጠቅለያ ላስቲክ ታሽጎ የሚሰጥ የስጦታ ዕቃም አይደለም።

ዛሬ መድረስ ከቤተሰብ በውርስ የሚገኝ የውርስ ገንዘብም አይደለም።

ዛሬ መድረስ ከእግዚአብሔር ብቻ የምናገኘው ልዩ ስጦታ ነው።

ስለዚህ አይታለፉም በተባሉ በሞት በተከበቡ ዘመናት ውስጥ አልፈን በሕይወት ዛሬ የመድረሳችን ምሥጢር የእግዚአብሔር የቸርነቱ ምልክት ማሳያ ነው።

በአባታዊ ፍቅሩ እየወደደን፤
በቸርነቱ ብዛት እየጠብቀን ዛሬን ያደረሰን እግዚአብሔር ምስጋና ለስሙ ይሁን!

አሜን!!!

እንግዲህ ይህንን ያህል በእግዚአብሔር በቸርነቱ ብዛት ተጠብቀን ዛሬ ከደረስን ዛሬ ያደረሰንን እግዚአብሔርን እያመሰገንን ለነገው ሕይወታችን ስንቅ የሚሆነውን የእግዚአብሔርን ቅዱስ ቃል ደግሞ አሁን ለጥቂት ደቂቃ በጋራ እንማማራለን።

የትምህርታችን ርዕስ፦
“ለርኵሰት ሳይሆን እግዚአብሔር በቅድስና ጠርቶናል።”
የሚል ነው።
1ተሰ.4፥7

እንደሚታወቀው የዐቢይ ጾም ፪ተኛው ሳምንት "ቅድስት" ይባላል።

የስሙ ስያሜ የቤተ ክርስቲያናችን ሊቅ ከሆነው ከቅዱስ ያሬድ የተገኘ ነው።

በዚህ ወቅት ቤተ ክርስቲያን
በሥርዓተ አምልኮዋ፤
በሥርዓተ ቅዳሴዋ፤
በመዝሙሯና
በስብከቷ ሁሉ ስለ ቅድስና በሰፊው ታስተምራለች።

በቅዳሴ ላይ የሚነበቡ የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎች፦
፩ኛ=በገባሬ ሠናይ ዲያቆን 1ተሰ.4፥1-13
፪ኛ=በንፍቅ ዲያቆን 1ጴጥ.1፥13-ፍ.ም.
፫ኛ=በንፍቅ ካህን
ሐዋ.10፥7-30

ምስባክ፦
"እግዚአብሔርሰ ሰማያተ ገብረ
አሚን ወሠናይት ቅድሜሁ
ቅድሳት ወዕበየ ስብሐት ውስተ መቅደሱ።"
የሚል ሲሆን ትርጉሙም፦
"እግዚአብሔር ግን ሰማያትን ሠራ።
ምስጋናና ውበት በፊቱ፥
ቅዱስነትና ግርማ በመቅደሱ ውስጥ ናቸው።"
ማለት ነው።
መዝ..95(96)፥5

በምሥጢራዊ ትርጉም ሲፈታ ደግሞ፦
"እግዚአብሔርሰ ሰማያተ ገብረ"
እግዚአብሔር ምን ሠራ ትለኝ እንደ ሆነ እግዚአብሔርስ እርሱ እግዚአብሔር ስለሆነ ሰባቱን ሰማያት ሠራ።

"አሚን ወሠናይት ቅድሜሁ"
እምነትና መልካም ምግባር ያለውን ሰው ይወድዳል።

"ቅድሳት ወዕበየ ስብሐት ውስተ መቅደሱ"
ቅዱስ ቅዱስ ተብሎ መመስገንም የባሕሪይ ገንዘቡ ነው።
የሚል ትርጉም አለው።

በዚህ እለት የሚነበበው የወንጌል ክፍልም
ማቴ.6፥16-25 ሲሆን፦

በዛሬው እለት የሚቀደሰው ቅዳሴ ደግሞ ካሉት 14 ቅዳሴያት መካከል "ቅዳሴ ኤጲፋንዮስ" ነው።

አሁን መጀመሪያ ወደ አነሣነው ርዕሰ ጉዳይ ስንመለስ፤

የትምህርታችን ርዕስ፦
“ለርኵሰት ሳይሆን እግዚአብሔር በቅድስና ጠርቶናል።”
የሚል ነው።
1ተሰ.4፥7

እዚህ ላይ ስለ ቅድስና ስናነሣ፤
"ቅድስና" የእግዚአብሔር የባሕሪይ ገንዘቡ ነው።
"አንተ ብቻ ቅዱስ ነህ" ተብሎ የሚዘመርለት እንደ እርሱ ያለ ቅዱስ የትም የለምና።
ራእ.15፥3-4

