Mereb Media መረብ ሚዲያ

Description
Welcome to our Channel, Mereb Media - መረብ ሚዲያ We provide daily reliable and trusted information.
We recommend to visit

The first Telecom operator in Africa https://t.me/EthiotelecomChatBot

Last updated 2 Monate, 1 Woche her

◉ Welcome to the 433 Films

Best Place To Find All Movies..

🤞For Promo - @Abusheymc

☕️Buy ads: https://telega.io/c/Films_433

Last updated 11 Monate her

"ይህ የቴሌግራም ቻናሌ ግንቦት1/2011ዓም የተከፈተ ነው። የእኔን የስልክ ወጪ ጨምሮ አገልግሎቴን መደገፍ የምትፈቅዱ ጓደኞቼ በ
👉🏿 https://donorbox.org/zemedemedia እና
👉🏿 https://www.paypal.com/paypalme/ZemedkunB በኩል ማገዝ ትችላላችሁ። በተረፈ ለቤተ ክርስቲያኔና ለኢትዮጵያ ሀገሬ የሚጠቅመውን ሁሉ አበረክት ዘንድ አብዝታችሁ ጸልዩልኝ።

Last updated 2 Wochen, 6 Tage her

1 month ago

በወቅታዊ ጉዳይ ከማራ ፋኖ አደረጃጀቶች የተሰጠ መግለጫ፤

ትግላችንን ለዳግም ባርነት ለሚያመቻቹን የብልጽግና እሳቤ አራማጆች አሳልፈን አንሰጥም!!!

ቀን፦ ጥር 18/2017 ዓ.ም

ትግላችን የኅልውና፣ የፍትሕ፣ የነጻነት፣ የሰብዓዊ ክብር ሆኖ እያለ ከፋፋይነት፣ ብልጣብልጥነት፣ አወናባጅነት፣ ከምንም በላይ በሕዝባችን ላይ የፖለቲካ ቁማርተኝነት እሳቤዎችን ከጀርባቸው አንግበው የአማራን ሕዝብ ለዳግም ባርነት ለመዳረግ በሞቱ የሚደራደሩ የአይሁድ ሸንጎ ማኅበርተኞችን ትናንት በአደባባይ ሕዝባችንም ሠራዊታችንም የተመለከተው የአደባባይ ሐቅ ነው።

የብልጽግና ሥርዓት በቅብብሎሽ የተረከበውን አማራ ጠልነት አተልቆ፣ አደርጅቶ፣ አጎምርቶ በሰው ልጆች ታሪክ ታይቶ ተሰምቶ የማያውቅ እልቂት በአማራ ሕዝብና በአማራዊ ማንነት ላይ ውርጅብኝ በሆነበት በዚህ ሰዓት ላይ የአርበኝነት፣ የሐቅና የፍትሕ ትግላችንን በድርድር ሰበብ ለማይጠረቃ የፖለቲካ ፍትወታቸው መወጣጫ መሰላል ለማድረግ የሚሞክሩ  አካላትን ለሠራዊታችንና ለሕዝባችን መግለጥ እንወዳለን።

ከፋፋይነት፣ ይሉኝታ የለሽ ነጣቂነት፣ ልጓም አልባ የሥልጣን ፍትወት ላይ የሚናውዙ አካላት ትግላችንን ትናንት በሕዝባዊ ግንባር፣ ሕዝባዊ ሠራዊት፣ ፋሕፍዴን ዛሬ ላይ ደግሞ  በአማራ ፋኖ ሕዝባዊ ድርጅት ጭንብል ተሸፍነው ትግላችንን ለማቃለል፣ ለማሳነስ የሄዱበት ርቀት እጅጉን አሳዝኖናል።

በደቡብ ወሎ ዞን፣ ዳውንት ወረዳ ልዩ ቦታው ኩርባክ በተባለ ቦታ የጎንደር፣ የጎጃም፣ የሸዋና የወሎ የፋኖ ተወካዮች በሚል ከአፍሪካ ኅብረት፣ ከኢጋድ፣ ከአብይ አሕመዱ ሃገራዊ የምክክር ኮሚሽን ተወካዮች ጋር ንግግሮች መደረጋቸውን ከሂደቱ ጀምሮ በየተቋሞቻችን የመረጃና ደኅንነት ዘርፎቻችን በኩል ስንከታተለው የቆየነው ጉዳይ መሆኑን ሳንገልጽ አናልፍም።

እሚገርመው ደግሞ እነዚህ አካላት ድርድሩን ሚዲያ ላይ ወጥተው በመሪያቸው በአቶ እስክንድር ነጋ እና በፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊው በረ/ኘ/ር ጌታ አስራደ በኩል ገልጸውልናል።

በዚህ መሠረት ከራሳቸው የሚዲያ ማብራሪያ ብቻ ተነስተን ተጠይቆችን በማቅረብ ሕዝባችንም ሆነ ሠራዊታችን ከዚህ እኩይ እሳቤ ራሱን እንዲጠብቅ እንፈልጋለን።

የመጀመሪያው ተጠየቅ፦ አቶ እስክንድር ነጋ፣ ካፒቴን ማስረሻ ሰጤ፣ ረ/ፕ/ር ጌታ አስራደ፣ ኮሎኔል ፋንታሁን ሙሃቤ እና ከሸዋ ማንነቱን በውል ያላወቅነው ግለሰብ በድርድር ሰበብ የኅልውና ትግሉን የማይመጥን፣ የአማራን ሕዝብ ጥያቄዎች በተወሰኑ ቡድኖች ፍላጎት ላይ ብቻ አንጠልጥሎ የጥድፊያው አንድምታ ምንድነው?፤ ያለሕዝብና ያለፋኖ ውክልና አማራውን ቀራንዮ አደባባይ ያቆመው ሥርዓት በተገኘበት መድረክ ላይ ለመገኘት ለምን ደፈራችሁ?

ሁለተኛው ተጠየቅ፦ የአማራ ፋኖ በጎጃም ሙሉ በሙሉ፣ የአማራ ፋኖ በወሎ (ቤተ-አማራ) ከሁለት ክፍለ ጦር ውጭ ሙሉ ለሙሉ፣ የአማራ ፋኖ አንድነት በጎንደር ከሦስት ክፍለ ጦር ውጭ ሙሉ ለሙሉ፣ የሸዋ ፋኖም አንድነት ለመፍጠር የንግግር ሂደት ላይ መሆኑ እየታወቀ ድርጅት የምትሉት ተቋም በምንታገልበት የአማራ ሰማይ ሥር የት ነው ያለው?

ሕዝባዊ ድርጅት በሚል በዲጂታል ሚዲያው የሚለፈፈው ከሐቅ የራቀ፣ ሙሉ ለሙሉ ከፋፋይ፣ መሪዎቹም ከተወሰኑት ወታደራዊ መሪዎች በስተቀር በግብር የተገለጠ ጸረ አማራ አቋም ያላቸው ስለመሆናቸው ማብራሪያና መግለጫችው ኅያው ምስክር ነው።

ታዲያ የአማራ ፋኖ ሕዝባዊ ድርጅት ዘጠና በመቶ የሚሆነውን የፋኖ ኃይል የያዘ ተቋም ነው የሚለው የእስክንድር ነጋ ንግግር የአማራን ሕዝብ የኅልውና ትግል ለማይጠረቃ ግለሰባዊ የሥልጣን ፍትወቱ መጠቀሚያነት እንጅ በእውነት ለአማራ ሕዝብ የኅልውና ትግል የወጣ ታጋይ አለመሆኑን ዳግም አረጋግጦልናል። ምክንያቱም የአማራ ፋኖ ሕዝባዊ ድርጅት መሬት ላይ የሌለ የትግላችን መከፋፈያነት መጠቀሚያ ካርድ ለመሆኑ በየቀጠናው የሚገኙ ፋኖዎችን ጫፍና ጫፍ አቁሞ እስከማታኮስ የዘለቀ ርካሽ የፖለቲካ መቆመሪያ ድርጅት ስለመሆኑ የትናንት ገሐዳዊ ሁነቶች ያረጋግጣሉ።