“አቤቱ፥ በአማልክት መካከል እንደ አንተ ያለ ማን ነው?
በምስጋና የተፈራህ፥
ድንቅንም የምታደርግ፥
በቅድስና የከበረ እንዳንተ ያለ ማን ነው?” ተብሎ እንደ ተጻፈ።
ዘጸ.15፥11

የቅዱሳኑ "ቅድስና" ከእግዚአብሔር በስጦታ ይሰጣቸዋል።

እግዚአብሔር ግን በባሕሪዩ ለዘላለም ቅዱስ ነው።

በመሆኑም ሰማያውያን መላእክት፦
“ቅዱስ፥ ቅዱስ፥ ቅዱስ፥ የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር፤
ምድር ሁሉ ከክብሩ ተሞልታለች"
እያሉ ያለማቋረጥ ቀን እና ሌሊት ያመሰግኑታል።
ኢሳ.6፥3

ስለዚህ፦
“እተካከለው ዘንድ በማን መሰላችሁኝ? ይላል ቅዱሱ።”
ኢሳ.40፥25

እንግዲያውስ ኑ!
እኛም ከቅድስት ሐና ጋር፦
እንደ እግዚአብሔር ያለ ቅዱስ የለም፥
እንደ አምላካችንም ያለ ጻድቅ የለም፤
እያልን እንዘምርለት!
1ሳሙ.2፥2

ስለ እግዚአብሔር የባሕሪይ ቅድስና ከመጽሐፍ ቅዱስ ብዙውን መመልከት እንችላለን።
ኢሳ.57፥15
ሕዝ.36፥20-21
ሉቃ.1፥50
ኢሳ.6፥3
ራእ.4፥8

እንግዲህ ይህ በባሕሪዩ ቅዱስ የሆነው እግዚአብሔር፦

"እኔ እግዚአብሔር አምላካችሁ ነኝና፤ ሰውነታችሁን ቀድሱ፥
ቅዱሳንም ሁኑ፥
እኔ ቅዱስ ነኝና፤
በምድርም ላይ በሚሳብ ተንቀሳቃሽ ሁሉ ሰውነታችሁን አታርክሱ።
እኔ አምላካችሁ እሆን ዘንድ ከግብፅ ምድር ያወጣኋችሁ እግዚአብሔር ነኝ፤ እንግዲህ እኔ ቅዱስ ነኝና እናንተ ቅዱሳን ሁኑ!" ይለናል።
ዘሌ.11፥44-45

እርሱ አባታችን ነው፤
እኛም ልጆቹ ነን፤
ስለዚህ ልጆች በአባታቸው ሊወጡ ስለሚገባ አባታችን እግዚአብሔር እርሱ በባሕሪዩ ቅዱስ እንደ ሆነ እኛም ደግሞ በኑሮአችን ቅዱሳን ልንሆን ይገባል።

ምክንያቱም መጠራታችንም በቅድስና ለቅድስና ነው እና።
1ተሰ.4፥7

ስለዚህ በቅድስና መኖር ያልቻለ ሰው ከተጠራለት ዓላማ ውጪ ሆኖአል ማለት ነው።

በቅድስና መኖር ሲባል ግን ምን ማለት ነው???