ድርድርም ውይይትም በመርኅ ላይ የተመሠረተ፣ ሐቀኛ የፖለቲካ ውክልናን የያዘ፣ የትግሉ መሠረተ ሃሳቦች ላይ የቆመ፣ የትግል ፍኖተ ካርታን በግልጽ በማስቀመጥ እነዚህን ሳይነጣጠሉ ሃሳብን የማቅረቢያ አመከንዮዎችን፣ ገሐዳዊ ሐቆችን ያለአንዳች የፖለቲካ ውስልትና በማቅረብ የሕዝብ ጥያቄ ማሸነፍ የሚችልባቸውን መደላድሎች መፍጠር ነው። ቅሉ አቶ እስክንድር ነጋ፣ ረ/ፕ/ር ጌታ አስራደ፣ ካፒቴን ማስረሻ ሰጤ፣ ኮሎኔል ፋንታሁን ሙሃቤ እና ከሸዋ አንድ ግለሰብ በጋራ የተገኙበት ሸንጎ በመርኅ ደረጃ የድርድርን መሠረተ ሃሳቦችን ያላሟላ መሆኑን ማረጋገጥ እንወዳለን።

ከዚህ ጋር ተያይዞ በዚህ የንግግር ሂደት ላይ የተገኙ ዓለምአቀፍ ተቋማት መሬት ላይ ከሌለ ስብስብ ጋር መቀመጣቸው ሥርዓታዊ የዘር ማጥፋት ድርጊት እየተፈጸመበት ያለውን የአማራን ሕዝብ ያላከበረና የማይመጥን አካሄድ በመሆኑ በቀጣይ አስፈላጊ ሆኖ ሲገኝ ሐቀኛ እንዲሁም አካታች ውክልና ከሚሰጣቸው ልሂቃን ጋር ብቻ እንዲሆን መግለጥ እንወዳለን።

በጥቅሉ ዳውንት ላይ የተካሄደው ድርድርም ይሉት ውይይት ሠራዊታችን የማያውቀው ምናልባትም የሚያወግዘው፤ ሕዝባችንን ያሳዘነ የፖለቲካ ቁማር ነው። ይህንን በድፍረት ለማለት የሚያስገድደን ጉዳይም ከእውነት የራቁ ድርጅታዊ ተረኮች (90% የፋኖ ኃይል የድርጅታችን አካል ነው፣ የወከልነውም ይህንን ግዙፍ ኃይል ያለው ፋኖ ነው) የሚሉ፣ የመርኅ፣ የፖለቲካ ውክልና፣ የተዓማኒነት እንዲሁም የአካታችነት የሚሉት ጥያቄዎችና መሰል ጉዳዮች ሲነሱ ውሃ የሚያነሳ ምላሽ የለም።

መላው የአማራ ሕዝብ፣ መላው ሠራዊታችን፣ የሚዲያ አካላት ይህ ጉዳይ በቀላል የሚታይ ባለመሆኑ የአማራ ፋኖ በሸዋ፣ የአማራ ፋኖ አንድነት በጎንደር፣ የአማራ ፋኖ በጎጃም፣ የአማራ ፋኖ በወሎ (ቤተ-አማራ) እና የአማራ ፋኖ ቢዛሞ እዝ ሕዝባችንን ለዳግም ባርነት አሳልፎ የሚሰጥ አደረጃጀትንም ሆነ አስተሳሰብ አጥብቀን ከማውገዝ ባሻገር የምንታገለው ጉዳይ ነው።

የአማራ ፋኖ በጎጃም
የአማራ ፋኖ በሸዋ
የአማራ ፋኖ በወሎ (ቤተ-አማራ)
የአማራ ፋኖ አንድነት በጎንደር እና
የወለጋ ክፍለ ሃገር ፋኖ እዝ (ቢዛሞ)

1 month ago

ቀጥታ ከጎንደር! ፋኖ በታላቁ ገበያ መሃል ሲንጎራደድ የተቀረፀ ቪዲዮ! ሕዝቡ በደስታ አለቀሰ/ "ከፋኖ ውጭ ሌላ እንዳናይ" https://www.youtube.com/watch?v=nb257BCcoNQ

1 month ago
ሰበር ዜና

ሰበር ዜና

የአማራ ፋኖ አንድነት በጎንደር እና የአማራ ፋኖ በወሎ(ቤተ-አማራ) በጋራ በሰሩት ኦፕሬሽን ስትራቴጂካዊ ቦታ የሆነችው ዱራ ላይ ጀብዱ በመሥራት ተቆጣጠሩ።

ዛሬ ጥር 18/2017 ዓ/ም ንጋት ላይ የአማራ ፋኖ አንድነት በጎንደር ዞዛምባ ንጉሱ ክፍለጦር ነፃነት ብርጌድ እና የአማራ ፋኖ በወሎ(ቤተ-አማራ) ላስታ አሳመነዉ ኮር ሃይሉ ከበደ ክፍለጦር 5ኛ(ደሃና መንድሱ) ሻለቃ ከሁለቱም የተወጣጡ የፋኖ አባላት ዋግኽምራ ዞን ደሃና ወረዳ #ዱራ የምትባለው ስትራቴጂካዊ ከተማ ላይ ሰፍሮ የነበረው ሚሊሻና ፖሊስ ላይ ድንገተኛ ጥቃት በመክፈት አካባቢውን ተቆጣጥረዋል።

በዚህ ኦፕሬሽን ባንዳዉ ላይ የደረሰ ኪሳራ አምስት ሙት፣ ሰባት ቁስለኛ፣ ሶስት ምርኮኛ እና ስድስት የነብስወከፍ መሳሪያ ከበርካታ ተተኳሽ እና ትጥቅ ጋር ተማርኳል።

ይህ ኦፕሬሽን ልዩ የሚያደርገው የአማራ ፋኖ አደረጃጀቶች እዉነተኛና መሬት የረገጠ አንድነት እየተፈጠረ በመሆኑ ሁለቱ አደረጃጀቶች የጋራ ዘመቻ መጀመራቸዉ ነው።

በኦፕሬሽኑ ወታደራዊ ስትራተጂክ ቦታዋ #ዱራ ሙሉ በሙሉ ነፃ የወጣች ሲሆን የተረፈው የጠላት ሃይል እግሬ አዉጭኝ ብሎ ወደ ደሃና አምደወርቅ ፈርጥጧል።

"የአማራ ባንዳ አለበት እዳ!"
"አሳመነዉነት ርዕዮታችን፣ ፋኖነት ክንዳችን!"
"ድል ለአማራ ህዝብ"
"ድል ለፋኖ"
ጥር 18/2017 ዓ.ም

የአማራ ፋኖ በወሎ ላስታ አሳመነዉ ኮር የህዝብ ግንኙነት ክፍል እና የአማራ ፋኖ አንድነት በጎንደር ዞዝምባ ንጉሡ ክፍለጦር ህዝብ ግንኙነት ክፍል

መረበኞች ነን መረጃ አጥማጆች!
###
አዲሱን የመረብ ሚዲያ ፌስቡክ ገፅን ይወዳጁ፣ ለወዳጅ ዘመድዎ ጋብዙ።

https://www.facebook.com/share/14tusNR7Kp/

3 months, 3 weeks ago
የመከላከያ አመራሩ ያስገደላት ወጣት!

የመከላከያ አመራሩ ያስገደላት ወጣት!

አብይ አህመድ እና ካድሬዎቹ የፈፀሙት አሰቃቂ ግፍ!

https://www.youtube.com/watch?v=u8aeiDuEhtY

3 months, 4 weeks ago

ቪዲዮው ተለቀቀ!

https://www.youtube.com/watch?v=kfhtQUVqTy8

4 months ago
ቀጥታ ከጦር ግምባር!

ቀጥታ ከጦር ግምባር!