እንደ ዘካርያስና እንደ ኤልሣቤጥ የእግዚአብሔርን ትዕዛዝና ሕግጋት
እየፈጸሙ በእግዚአብሔር ፊት ጽድቅን ጠብቆ መኖር።
ሉቃ.1፥6

በተረገመ ትውልድ ውስጥ እንኳ እንደ ኖኅ በእግዚአብሔር ፊት ጻድቅ ሆኖ መገኘት።
ዘፍ.7፥1

ከአፍ ወደ ውጭ የሚወጣው ክፉ ንግግር ሰውን ያረክሳልና ክፉ ከመናገር መቆጠብ።
ማቴ.15፥18
ኤፌ.4፥29
1ሳሙ.2፥3

ከሕሊና ውስጥ ክፉ አሳብን ማስወገድ።

በልብ ውስጥም ቂምን አለመቋጠር።

በጠቅላላው በቅድስና መኖር ማለት የራስን ምኞት ትቶ እንደ እግዚአብሔር ሐሳብና ፈቃድ መኖር ማለት ነው።

ርኩሰት ግን የሥጋ ሥራ ነው።
እርሱም፦
?ዝሙት፥
?ርኵሰት፥
?መዳራት፥
?ጣዖትን ማምለክ፥
?ምዋርት፥
?ጥል፥
?ክርክር፥
?ቅንዓት፥
?ቁጣ፥
?አድመኛነት፥
?መለያየት፥
?መናፍቅነት፥
?ምቀኝነት፥
?መግደል፥
?ስካር፥
?ዘፋኝነት፥ ይህንም የሚመስል ነው። እንደዚህ ያሉትን የርኩሰት ሥራ የሚሠሩ የእግዚአብሔርን መንግሥት አይወርሱም ተበሎ በግልጥ ተጽፎልናል።
ገላትያ 5፥19-21

ኑ!
ቅዱስ እግዚአብሔር በቅድስና እንድንኖር ጠርቶናልና ሀጢአትን ሁሉ ትተን በቅድስና ጎዳና ላይ እንመላለስ!

ለቅድስና ተጠርታችሁ አትርከሱ!

ለዝማሬ ተጠርታችሁ ዘፋኞች አትሁኑ!

ለፍቅር ተጠርታችሁ በጥላቻ አትመላለሱ!

ለዕርቅ ተጠርታችሁ ቂመኞች አትሁኑ!

ለሕይወት ተጠርታችሁ ለሞት እጅ አትስጡ!

በብርሃ ተጠርታችሁ ወደ ጨለማ አትሂዱ!

ለክብር ተጠርታችሁ ለውርደት አትሁኑ!

ደግሞም ይህንን ምክር የሚጥል ሰውን የጣለ አይደለም፥
መንፈስ ቅዱስን በእናንተ እንዲኖር የሰጠውን እግዚአብሔርን ነው እንጂ።
1ኛ ተሰ.4፥8

ስለዚህ "እኔ ቅዱስ ነኝና ቅዱሳን ሁኑ ተብሎ ስለ ተጻፈ የጠራችሁ ቅዱስ እንደ ሆነ እናንተ ደግሞ በኑሮአችሁ ሁሉ ቅዱሳን ሁኑ።”
1ጴጥ.1፥15-16
╭✥✥✥✥✥✥✥✥✥╮
✥┈┈••●◉✞◉●••┈••✥
. አባ ኒቆዲሞስ (ጳጳስ)
. 07/07/2016 ዓ.ም
. ከሕይወት ተራራ ላይ
✥┈┈••●◉✞◉●••┈┈✥
╰✥✥✥✥✥✥✥✥✥╯

1 year ago

የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ የጾመ ነነዌ መልዕክት
++++++++++++++++++++++++++++++++++
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን
'ተንሥእ ወሑር ኅበ ነነዌ ሀገር ዐባይ - ተነሥተህ ወደ ታላቂቱ ከተማ ወደ ነነዌ ሂድ"
ዮና ፩;፪
ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ወኤጲስ ቆጶሳት፤
መንፈሳዊ ተልእኮ ተቀብላችሁ በየተሰጣችሁ ጸጋ በተለያየ ስፍራ ሆናችሁ የምታገለግለ‐ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን፤
በመንፈስ ቅዱስ ልደት የከበራችሁ ምእመናን ወምእመናት ልጆቻችን በሙሉ፤ ዘመንን በዘመን እየተካ፣ መዓቱን በምሕረት እየመለሰ የሚያኖረን እግዚአብሔር እንኳን ለ2016 ዓ.ም ጾመ ነነዌ አደረሰን አደረሳችሁ ለማለት እንወዳለን፡፡

በብሉይ ኪዳን ዘመን የነበሩት የሰው ልጆች በኃጢአት በወደቁ ጊዜ እግዚአብሔር አምላክ የሁሉ አባት በመሆኑ ተወልዶ ብልጫ የለም" እንዲሉ ከእስራኤል ውጭ ወዳለችው ነነዌ ነቢዩ ዮናስንና ነቢዩ ናሆምን ልኳል። በበደል ውስጥ ሆነው ቢጾሙም ሆነ ቢጸልዩ ጸሎቱ ድል የሚነሣ መሥዋዕቱም የሚያስምር አይሆንምና፡ ንስሐም ለድሀና አቅም ለሌለው የሚሰበክ ሳይሆን ከሊቅ እስከ ደቂቅ ያደፈ ሁሉ የሚጠራበት የሕይወት መስታወት ነውና የሕይወት ትንሣኤ በሆነው ንስሐ ነነዌን ለማንሣት ዮናስ ወደ ንጉሡና ወደ ሠራዊቱ የንስሐ ሰባኪ ሁኖ ተልኳል።

ነነዌ ከተማዋ አድጎ፡ ልማቷ ቢሰለጥንም እግዚአብሔር ግን የተመለከታት ፈርሳና ተበላሽታ ነበር፡፡ በፈረሰ ልብ የሚገነቡ ከተሞች የቀን ጉዳይ እንጂ ፍርስራሽ መሆናቸው አይቀሬ ስለሆነ ዛሬ ነነዌ ከታሪክ መዝገብ ላይ ብትሰፍርም በዓይን ግን የምትታይ አይደለችም። ቅድስት ቤተ ክርስቲያን የነነዌን ጾም ያወጀችው ዓመት ሙሉ የተጣላ በነዚህ ሦስት ቀናት እንዲታረቅ፣ ሲካሰስ የሚኖር ሕዝብም ወደፈጣሪው በንስሐ እንዲመለስ ነው።

እግዚአብሔር አምላክ ነቢዩን ወደ ነነዌ ሲልከው፡- “ተነሥተህ ሂድ" ማለቱ በበደል የሳተን በሩቅ ሆኖ መተቸት መንፈሳዊ ተልእኮ ባለመሆኑ ተነሥተን ብንሄድ፣ መንገድ አጋምሰን ወገኖቻችንን ብንፈልግ ሁሉንም ለንስሐ ማብቃት እንደምንችል ሲያስተምረን ነው፡፡ ለመነሣት ስንፍናንና ፍርሃትን ድል መንሣት ያስፈልጋል። ለይቅርታ ስንነሣ ትዕቢትን እናሸንፋለን። ፉክክርን እናርቃለን። ለጋራ ሀገራችን የጋራ መፍትሔ፡ ለጋራ ቤተ ክርስቲያናችን የጋራ መድኃኒትን እናገኛለን።

በሌላ በኩል አምላካችን እግዚአብሔር በደለኛይቱን ከተማ ታላቂቱ ከተማ በማለት ሲጠራት ሕዝቡንም ግራና ቀኙን የማያውቅ በማለት ራርቷል። እግዚአብሔር አምላክ አክባሪ፤ አዛኝ፡ በደለኛውንም በክብር እንጂ በውርደት የማይጠራ አምላክ ነው። እኛም ይህንን የነነዌን ጾም ስንጾም በአንድ በኩል እንጀራን የተራቡ፣ በሌላ በኩል ሰላም የተራቡ ወገኖች ስለአሉን ወደ እነዚህ ወገኖች የንስሐን ስብከት፣ የማጽናናትን መልእክት ይዘን መሄድ አለብን። በተጨማሪም ከቀዬአቸው የተፈናቀሉትን፡ በረሃብ፣ በመታረዝ፣ በጦርነት ውስጥ የሚገኙ ወገኖቻችንን የመከራ ማቅ በሕሊናችን ተሸክመን ስለጸሙ የተውነው የዕለት ቊርሳችንን ለእነርሱ ሞትን ማባረሪያ እንዲሆን ልንፈቅድ ያስፈልጋል።

የተወደዳችሁ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን!

ይህንን የነነዌ ጾም ልንቀበል ዋዜማ ላይ ባለንበት በዚህ ጊዜ በቤተክርስቲያናችን ጥንታዊ ከሆኑት ገዳማት አንዱ በሆነው በዝቋላ ደብረ ከዋክብት አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ገዳም የሚገኙ፣ ዓለሙን ትተው በፈቃዳቸው ረሀብተኛ እና ጥማተኛ ሆነው ሀገርን በጸሎት የሚጠብቁ መነኮሳት ጫካው መኖሪያችሁ፣ ዳዋው ልብሳችሁ፤ ቅጠሉ ምግባችሁ መሆን አይችልም ተብለው የሰማዕትነትን ጽዋ ተጎንጭተዋል፡፡ እነርሱ በሥጋ እየሞቱ እኛም በየቀኑ ሟቾችን እየቆጠርን በኀዘን ለመኖር የተፈረደብን ሆነናል፡፡
ይህ ለእነርሱ ክብር ቢሆንም ለቤተክርስቲያን ግን ታላቅ ደወል ያሰማ ክስተት ነውና ውሉደ ክህነት ቤተክርስቲያናችሁን የምትጠብቁበት፣ የመከራውን ማዕበል ለማለፍ በመንፈሳዊ ፍቅር አንድነትን ማጽናት የሚያስፈልግበት ጊዜ መሆኑን እናሳስባለን፡፡