የእስልምና እምነት ተከታዩ የመከላከያ ሰራዊት አባል አፈሙዙን አዞረ!

"ወላሂ አማራ ያሸንፋል፡ አይዟችሁ በርቱ" ይህ ከወንድሞቼ ጋር አልገጥምም ብሎ ወደ ራሱ አባሎች አፈሙዙን  ያዞረው የመከላከያ ሰራዊት አባል ከመሰዋቱ በፊት የተናገረው የመጨረሻ ቃል ነው።

ይህን በወሎ ግምባር የተፈፀመ ከባድ ተጋድሎ ተከታተሉ?

https://www.youtube.com/watch?v=EyxsFpoUhS4

4 months ago

ሰበር የድል ዜና!

በሁለት አቅጣጫ የመጣው  የአገዛዙ ጥምር ጦር ጉዳት ደረሰበት!!

የአማራ ፋኖ በወሎ አማራ ሳይንት መቅደላ ክፍለጦር አካል የሆነው በተንታ ወረዳ የሚንቀሳቀሰው  በፋኖ ሰይድ አለምዬ የሚመራው ቴዎድሮስ ሻለቃን ለማፈን   ከመቅደለ ወረዳ እና ከተንታ ወረዳ በመነሳት  በሁለት አቅጣጫ ፋኖዎች ይገኙበታል ወዳሉበት ቦታ  የወተት 010 ቀበሌ ላይ በመሄድ ተኩስ የከፈተው የአገዛዙ አራዊት ሰራዊት ጥምር ጦር  ከጠዋቱ 12:00 ሰአት  እስከ ረፋዱ 5:00 ሰአት ድረስ ከፍተኛ ትንቅንቅ የተደረገ ሲሆን በዚህም አውደ ውጊያ ላይ የአገዛዙ ጥምር ጦር  ከፍተኛ ጉዳትን አስተናግዷል። 

ከተንታ ወረዳ የመጡት የብርሃኑ ጁላ ጥምር ኃይል  3 ሙት እና  ከ5 በላይ ቀላልና ከባድ ቁስለኛውን ጭኖ ወደመጣበት ተመልሷል።

በተመሳሳይ ከመቅደላ ወረዳ የመጣው ጥምር ጦር ደግሞ ከፍተኛ  ጉዳት የደረሰበት ሲሆን ነገር ግን የደረሰበትን የጉዳት መጠን  በውል ማወቅ አልተቻልም።

19/02/2017 ዓ/ም
አማራ ፋኖ በወሎ
ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ!

መረበኞች ነን መረጃ አጥማጆች!

የቴሌግራም ?https://t.me/MerebMedia24

ፌስቡክ?https://www.facebook.com/profile.php?id=61564373210803

4 months, 1 week ago
ሰበር ዜና!

ሰበር ዜና!

ወታደራዊ አዛዦች የተሳተፉበት አሰቃቂ ግፍ!

በዚህ ምሽት ቀጥታ ስርጭት ከላሊበላ ከተማ!

https://www.youtube.com/watch?v=7c0ta1XAug0

We recommend to visit

The first Telecom operator in Africa https://t.me/EthiotelecomChatBot

Last updated 2 Monate, 1 Woche her

◉ Welcome to the 433 Films

Best Place To Find All Movies..

🤞For Promo - @Abusheymc

☕️Buy ads: https://telega.io/c/Films_433

Last updated 11 Monate her

"ይህ የቴሌግራም ቻናሌ ግንቦት1/2011ዓም የተከፈተ ነው። የእኔን የስልክ ወጪ ጨምሮ አገልግሎቴን መደገፍ የምትፈቅዱ ጓደኞቼ በ
👉🏿 https://donorbox.org/zemedemedia እና
👉🏿 https://www.paypal.com/paypalme/ZemedkunB በኩል ማገዝ ትችላላችሁ። በተረፈ ለቤተ ክርስቲያኔና ለኢትዮጵያ ሀገሬ የሚጠቅመውን ሁሉ አበረክት ዘንድ አብዝታችሁ ጸልዩልኝ።

Last updated 2 Wochen, 6 Tage her