በመጨረሻም ታላቅ ሀገር ይዘን፣ ምድሩ ሳይጠበን አመል እያጋፋን ነውና ጸማችን፣ ጸሎታችን ቅድመ እግዚአብሔር ደርሶ ለሀገር ደኅንነት፡ ለሕዝብ ድኅነት እንዲያመጣልን፡

እግዚአብሔር ይቅር ብሎን ዘመኑን በምሕረት ያሻግረን ዘንድ በታላቅ ንስሐ፣ በጸሎትና በአስተብቍዖት ወደ እግዚአብሔር እንድንቀርብ አባታዊ መልእክታችንን በመሐሪው አምላክ ስም እናስተላልፋለን።

እግዚአብሔር አምላክ ኢትዮጵያንና ሕዝቦቿን ይባርክ || ወስብሐት ለእግዚአብሔር!!! አሜን።

አባ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት

አዲስ አበባ፡ ኢትዮጵያ
የካቲት 16 ቀን 2016 ዓ.ም

1 year ago
"ቃለ እግዚአብሔር እምድንግል አስተርአየ ፤ ኤልሳቤጥ …

"ቃለ እግዚአብሔር እምድንግል አስተርአየ ፤ ኤልሳቤጥ ኮነት ዓባየ ፤ እስመ ወለደት ነቢየ።" ቅዱስ ያሬድ

እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም መታሰቢያዋን ለሚያደርግ ስሟን ለሚጠራ በስሟ ለድኆችና ለችግረኞች ቀዝቃዛ ውኃ ለሚሰጥ የክብር ባለቤት ከሆነ ከተወደደ ልጅዋ ከጌታችንና ከመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የምሕረት ቃል ኪዳንን የተቀበለችበት በዓል ነው።

ዳግመኛም በዚህች ዕለት የመጥምቁ ዮሐንስ እናት የከበረች ኤልሳቤጥ ዐረፈች።

የእመቤታችን ጣዕሟን ፍቅሯን ያሳድርብን፤ የቅድስት ኤልሳቤጥ በረከት ከእኛ ጋር ለዘለዓለሙ ይኑር። አሜን

እንኳን አደረሰን አደረሳችሁ

እግዚአብሔር ኢትዮጵያንና ሕዝቧን ይባርክ !
ብጹዕ አቡነ ሄኖክ
? @tonetore

1 year ago

ሕንዳዊው ብፁዕ ዶ/ር ር ግ ሪርየስ የጻፉትን መሠረት አድርገው ብፁዕ ዖር ዘካርያስ ሰር ኤፍሬም እንዳት፤ መንበርን ከምድር እስከሰማይ ስቶርያት የሰጣቸው ጌታችን ነው - ኢየሱስም እንዲህ አላቸው፡፡ እውነት እላችኃለሁ እናንተስ የተከተላችሁኝ በዳግመኛ ልደት የሰው ልጅ በክብሩ ዙፋን በሚቀመጥበት ጊዜ እናንተ ደግሞ በአሥራ ሁለቱ የእስራኤል ነገድ ልትፈርዱ በአሥራ ሁለት ዙፋን ትቀመጣላችሁ። ማቴ ፲፱፥፳፰ የሚገርማችሁ መንበርን ለሐዋርያት ሲሰጥ ለይሁዳም ሰጥቶት ነበር፤ ነገር ግን ይሁዳ ሥልጣኑን ስለናቃት፤ መጠራቱን ለምድራዊ ሥራና ቁሳዊ ፍላጎት ስለሸጠ፣ ጌታውን ክዶ ለሰዎች ፍላጎት ስለተንበረከከ መንበሩ ለሌላ ተሰጠች ብሏል፡፡ በርግጥም የይሁዳ ከሐዋርያዊ ጥሪው እና ከተሰጠው መንበር ተዋረደ ለሰማያዊ ሥልጣን ተጠርቶ ምድራዊ፤ ለመንፈሳዊ ክብር ተጠርቶ ቁሳዊ ስለሆነ በምትኩ ማትያስ ተመረጠ፡፡ እሱ ጎደለ እንጅ መንበረ ሐዋርያት አልጎደለም፡፡

ሐዋርያት ያስተማሩት ከጌታችን የተማሩትን ነው፤ የሐዋርያት ተከታዮች የሆኑ ጳጳሳት የሐዋርያትን ትምህርት ለመጠበቅ ሲሉ ሐዋርያት ባስተማሩባቸውና ሐዋርያት በመሠረቷቸው ቦታዎች መናብርትን መሠረቱ፤ መናብርቱ ግጭትና ጭቅጭቅ ለማስነሣት፣ በአንድ ቦታ ተወስኖ ለመቆየት የእኔ እኔ ለመባባል ወይም ልዩነት ለመፍጠር የተቋቋሙ ሳይሆን ትምህርተ ሐዋርያትን ለማስፋፋት እና ለመጠበቅ የተመሠረቱ ናቸው፡፡ መናብርቱ የተመሠረቱበት ዋና ምክንያት ለክፍፍል እና ለልዩነት፣ ወይም ለምድራዊ ዓላማ ሳይሆን ማንም እየተነሣ የራሱ መሠረት እንዳይፈጥር፣ አስተዳደራዊ ማእከላትን ለመፍጠር፤ የሥልጣነ ክህነትን ደረጃ ለመወሰን፣ አገልግሎትን ለማሳለጥ፣ ለወንጌልና ለትምህርተ ሐዋርያት መስፋፋት ሲሆን መናብርቱን ለማቋቋም እንደመሥፈርት የተወሰደው የዐሥራ ሁለቱ ሐዋርያት መቅድመ ትምህርት፤ መሥዋዕትነት፣ ተልእኮና ሥምሪት እንጂ ዘርን፣ ጎሣን፣ ፖለቲካዊ አቋምን መሠረት ያደረገ አይደለም፡፡ መናብርት ለአብያት ክርስቲያናት አንድነት፡' የተበታተነውን አንድ ለማድረግ ሥልታዊ መዋቅር ለመዘርጋት፣ ለወንጌል መስፋፋት እና ለቤተ ክርስቲያን አስተዳደር ለትውፊት መጠበቅ አስተዋጽኦ እንዲያደርጉ
ነው፡፡

እዚህ ላይ በትልቅ አጽንዖት ማየት የሚያስፈልገው የመናብርቱ ምሥረታ ከፖለቲካ ወይም ከመንግሥት መዋቅር ጋር ግንኙነት አልነበረውም፤ ክርስትና እንኳንስ በሮም መንግሥታት መዋቅር ልታቋቍም ይቅርና እንዲያውም በሮማውያን የምትሳደድ ነረች፡፡ የቤተ ክርስቲያን መዋቅር የራስዋን ሐዋርያዊ ተልእኮ መሠረት ያደረገ፣ ሁሉንም የዓለም ሕዝብ በቋንቋው፣ በባህሉ ሳትከፍል በአንድነት ለማዳረስ የተፈጸመ ነው፡፡ ነገር ግን የፖለቲካ መዋቅርን በተከተለችበት ጊዜ ሁሉ የገጠማት ችግር እና ስደት ነው።

፪) መንበር ያለ "ፓትርያርክ" እና ያለ "ሲኖዶስ"

#ይቀጥላል --->

We recommend to visit

The first Telecom operator in Africa https://t.me/EthiotelecomChatBot

Last updated 2 Monate, 1 Woche her

◉ Welcome to the 433 Films

Best Place To Find All Movies..

🤞For Promo - @Abusheymc

☕️Buy ads: https://telega.io/c/Films_433

Last updated 11 Monate her

"ይህ የቴሌግራም ቻናሌ ግንቦት1/2011ዓም የተከፈተ ነው። የእኔን የስልክ ወጪ ጨምሮ አገልግሎቴን መደገፍ የምትፈቅዱ ጓደኞቼ በ
👉🏿 https://donorbox.org/zemedemedia እና
👉🏿 https://www.paypal.com/paypalme/ZemedkunB በኩል ማገዝ ትችላላችሁ። በተረፈ ለቤተ ክርስቲያኔና ለኢትዮጵያ ሀገሬ የሚጠቅመውን ሁሉ አበረክት ዘንድ አብዝታችሁ ጸልዩልኝ።

Last updated 2 Wochen, 6 Tage her